20/05/2024
#ኢራን
ኢራን በሂሊኮፕተር አደጋ በሞቱት በኢብራሂም ራይሲ ሞትክ ፕሬዝዳንት ሾመች!
የኢራን ምክትል ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ሞክበር አዲሱ የኢራን ፕሬዝዳንት ተደርገው መመረጣቸው ተሰምቷል፡፡
የኢራን ከፍተኛ መሪ ዓሊ ኮማኒ ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ የሚገኙትን ሞክበርን በሄሊኮፕተር አደጋ በሞቱት ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ ምትክ ሾመዋቸዋል፡፡
ኮማኒ ሹመቱን ያስታወቁት በፕሬዝዳንት ራይሲ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ለመግለጽ መልዕክት ባስተላለፉበት ወቅት ነው፡፡