Gulelle Sub City council የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት

Gulelle Sub City council  የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gulelle Sub City council የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት, Government Organization, Addis ababa, Addis Ababa.

"በጎነት " የማህብረሰብን መልካም እሴቶች ያጠነክራል ፡፡/ምክር ቤት ኮሙኒኬሽን 18/12/ 2018 ዓ.ም/"በጎነት" ማህበራዊ ትስስርን ይፈጥራል ፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ይፈታል...
24/08/2026

"በጎነት " የማህብረሰብን መልካም እሴቶች ያጠነክራል ፡፡

/ምክር ቤት ኮሙኒኬሽን 18/12/ 2018 ዓ.ም/

"በጎነት" ማህበራዊ ትስስርን ይፈጥራል ፤ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ይፈታል ፤ የህብረተሰቡን መልካም እሴቶች ያጠነክራል ፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አባይነሽ ቴኒ በተገኙበት ‎በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባራት የአረጋውያንና የአቅመ ደማ ቤት እድሳት ተከናውኗል ፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ ምክር ቤቶች የ13ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ የማጠቃለያ ጉባኤን አካሄዱ ፡፡/ምክር ቤት ኮሚኒኬሽን 12/12/2018 ዓ.ም/የወረዳ ምክር ቤቶች  በበጀት ዓ...
18/08/2026

የጉለሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ ምክር ቤቶች የ13ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ የማጠቃለያ ጉባኤን አካሄዱ ፡፡

/ምክር ቤት ኮሚኒኬሽን 12/12/2018 ዓ.ም/

የወረዳ ምክር ቤቶች በበጀት ዓመቱ አስፈፃሚ አካላትን በመደገፍ ፣ በመከታተልና በመቆጣጠር ፣ የሚያጋጥሙ ብልሹ አሰራሮችን በመቅረፍ ፣ አገልግሎት አሰጣጡ የተሳለጠና ተደራሽ እንዲሆን በመደገፍ ፣ በሁሉም ወረዳዎች ፍትሃዊ የሀብት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በማድረግ እንዲሁም በክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች የአረጋውያንና የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት ፣ የአረንጓዴ አሻራ በችግኝ ተከላና እንክብካቤ ፣ በማእድ ማጋራት ፣ በደም ልገሳ ውጤታማ ስራ መሰራታቸውን በጉባኤው ላይ ተገልጿል ፡፡

ምክር ቤቶች የወረዳ አስተዳድራቸውን የበጀት ዓመት የማጠቃለያ ሪፖርት እቅድ አፈፃፀም በጉባኤው ላይ የገመገሙ ሲሆን በእቅድ አፈጻጸም የታዩ ውስንነቶች በቀጣይ እንዲታረሙ ጥንካሬዎች እንቀጥሉ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ ጉባኤያቸውን አጠናቀዋል ፡፡

ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ አካላት የማጠቃለያ ምዘና እውቅናና ሽልማት ሰጠ ፡፡/ምክር ቤት ኮሚኒኬሽን 07/12/2018 ዓ.ም /የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት በ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ ምዘ...
13/08/2026

ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ አካላት የማጠቃለያ ምዘና እውቅናና ሽልማት ሰጠ ፡፡

/ምክር ቤት ኮሚኒኬሽን 07/12/2018 ዓ.ም /

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት በ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ ምዘና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ አስፈጻሚ አካላት የምክር ቤት አባላት ፣ የሴክተር አመራሮች ፣ ቋሚ ኮሚቴዎች ፣ የመራጭ ተመራጭ ሰብሳቢዎች እና የክብር እንግዶች በተገኙበት የእውቅናና የምስጋና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ ፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ መኩሪያ ጉርሙ በበጀት ዓመቱ አስፈፃሚ አካላትን ከዝግጅት ምእራፍ እስከ ማጠቃለያ ምእራፍ ድረስ በመደገፍ ፣ በመከታተል እና በመቆጣጠር ለአስፈጻሚው አካል አቅም በመሆን የህብረተሰቡ የልማት ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ፣ የመልካም አስተዳድር ችግሮች እንዲፈቱ ፣ አገልግሎት አሰጣጡ እንዲሳለጥ እና ተጨባጭ ለውጥ እንዲመጣ በሱፐር ቪዢን ፣ በድንገተኛ ምልከታ ፣ በገጽለገጽ የሪፖርት ግምገማ እና በመስክ ምልከታ ለተቋማት ጥንካሬያቸውንና ክፍተታቸውን በማሳወቅ ክፍተቶችን እንዲያስተካክሉ የጽሁፍና የቃል ግብረ መልስ በመስጠት ምክር ቤቱ ውጤታማ ስራዎችን ሰርቷል ብለዋል ፡፡

አስፈጻሚ አካላትም የተሰጣቸውን ግብረ መልስ እንደ ግብዓት በመጠቀም የህብረተሰቡን የልማት ፍትሀዊ ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ስራ መስራታቸውን ክቡር አፈ ጉባኤው ገልጸዋል ፡፡

የምዘና ሂደቱንና የምዘና ግኝቶችን አስመልክቶ ጥቅል የሪፖርት ግብረ መልስ የቀረበ ሲሆን ተቋማት ለተገልጋይና ለአገልጋይ ምቹ የስራ አከባቢ በመፍጠር የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱ ቀልጣፋና ተደራሽ በሆነ አግባብ መሰጠት መቻላቸው ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ የተገልጋይ እንግልትና ማመላለስ እየቀነሰ መሄዱ ፤ የሚቀርቡ ቅሬታዎችና አቤቱታዎች መቀነስ መቻሉ ፤ በተቋማት መካከል ቅንጅታዊ ስራዎችን በመተግበር ተመሳሳይ ተግባሮች በጋራ ውጤታማ ስራ መስራቱ ፤ ተቋማት ቴክኖሎጂን በማዘመን አገልግሎት በቴክኖሎጂ መስጠት መቻላቸው በቀረበው የሪፖርት ግብረ መልስ ላይ ተገልጿል ፡፡

በበጀት ዓመቱ ከስድስቱም ቋሚ ኮሚቴዎች ከፍተኛ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ተቋማት የዋንጫና የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ፡፡

የጉለሌ  ክፍለ ከተማ ምክር ቤት የ2018 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም በመገምገም በጀት ዓመቱ ከፍተኛ ውጤት እንዲያስመዘግብ ላደረጉ ቋሚ ኮሚቴዎች ፣ ለመራጭ ተመራጭ ትስስር አደረጃጀት ፣  ለሴት ...
04/08/2026

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት የ2018 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም በመገምገም በጀት ዓመቱ ከፍተኛ ውጤት እንዲያስመዘግብ ላደረጉ ቋሚ ኮሚቴዎች ፣ ለመራጭ ተመራጭ ትስስር አደረጃጀት ፣ ለሴት ኮከስ የምክር ቤት አባላት እንዲሁም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የወረዳ ምክር ቤት ጽ/ቤቶች የምስጋናና የእውቅና ሽልማት ፕሮግራም አካሄደ ፡፡

/ምክር ቤት ኮሚኒኬሽን 28/11/2018 ዓ.ም /

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትን የክፍለ ከተማና የወረዳ ምክር ቤት አባላት ፣ የወረዳ ምክር አመራሮችና ባለሙያዎች ፣ ቋሚ ኮሚቴዎች ፣ የመራጭ ተመራጭና የሴት ኮከስ ሰብሳቢዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ገምግሟል ፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ መኩሪያ ጉርሙ የ2018 በጀት ዓመት በርካታ ውጤታማ ስራ የተመዘገበበት ዓመት ነው ያሉ ሲሆን ፤ ምክር ቤቱ አስፈፃሚ አካላትን በመደገፍና በመከታተል እንዲሁም የ7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ፣ ፍትሀዊና በህዝቡ ዘንድ ታማኒነት እንዲኖረው ሁኖ እንዲጠናቀቅ ምክር ቤቱ ተልዕኮውን ተወጥቷል ብለዋል ፡፡

ምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤውን ወቅቱን ጠብቆ በማካሄድ ፣ የፓርላማና የአዲስ አበባ ከተማ የምክር ቤት አባላት የህዝብ የውይይት መድረኮች ፣ የአረጋውያንና የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት ፣ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላና እንክብካቤ ፣ በማእድ ማጋራት ፣ በደም ልገሳ ውጤታማ ስራ መሰራቱን ተገልጿል ፡፡

በውስንነት የታዩ ተግባራት በቀጣይ የዕቅዱ አካል ተደርገዉ ሊሰራባቸዉ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡

በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈፃፀም ለነበራቸዉ የወረዳ ምክር ቤቶች የዋንጫና የሰርተፍኬት ሽልማት ሲበረከትላቸው ፤ ምክር ቤቱ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግብ ላደረጉ ቋሚ ኮሚቴዎች ፣ የመራጭ ተመራጭ ትስስር አደረጃጀት ፣ የሴት ኮከስ የምክር ቤት አባላት እንዲሁም ለቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች የምስጋናና የእውቅና ሽልማት ሰርቲፊኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡

''ተስፋን እንትከል!" የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር። (ምክር ቤት ኮምኒኬሽን 27/11/2018 ዓ.ም)      የጉለሌ ክፈለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ  አቶ መኩ...
03/08/2026

''ተስፋን እንትከል!" የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር።

(ምክር ቤት ኮምኒኬሽን 27/11/2018 ዓ.ም)

የጉለሌ ክፈለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ መኩሪያ ጉሩሙ በተገኘበት ፣ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ ምክር ቤት አመራሮች እና ባለሙያዎች " በአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር " አረንጓዴ አሻራቸውን በእንጦጦ ተራራ ላይ አሳርፈዋል ።

በመርህ ግብሩ ላይተገኝተዉ መልእክት ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ መኩሪያ ጉርሙ ችግኝን መትከል ሀገርንና ትዉልድን በጽኑ መሰረት ላይ ማቆም ነው ። ችግኝ የተፈጥሮን ሚዛን በመጠበቅ የማይተካ ሚና ስላለው ችግኝን መትከል ሁሉም የህበረተሰብ ክፍል የስራ ባህል ማድረግ ይኖርበታል ብለዋል።

የበጎ ፈቃድ የቤት እድሳት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት| ሐምሌ 24/2018 ዓ.ምበጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የተቸገሩ...
01/08/2026

የበጎ ፈቃድ የቤት እድሳት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል

ጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት| ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም

በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የተቸገሩ ወገኖችን ቤት የማደስ ሥራ በተጠናከረ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል።

በዛሬው ዕለትም በወረዳው ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት አስተባባሪነት በቤት ቁጥር 013 የሚኖሩት የአካል ጉዳተኛው የአቶ ዘካሪያስ ዓለማየሁ ቤት እድሳት በይፋ ተጀምሯል።

በእድሳት ማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክትል አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አባይነሽ ቴኒ፤ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በእርስ መደጋገፍንና አብሮነትን የሚያጎለብት ሰው ተኮር ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም መሰል የደግነት እና የድጋፍ ሥራዎች አሁንም ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።

3ኛው ዙር የአካባቢ ብክለት መከላከል ንቅናቄ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እሸቱ ለማ እና የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ገባኤ የተከበሩ ...
31/07/2026

3ኛው ዙር የአካባቢ ብክለት መከላከል ንቅናቄ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እሸቱ ለማ እና የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ገባኤ የተከበሩ አቶ መኩሪያ ጉርሙ እንዲሁም የክብር እንግዶች በተገኙበት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ተካሄደ::

‎/ምክር ቤት ኮሙኒኬሽን 23/11/2018 ዓ.ም

‎3ኛው ዙር ክፍለ ከተማ አቀፍ የአካባቢ ብክለት መከላከል ንቅናቄ ጽዱ ኢትዮጵያ ለትውልድ” በሚል መሪ ቃል በጉለሌ ክፍለ ከተማ አከባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት አስተባባሪነት የንቅናቄ መርሀ ግብር ተካሄደ ፡፡

በመርሀ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር እሸቱ ለማ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ባለፉት ዓመታት በአዲሰ አበባ በወንዝ ልማት ጥበቃ ፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን በማልማትና በመንከባከብ ፣ አካባቢን ከተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች በመጠበቅ ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገቡን ገልጸዋል ፡፡

ተፈጥሮን መጠበቅ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ድርሻ መሆኑን በመገንዘብ አካባቢ እንዳይበከልና ለጉዳት እንዳይጋለጥ ሁሉም ሰው ሀላፊነቱን እንዲወጣም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ገባኤ የተከበሩ አቶ መኩሪያ ጉርሙ በበኩላቸው አካባቢን በማልማትና በመንከባከብ ለዜጎች ምቹ ፣ ማራኪና ሳቢ አካባቢ ለመፍጠር የሚሰራውን ስራ አድንቀው ፤ ክፍለ ከተማችንና ከተማችን የአካባቢ ጥበቃ ስራን በማጠናከርና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ከተማችን በሁሉም ዘርፍ ተመራጭ ምቹ የማድረግ ስራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል ። የጉለሌ ክፍለ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሀና ምህረቱ በመርሀ ግብሩ ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል ፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለማቃለል ፤ በክረምት በጎ ፈቃድ  የያዛቸውን  ግቦች ለማሳካት በክፍለ ከተማው በሁሉም ወረዳዎች  የበጎ አድራጎት ስራ...
30/07/2026

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለማቃለል ፤ በክረምት በጎ ፈቃድ የያዛቸውን ግቦች ለማሳካት በክፍለ ከተማው በሁሉም ወረዳዎች የበጎ አድራጎት ስራዎችን እየሰራ ነው ፡፡

/ምክር ቤት ኮሙኒኬሽን 23/11/2018 ዓ.ም /

ምክር ቤቱ በክረምት በጎ ፈቃድ በደም ልገሳ ፣ በአካባቢ ጸጥታ ፣ በጽዳት ፣ የአቅመ ደካማና የአረጋውያን ቤት እድሳት ፣ ማእድ በማጋራት ፣ በአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ እና በሌሎች የልማት ስራዎችና ሰው ተኮር ተግባራት ላይ ሰፊ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ፡፡

ምክር ቤቱ በዛሬው እለትም የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት ሀላፊ የተከበሩ አቶ አብርሀም ምስጋናው በተገኙበት በጉለሌ ወረዳ 2 /ሁለት/ እና ወረዳ 5 /አምስት/ የአረጋውያንና የአቅመ ደካማ የቤት እድሳትን አከናውነዋል ፡፡

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት  በክረምት በጎ ፈቃድ የአቅመ ደካማ አረጋውያን የቤት እድሳት በጉለሌ ወረዳ 3 እና ወረዳ 8  አካሄደ ። (ምክር ቤት ኮሙኒኬሽን 21/11/2018 ዓ.ም)ምክር...
29/07/2026

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት በክረምት በጎ ፈቃድ የአቅመ ደካማ አረጋውያን የቤት እድሳት በጉለሌ ወረዳ 3 እና ወረዳ 8 አካሄደ ።

(ምክር ቤት ኮሙኒኬሽን 21/11/2018 ዓ.ም)

ምክር ቤቱ በክረምት በጎ ፈቃድ መርሀ ግብር በርካታ የበጎ ፈቃድ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ፡፡

በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ምክትል አፈ - ጉባኤ ወ/ሮ አባይነሽ ቴኒ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰው ተኮር በመሆኑ የህብረተሰቡን ማህበራዊ ችግሮች በመፍታት ተጠቃሚነትን እያረጋገጥንበትና አብሮነታችን እያሳየንበት እንገኛለን ብለዋል ፡፡

ምክር ቤቱ የተጣለትን ማህበራዊ ሃለፊነት እየተወጣ መሆኑን ገልጸው ፤ የበጎ ፈቃድ ስራዎችን ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ፡፡

‘‘ደሜን ለወገኔ” በሚል መሪ ቃል የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት  የደም ልገሳ መርሀ ግብር አካሄደ ፡፡(ምክር ቤት ኮሚኒኬሽን 20 /11/2018 ዓ.ም /የጉለሌ ክፍለ ከተማ የምክር ቤት አ...
27/07/2026

‘‘ደሜን ለወገኔ” በሚል መሪ ቃል የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት የደም ልገሳ መርሀ ግብር አካሄደ ፡፡

(ምክር ቤት ኮሚኒኬሽን 20 /11/2018 ዓ.ም /

የጉለሌ ክፍለ ከተማ የምክር ቤት አባላት ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ ምክር ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች ‘‘ደሜን ለወገኔ” በሚል መሪ ቃል በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሀ ግብር የደም ልገሳ ፕሮግራም አካሄዱ፡፡

በመርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ አባይነሽ ቴኒ በደም እጥረት ምክንያት ክቡር የሆነው የሰው ሕይወት እንዳይጠፋ የምክር ቤት አባላትና የተቋሙ ሰራተኞች የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ ይገኛሉ ብለዋል ።

ደም መስጠት የዜጎችን ሕይወት የማዳን ታላቅ ተግባር ስለሆነ የምክር ቤት አባላትና የተቋሙ ሰራተኞች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ደም በመለገስ የሚደርስ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ እንደሌለ በመረዳት በዚህ በጎ ተግባር እንዲሳተፉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ፡፡

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gulelle Sub City council የጉለሌ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share