M.O.R East Addis Ababa Branch

M.O.R East Addis Ababa Branch Offcial page of Ministry Of Revenues Easter Addis Ababa Tax Payer Branch Office

መልካም በዐል !
27/05/2026

መልካም በዐል !

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በሚያዚያ ወር 1.44  ቢልዮን  ብር ገቢ ሰበሰበ።…………ግንቦት 10 /2018 የምስራቅ /አ/አ/አነ/ግ /ከ /ቅ/ጽ/ቤትይህ የተገለጸው የሚያዚያ ወር   የስራ አፈፃፀም ከቅ...
18/05/2026

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በሚያዚያ ወር 1.44 ቢልዮን ብር ገቢ ሰበሰበ።
…………
ግንቦት 10 /2018 የምስራቅ /አ/አ/አነ/ግ /ከ /ቅ/ጽ/ቤት
ይህ የተገለጸው የሚያዚያ ወር የስራ አፈፃፀም ከቅ/ጽ/ቤቱ ማኔጅመንት ጋር ውይይት ሲደረግ ነው።
የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ወርቃለም ተሾመ የገቢ እቅዱን 1.44 ቢልዮን በመሰበሰብ 103.05 በመቶ አፈጻጸም ተመዝግቧል ብለዋል ፡፡ ይህ ስኬት በየደረጃው ያሉ ሃለፊዎችና ሰራተኞች እንዲሁም ግብራቸውን በሃላፊነት የከፈሉ ግብር ከፋዮች ውጤት መሆኑን ገልጸው አመሰግነዋል ፡፡በአስር ወራት እየተመዘግበ ያለው አፈጻጸምም የበጀት ዓመቱ ሲጠቃለል የዓመቱ እቅድ እንደሚሳካ የሚያሳይ እንደሆነ ገልጸው ግምገማው በቀጣይ ሊሰሩ በሚችሉ ስራዎች ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግ ተናግረዋል ፡፡
ይህንም ተከትሎ ወሪ/ት ፍሬህይወት ተፈራ የዕቅድና በጀት አፈፃፀም ክትትል ከፍተኛ ባለሙያ የሚያዚያ ወር የስራ አፈፃፀም ሲያቀርቡ ቅ/ጽ/ቤቱ ከቀጥታ ታክሶች፤ ቀጥታ ካልሆኑ ታክሶች እና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች በአጠቃላይ 1.4 ብሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ብር 1.44 ብሊዮን በመሰብሰብ አፈፃፀሙ 103.05% መሆኑን በሪፖርታቸው አሳይተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ከተሰበሰበው አጠቃላይ ገቢ ብር 1.44 ብሊዮን መካከል ብር 1.03 ብሊዮን ከቀጥታ ታክሶች፣ብር 404.92 ሚልዮን ቀጥታ ካልሆኑ ታክሶች እንዲሁም ብር 3.08 ሚሊዮን ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች የተሰበሰበ መሆኑ ተገልጿል።
ወ/ሮ ወላንሳ ወጋየሁ የሰው ሀይል መረጃና አገልግሎት ቡድን አስተባባሪ በሰራተኛ እርካታ ዙሪያ ዳሰሳዊ ጥናት እና ምክረ ሀሳብ አቅርበዋል ፡፡ የማኔጅመንቱም አባላት በጥናቱ ላይ ውይይት በማካሄድ ይህን መሰል ጥናት መጠናከር እንደሚገባው ጠቁመዋል ፡፡
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ስራን ከመገምገም ጎን ለጎን የገቢ አሰባሰብ አቅም ላይ ከፍተኛ መሻሻል ሊያመጣ ያስችላል ያላቸውን የስልጠና ርዕሰ ጉዳይ በመምረጥ አመራሮቹ በሥራቸው ውጤታማነት፣ ውሳኔ መስጠት፣ ቡድን መምራት እና የማስፈጸም አቅም ከፍ እንዲልና የእውቀት አድማሳቸውን ለማስፋት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል ፡፡ በዛሬውም እለት” የስሜት ልህቀት” ”Emotional Intelligence”) በሚል ርዕሰ ጉዳይ ስልጠና በአቶ ሳሙኤል ካሳሁን በዛፋር የንግድ ስራ የሥልጠና እና የኢንቨስትመንት የማማከር አገልግሎት አማካኝነት ተሰጥቷል ፡፡
ወ/ሮ ወርቃለም ስልጠናውን ለሰጡ ለአቶ ሳሙኤል እና ድርጅታቸውን አመስግነው በቀሩት ሁለት ወራት የገቢ አሰባሰብ ሂደት ሁሉም አመራርና ፈጻሚ ሙስናን በመዋጋት፣የአገልግሎት አሰጣጡን በማሻሻልእና ገቢ ሊያስገኙ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረግ እና ሰላማዊ በሆነ የስራ እንቅስቃሴ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥተዋል፡፡ የግንቦት ወር የትኩረት አቅጣጫ ያሉትን አመላክተዋል ፡፡ ምክትል ስራ አስኪያጆችም ከተሰጠው አቅጣጫ አንጻር በዘርፍ የተለዩትን ተቀበለው እንደሚያስፈጽሙ ተናግረዋል።
የማኔጅመንት አባላቱም ዕቅዱን ለማሳካት ያላቸውን ቁርጠኝነት በመግለጽ ስልጠናው ለገቢው ስኬት ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑንና ለስራቸውም አቅም እንደሚሆናቸው ተናግረዋል ፡፡
………….

የሃዘን መግለጫ!ግንቦት 08/2018 ዓ. ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)በገቢዎች ሚኒስቴር ጅማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ በመሆን ሀገራቸውን ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ደሜ ከበደ ገጀአ ባጋጠማቸው...
17/05/2026

የሃዘን መግለጫ!

ግንቦት 08/2018 ዓ. ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

በገቢዎች ሚኒስቴር ጅማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ በመሆን ሀገራቸውን ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ደሜ ከበደ ገጀአ ባጋጠማቸው የጤና እክል ምክንያት በሀገር ውስጥ እና ከአገር ውጭ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ሕይወታቸው በማለፉ የገቢዎች ሚኒስቴር አመራር እና ሰራተኞች የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን!

አቶ ደሜ ከበደ በገቢው ዘርፍ ያላቸውን እውቀት እና የአመራር ክህሎት በመጠቀም ውጤታማ ስራ ከሰሩ አመራሮች መካከል ተጠቃሽ ነበሩ።

የአቶ ደሜ ከበደ የቀብር ስነ-ስርዓት እሁድ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም በጅማ ከተማ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት የሚፈጸም ይሆናል፡፡

የወንድማችን ነፍስ በሰላም ትረፍ!

 # #የበጀት ዓመቱ  የግንቦት ወር  ሞጁላር የተሰኘው  የታክስ  ትምህርታዊ ስልጠና  ተጀመረ………………….      ግንቦት 6/2018 ምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤትየበጀት ዓመቱ  የግን...
15/05/2026

# #የበጀት ዓመቱ የግንቦት ወር ሞጁላር የተሰኘው የታክስ ትምህርታዊ ስልጠና ተጀመረ
………………….
ግንቦት 6/2018 ምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት
የበጀት ዓመቱ የግንቦት ወር ሞጁላር የተሰኘው የታክስ ትምህርታዊ ስልጠና በዛሬው እለት የተጀመረ ሲሆን ወ/ሮ የሺወርቅ ተጫነ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና መረጃ አቅርቦት የስራ ሂደት አስተባባሪ ታክስ በስልጠናው ዙርያ አጠቃላይ ሂደቱ ምን እንደሚመስልና ሰልጣኞች የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት ተግባር ገለጻ አድርገዋል ፡፡የንግድ ስርዓቱ ጤናማ ለማድረግና ግብር ከፋዮም በእውቀት የተመረኮዘ የንግድ እንቅስቃሴ እንዲኖረው ፣ ለሀገሩ ታማኝ ግብር ከፋይ እንዲሆን ከሚያደርግባቸው መንገዶች አንዱ ለ90 ሰዓታት የሚሰጠውን ሞጁላር የተሰኘውን ስልጠና ለግብር ከፋዩ በመስጠት መኆኑን ጠቅሰው ይህም የግብር ከፋዩን ባህሪ እየለወጠ መሆኑንና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ገጽታን ከመገንባት አንጻርም ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ጠቅሰዋል ፡፡
ስልጠናውንም አቶ ተስፋዬ ነጋሽ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ በመጀመሪያ ሴምስተር ከሚሰጠው ስልጠና መሀከል ከመቀጠር የሚገኝ በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያ 1395/2017 መሰረት ለሰልጣኞቹ ማሰልጠን ጀምረዋል ።

ለግብር አሰባሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያደረጉ ካሉና  በታክስ ተገዢነት ክፍተት ከሚታይባቸው  ግብር ከፋዮች ጋር  ስልጠናና  ውይይት ተካሄደ   ……………ምስራቅአ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት/ ግ...
15/05/2026

ለግብር አሰባሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያደረጉ ካሉና በታክስ ተገዢነት ክፍተት ከሚታይባቸው ግብር ከፋዮች ጋር ስልጠናና ውይይት ተካሄደ
……………
ምስራቅአ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት/ ግንቦት 07/2018/
ወ/ሮ ወርቃለም ተሾመ የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ ተቀራርቦ በመስራትና ለሚገጥሙ ችግሮች በጋራ በመሆን መፍትሄ እየተሰጠ በመሄድ የግብር አሰባሰብ ሂደቱን ቀልጣፋ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ የጠቆሙት ለግብር አሰባሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያደረጉ ካሉና በታክስ ተገዢነት ክፍተት ከሚታይባቸው ግብር ከፋዮች ጋር ስልጠናና ውይይት በተካሄደበት መድረክ ላይ ነው ፡፡
በእለቱም በታክስ ህግ ተገዢነትና የኦዲት አሰራር ሂደትን በተመለከተ ወ/ሮ የሺወርቅ ተጫነ የታክስ ከፋዮች ትምህርትና መረጃ አቅርቦት የስራ ሂደት አስተባባሪ እንዲሁም አቶ እሸቱ ኢራጎ የታክስ ከፋዮች መረጃ አቅርቦት ከፍተኛ ባለሙያ በአዲሱ የገቢ ግብር አዋጅ 1395/2017 በተመለከተ ስልጠናዎችን ሰጥተዋል ፡፡
ስልጠናውንም ተከትሎ ስራ አስኪያጂዋ የታክስ ለውጥን በጊዜ ማሳወቅ፣ማናቸውንም ግብር ሂደቶችን በቴክኖሎጅ መጠቀም ፣የኢ-ፔይመንት ክፍያ ስርዓትን መከተል ፣ ሀሰተኛ የግብይት ደረሰኞች መለየት ፣ ሁሉም ግብር ከፋዮች የኪውአር ኮድ ደረሰኝን መጠቀም እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል ፡፡
ወ/ሮ ወርቃለም በፌደራል የገቢ ግብር/ ማሻሻያ / አዋጅ ቁጥር 1395/2017 መሰረት ከተያዘዉ የግብር ዓመት በፊት በነበረዉ ግብር 25% (ሀያ አምስት በመቶ) ቅድመ ግብር ክፍያ ሰኔ 30 የሚዘጉ ግብር ከፋዮች የ2017 የግብር ዘመን ሁለተኛ ዙር የመክፈያ ጊዜ ከግንቦት 1 እስከ የግንቦት 30/2018 ድረስ በመሆኑ ግብር ከፋዮች በውቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ፡፡
በመድረኩም ላይ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ምክትል ስራ አስኪያጆች አቶ ማቲያስ አየለ እና ወ/ሮ ዓለም ታምራት እና የስራ ሂደት አስተባባሪዎች ምላሽ ሰጥተዋል ፡፡

በቅ/ጽ/ቤታችን የተቋማዊ ስጋት ሥራ አመራርና ሥነ-ምግባር ቡድን ሰራተኞች በሆኑት በአቶ ተስፋዬ ግርማ፣ አቶ አዲሱ ኡርጌሳ እና አቶ ጌታሰው አሰፋ በሙያ ስነ-ምግባር፣ በአስቸኳይ ሙስና መከላ...
03/05/2026

በቅ/ጽ/ቤታችን የተቋማዊ ስጋት ሥራ አመራርና ሥነ-ምግባር ቡድን ሰራተኞች በሆኑት በአቶ ተስፋዬ ግርማ፣ አቶ አዲሱ ኡርጌሳ እና አቶ ጌታሰው አሰፋ በሙያ ስነ-ምግባር፣ በአስቸኳይ ሙስና መከላከል እና የሀብት ምዝገባ ህጎች ጋር በተያያዘ ሚያዚያ 24/2018 ዓ.ም በቅ/ጽቤቱ የስብሰባ አዳራሽ አዲስ ቅ/ጽ/ቤቱን ለተቀላቀሉና ስልጠናውን ከዚህ ቀደም ላልወሰዱ አመራሮችና ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቅ/ጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ወርቃለም ተሾሞ የሥነ-ምግባር ስልጠናዎች የቅ/ጽ/ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ህዝብና መንግስት የጣለባቸውን ኃላፊነት በተገቢው ለመወጣት ወሳኝ መሆናቸውን ገልጸው መልዕክት አስተላልፈዋለ፡፡

የክላስተር  ሁለት 3ኛ  ዙር የታክስ እና ጉምሩክ ክበባት የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር በአዘጋጁ ምስራቅ  አዲስ አበባ አነስተኛ  ግብር ከፋዮች  ቅርጫፍ   ጽ/ቤት  አሸናፊነት ተጠና...
02/05/2026

የክላስተር ሁለት 3ኛ ዙር የታክስ እና ጉምሩክ ክበባት የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር በአዘጋጁ ምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርጫፍ ጽ/ቤት አሸናፊነት ተጠናቀቀ ፡፡
…………ሚያዚያ 24/2018 ምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት
የገቢዎች ሚንስቴር የጉምሩክ ኮሚሽን የታክስ እና የቀረጥ ዕውቀትን ለትውልዱ ለማስገንዘብ ያታክስ ክበባትን በማቋቋም የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር እያካሄደ ይገኛል:: ይህንም ተከትሎ በዛሬው እለት የክላስተር ሁለት 3ኛ ዙር የታክስ እና ጉምሩክ ክበባት የተማሪዎች ጥያቄ እና መልስ ውድድር የምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርጫንጫፍ ጽ/ቤትን በወከለው የካ አባዶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ ወሮ ወርቃለም ተሾመ የጥያቄና መልስ ውድድሩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩ ሲሆን "እንደ ሀገር ታማኝ እና ሀላፊነት ያለው ትውልድ ለመፍጠር በታክስና በጉምሩክ ጉዳዮች ዙሪያ እውቀት ያለው ዜጋ መፍጠር አስፈላጊ ነው፣ ታክስ የሀገር ልማት መሠረት ሲሆን ሀገር እንድትገነባ የሚያግዝም ዋና ኃይል ነው" በማለት የመደረኩ ዓላማም "ትውልዱ የታክስ እና ቀረጥ እውቀት እንዲያገኝና ኢትዮጵያ የሀገር ወጭ በሀገር ገቢ ለመሸፈን የምትሄድበትን ጉዞ አጋር እንዲሆን ያስችላል" ብለዋል ፡፡
በክላስተር ሁለት አራት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በማጣመር ውድድሩን በምስራቅ ቅርጫፍ አስተባባሪነት የተካሄደ ሲሆን የምስራቅ አዲስ አበባ አ/አ/አ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት ወክሎ የየካ አባዶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ኃይለ ልዑልየማነ፣ የሰሜን ምዕራብ አ/አ/አ/ግ/ከ/ቅ/ፅ/ቤትን በመወከል ፤ትብለጥ ተገኝ ከእቴጌ መነን የልጃገረዶች 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት ቃል ኪዳን አዲሱ ደግሞ ከለም 2ኛ ደረጃ ት/ቤት, (ቦሌ ኤርፖርት ጉምሩክ እንዲሁም አሜን እስክንድር ቅዱስ ዮሴፍ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት ወክሎ ከመካከለኛ ቁ.1 ግ/ከ/ቅ/ፅ/ቤት ተወዳድረዋል፡፡በዚህም መሰረት ከየካ አባዶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ኃይለ ልዑል የማነ በአንደኛ ደረጃ በማጠናቀቅ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር ክላስተሩን ወክሎ አሸንፏል፡፡የየቅርጫፍ ጽ/ቤት ኋላፊዎች ቅርጫፋቸውን በመወከል ለትምህርት ቤቶች፣ለተማሪዎች ፣ለርዕሳነ መምህራን እንዲሁም ለአብቂ መምህራን እንደየደረጃቸው የሞባይል፣የገንዘብ፣የሞንታርቦ እንዲሁም የዕወቅና ሰርተፍኬት ሽልማት አበርክተዋል፡፡መድረኩን በተመለከተ የማጠቃላያ ንግግር ያደረጉት በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ጉዳዮች ትምህርት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ሲሳይ " በየቅርጫፍጽ/ቤቶች የሚገኙ የታክስ ትምህርትና መረጃ አቅርቦት ስራ ክፍሎች ግብር ከፋዮችን በማስተማር የታክስና ቀረጥ ዕውቀት በማስጨበጥ እንደ ሀገር መንግስት የሰጠውን ትኩረት ተግባራዊ እያደረጉ እንደሆነ እና ትውልድን በመቅረጽ በርካታ ስራዎችን እየሰሩ እንደሆነ ገልጸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ክላስተሩን ወክሎ በአንደኛ ደረጃ ላጠናቀቀው ተማረ ኋይለ ልዑል የማነ በቀጣይ ብርቱ ፉክክር እንደሚጠብቀው በመግለጽ በቂ ዝግጅት ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ከዚህ ጋር አያይዘው ከሽልማት ባሻገር ተማሪዎች የታክስና ቀረጥ ምንነትን ከሀገር ዕድገትና ፍቅር ጋር በማስተሳሰር በሚሰማሩበት መስክ ሁሉ ከውዲሁ ስለ ታክስና ቀረጥ ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ያግዛል ብለዋል፡፡

29/04/2026
ለ December ዘጊ የምስራቅ ግብር ከፋዮቻችን በሙሉ
29/04/2026

ለ December ዘጊ የምስራቅ ግብር ከፋዮቻችን በሙሉ

3 likes. "ለግብር ከፋዮች በሙሉ"

ከዲሴምበር ዘጊዎችና በታክስ ተገዢነት ክፍተት ካሉባቸው ግብር ከፋዮች ስልጠናና  ውይይት ተካሄደ ……………ምስራቅአ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት/ ሚያዚያ 20/2018/ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ኢኮኖሚው የ...
29/04/2026

ከዲሴምበር ዘጊዎችና በታክስ ተገዢነት ክፍተት ካሉባቸው ግብር ከፋዮች ስልጠናና ውይይት ተካሄደ
……………
ምስራቅአ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት/ ሚያዚያ 20/2018/
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በመሰበብሰብ ሀገራዊ ሀላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ፡፡» ወ/ሮ ወርቃለም ተሾመ የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ
ስራ አስኪያጇ ይህን ያሉት በዛሬው እለት ከዲሴምበር ዘጊዎችና በታክስ ተገዢነት ክፍተት ካሉባቸው ግብር ከፋዮች ጋር በተደረገ ውይይት ላይ ሲሆን በታክስ ተገዢነት ክፍተት ያለባቸው ግብር ከፋዮች ወደተሻል የታከስ ስርዓት እንዲመጡ የሚያግዝ ስልጠና እና ውይይት ተካሂዷል ፡፡
ወ/ሮ ወርቃለም ግብር ከፋዩ ወደተሻል የታክስ ስርዓት መምጣት የሚችለው በታክስ ስርዓቱ ላይ የተቀመጡ ህጎችን በአግባቡ መወጣት ሲቻል ነው ብለዋል ፡፡ ይህ መድረክ የተዘጋጀው በገሪጎሪያን አቆጣጠር ገቢ ግብራቸውን ዲሴምበር 30 አሳውቀው ለሚከፍሉና አልፎ አልፎ የህግ ተገዢነት ክፍተት ከታየባቸው ግብር ከፋዮች ጋር ሲሆን በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ 1395/2017 ፣ የህግ ተገዢነት ምንነትና የኦዲት አሰራርን በተመለከተ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል ፡፡ ስልጠናው የተሰጠው በአቶ እሸቱ ኢራጎና በአቶ ሴናመል አብዲሳ ነው ፡፡
ስልጠውን ተከትሎ በስራ አስኪያጇ ወ/ሮ ወርቃለም ተሾመ እና በታክስ ኦፕሬሽን ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አየለ አማካኝነት ውይይት ተደርጓል ፡፡ በውይይቱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከጊዜ ወደጊዜ የስልጠና እና የአገልግሎት አሰጣጡን እያሻሻለ መምጣቱ የተጠሩ ግብር ከፋዮች ገልጸው በግብር አከፋፈል ሂደቱ እየገጠሟቸው ያሉ ችግሮችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
ይህን መነሻ በማድረግ የሚመለከታቸው የስራ ክፍሎች እንዲሁም በስራ አስኪያጇ ወ/ሮ ወርቃለም ተሾመ እና በታክስ ኦፕሬሽን ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አየለ ምላሽና ማብራሪያ ተስጥቷል ፡፡ በተጨማሪም እንደ ግብዓት የሚያገለግሉና በቀጣይ መስተካከል የሚገባቸውን ጉዳዮች በእቅድ ይዘው እንደሚፈቱ ወ/ሮ ወርቃለም ተናግረዋል ፡፡
በመጨረሻም ግብር ከፋዮች ከተጠሩበት መድረክ አንጻር ወርሃዊ ታክሳቸውን እንዲከፍሉ እንዲሁም የዲሴምበር 2025 ዘጊዎች በቀሩት ጥቂት ቀናት ግብራቸውን አሳውቀው ክፍያ እንዲፈጽሙ ጥብቅ ማሳሰቢያ ወ/ሮ ወርቃለም የሰጡ ሲሆን የታክስ ለውጥን በጊዜ ማሳወቅ፣ማናቸውንም ግብር ሂደቶችን በቴክኖሎጅ መጠቀም ፣የኢ-ፔይመንት ክፍያ ስርዓትን መከተል ፣ ሀሰተኛ የግብይት ደረሰኞች መለየት ፣ ሁሉም ግብር ከፋዮች የኪውአር ኮድ ደረሰኝን መጠቀም እንደሚያስፈልግና በግብይት ወቅትም ጥንቃቄ ተገቢ እደሆነ ጠቅሰው ኦዲት የሚደረጉ ግብር ከፋዮችም ትክክለኛ መረጃ መስጠት እንደሚገባቸው አጽንዖት ሰጥተዋል ፡፡

Address

Lem Hotel, Megenagna
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 08:00 - 00:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when M.O.R East Addis Ababa Branch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share