28/08/2026
የሀረሪ ክልል ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ከአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ጋር የልምድ ለውጥ አደረገ::
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገዛኸኝ በቀለ የተመራው የሀረሪ ክልል ምክር ቤት አመራሮች በአዲስ አበባ ምክር ቤት በመገኘት የልምድ ልውውጥ አድርጏል::
የሀረሪ ክልል ምክር ቤት አመራሮች በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የተሰሩ የሪፎርም ስራዎችን በተመለከተ በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጀዋሪያ ቀሊ አማካኝነት ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን በቆይታቸውም ምክር ቤቱ የሰራቸውን የተለያዩ ሪፎርም ስራዎች ተዘዋወረው ጎብኝተዋል::