የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን Fire and Disaster Risk Management Commission

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን Fire and Disaster Risk Management Commission

የእሳትና አደጋ  ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን Fire and Disaster Risk Management Commission ይህ ገጽ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ክልል ውስጥ የሚከሰቱ አደጋ ክስተቶችን የቅድመ አደጋ ጥንቃቄ የሚተላለፍበት ገጽ ነው፡፡
(2)

በጷጉሜን እና በአዲሱ ዓመት የበዓላት ሰሞን የአደጋ ስጋትን ለመቀነስ ለ11ዱም ክፍለ ከተማ የብሎክ አመራሮች የተጠናከረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።AAFDRMC ነሐሴ 29/2018 አዲስ...
04/09/2026

በጷጉሜን እና በአዲሱ ዓመት የበዓላት ሰሞን የአደጋ ስጋትን ለመቀነስ ለ11ዱም ክፍለ ከተማ የብሎክ አመራሮች የተጠናከረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

AAFDRMC ነሐሴ 29/2018 አዲስ አበባ

​የአዲስ አበባ ከተማ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ቅነሳ ዘርፍ የጷጉሜን ቀናት እና ከሚጠበቀው የ2019 አዲሱ ዓመት በዓላት ጋር ተያይዞ በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ድንገተኛ አደጋዎችን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችል የተጠናከረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከ11ዱም ክፍለ ከተሞች ለተወጣጡ የብሎክ አመራሮች ስልጠና ሰጥቷል።

​የአደጋ ስጋት ቅነሳ ዘርፍ ምስክትል ኮሚሽነር አቶ ደሳለኝ ፉፋ በስልጠናው ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ በየክፍለ ከተማውና በየአካባቢው የእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ተከስተው የከፋ ጉዳት እንዳያደርሱ ስጋቶችን አስቀድሞ የማወቅና የመከላከል አቅምን ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም የብሎክ አመራሮች ከዚህ ስልጠና ያገኙትን እውቀትና ግንዛቤ ወደ ታች በማውረድ፣ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ በማስተማርና በማሳተፍ በበዓላት ሰሞን የተቀናጀ የአደጋ ደህንነት ንቅናቄ እንዲፈጥሩ አሳስበዋል።

ስልጠናውን የሰጡት በዘርፉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ግንዛቤና ስርፀት ቡድን መሪ አቶ መኩሪያ መንግስቴ እንደ ገለጹት በመዲናችን በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ምክንያቶች የሚከሰቱ አደጋዎችን የመከላከል ስራ ውጤታማ የሚሆነው በህዝብ አደረጃጀቶች ንቁ ተሳትፎ መሆኑን ጠቅሰው፤ የብሎክ አመራሮች ማህበረሰቡን በቀጥታ የሚያገኙ እንደመሆናቸው መጠን ሚናቸው የላቀ መሆኑን አስረድተዋል።በማብራሪያቸው ለብሎክ ለአመራሮቹ የተለያዩ የአደጋ መንስኤዎችንና ቅድመ ጥንቃቄዎችን የተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

​በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ሰልጣኞች በበዓላት ወቅት ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎችን ለመግታት የሚያስችል ጠቃሚ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸው፣ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በመወጣት አዲሱ ዓመት የሰላምና ከአደጋ የጸዳ እንዲሆን አካባቢያቸውን በመጠበቅና ህብረተሰቡን በማንቃት በተነሳሽነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
​ #አደጋስጋትቅነሳ #አዲስአበባ #ጷጉሜን #አዲስዓመት #የአደጋደህንነት

የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የቋጉሜ ቀናትና የአዲስ ዓመት በዓላትን ታሳቢ ያደረገ የወትሮ ዝግጁነቱን ከመቼውም ጊዜ በተለየ መልኩ ማጠናቀቁን አስታወቀ።​አዲስ አበባ...
04/09/2026

የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የቋጉሜ ቀናትና የአዲስ ዓመት በዓላትን ታሳቢ ያደረገ የወትሮ ዝግጁነቱን ከመቼውም ጊዜ በተለየ መልኩ ማጠናቀቁን አስታወቀ።

​አዲስ አበባ | ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (AAFDRMC)

​የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የቋጉሜ ቀናት እና የአዲስ ዓመት በዓላት በሰላምና በፍጹም ደህንነት ተከብረው እንዲጠናቀቁ ከመቼውም ጊዜ በተለየ መልኩ የወትሮ ዝግጁነቱን በሙሉ አቅም ማጠናቀቁን አስታወቀ።

​ኮሚሽኑ የ2018 የቋጉሜ ቀናትና የአዲስ ዓመት በዓላትን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በእቅድ በመምራትና ጠንካራ ተቋማዊ የአደጋ ስጋት ስርዓትን በተከተለ መልኩ ባዘጋጀው የበአል እቅድ ኦሬተሽን መድረክ ላይ ነው ዝግጁነቱን ያሳወቀው።

​በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ቴዎድሮስ ወልደሚካኤል እንደገለጹት፤ መላው የፓራ ሚሊተሪ አባላት በአእምሮ፣ በመንፈስና በስነ-ልቦና ከፍተኛ ዝግጁነት ላይ ይገኛሉ። የሰው ኃይልና የግብአት አቅርቦት በሙሉ አቅም መሟላቱን ያረጋገጡት ዋና ኮሚሽነሩ፣ ህዝባችንን በ24/7 ፈጣን አገልግሎት ለማገልገል ዝግጁ ነን ብለዋል።

አክለውም «የወትሮ ዝግጁነታችን ከግንዛቤ ማስጨበጥ እስከ አደጋ መከላከል የተዘረጋ ነው፤ ከሌሎች ባለድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅትና በተናበበ መልኩ በመስራት የከተማችንን ነዋሪዎች ደህንነት አስተማማኝ ማድረግ ይገባል» ሲሉ ገልጸዋል።

​በሌላ በኩል የቅድመ ዝግጅነት ኦሬንቴሽኑን ያወያዩት በኮሚሽኑ የአደጋ ቅነሳ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ደሳለኝ ፉፋ በበኩላቸው፤ ከማዕከል እስከ ቅርንጫፍ ባሉ መዋቅሮች በሰው ኃይልና በግብአት የተደገፈ ዝግጁነት መደረጉን ገልጸዋል። ከቅድመ መከላከል እስከ ድገንተኛ አደጋ ምላሽ አሰጣጥ ያለው ስርዓት በተደራጀ መልኩ መዘጋጀቱን በመጠቆም፣ በዓላቱ በሰላም እንዲከበሩ ኮሚሽኑ በግንባር ቀደምትነት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

​በውይይቱ ማጠቃለያም የፓራ ሚሊተሪው ክፍሎች፣ የአደጋ ቅነሳ ዳይሬክተሮችና የስራ ቡድኖች በሙሉ የከተማዋን ደህንነት በጥብቅ ዲስፕሊን ለመጠበቅና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር ተናበው ለመስራት ሙሉ ዝግጁነታቸውን አሳይተዋል።

​አደጋ ሲያጋጥም ወይም የስጋት ጥቆማ ሲኖር በነጻ ስልክ መስመር 939 በመደወል ጥቆማ መስጠት ይችላሉ!

​ #አዲስአበባ #የእሳትናአደጋስጋት #የወትሮዝግጁነት #ቋጉሜ #አዲስዓመት2018

የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።AAFDRMC ወላይታ ሶዶ ፦ነሐሴ 28/2018ዓ.ም(ወሬቴድ)በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ጊቢ በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ሕንጻ ላይ ድንገት ተከስ...
03/09/2026

የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።

AAFDRMC ወላይታ ሶዶ ፦ነሐሴ 28/2018ዓ.ም(ወሬቴድ)

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ጊቢ በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ሕንጻ ላይ ድንገት ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ሕንጻ ላይ ዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም መንስኤው ያልታወቀ ድንገተኛ የእሳት አደጋ ተከስቷል።

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋና ጊቢ በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ሕንጻ ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ በሚገኘው የማህበራዊ ዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም መንስኤው ያልታወቀ ድንገተኛ የእሳት አደጋ አጋጥሟል።

የእሳት አደጋዊ በአሁን ሰዓት በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የዩኒቨርሲቲውና የአካባቢው ማህበረሰብ ላደረጉት ትብብር የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ከልብ የመነጨ ምስጋናውን ያቀርባል።

የእሳት አደጋው በአሁን ሰዓት በዪኒቨርሲቲውና በአካባቢው ማህበረሰብ ብርቱ ትግል በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው እና የአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም የሶዶ ከተማ እና የዞን አስተዳደር አካላት ላደረጉት ብርቱ ትብብርና ርብርብ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ከልብ የመነጨ ምስጋና ያቀርባል።

የደረሰው የእሳት አደጋ የከፋ እንዳይሆን መላው ማህበረሰብና የግል ድርቶች ሁሉ ላደረጋችሁት ሁሉአቀፍ ትብብር የዩኒቨርስቲው አስተዳደር በድጋሚ ያመሰግናል።

የእሳት አደጋው መንስዔና የጉዳቱን መጠን በሚመለከተው አካል ተጣርቶ ሲቀርብ ለማህበረሰቡ መረጃ የሚንሰጥ ይሆናል።

ምንጭ:- ወላይታ ሶዶ ቴሌቪዥን

አምራችና ሸማቹ በቀጥታ የሚገናኝባቸው ልዩ የአዲስ አመት ባዛሮች በ11 ከፍለ ከተሞች ለህዝብ ክፍት ሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበዓላት ወቅት የሚከሰተውን የምርት እጥረትና የዋጋ ን...
03/09/2026

አምራችና ሸማቹ በቀጥታ የሚገናኝባቸው ልዩ የአዲስ አመት ባዛሮች በ11 ከፍለ ከተሞች ለህዝብ ክፍት ሆኑ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበዓላት ወቅት የሚከሰተውን የምርት እጥረትና የዋጋ ንረት ለመከላከል አምራቾች ከሸማች ጋር በቀጥታ የሚገናኝባቸው ልዩ የአዲስ አመት ባዘሮችን በ11 ከፍለ ከተሞች በዛሬው ዕለት ለህዝብ ከፍት አድርጓል፡፡

አስተዳደሩ በዛሬው ዕለት የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ከእሁድ ገበያዎች በተጨማሪ በ11 ክፍለ ከተሞች የበዓል ባዛሮች በይፋ ያስጀመረ ሲሆን ሸማቾች ከትራንስፖርት እንግልት ነፃ በሆነ መልኩ በአቅራቢያቸው ከሚገኙ የሸማቾች ሱቆችና የባዛር ማዕከላት መሰረታዊ የግብርናና የኢንዱስትሪ ፍጆታ ምርቶችን ጨምሮ እንደ ሽንኩርት፣ ቅቤ፣ እንቁላል፣ ዱቄት፣ ዘይት እና የባልትና ውጤቶች እንዲሁም የሀገር ባህልና ዘመናዊ አልባሳትና የተለያዩ ጌጣጌጦች፣ የእደ ጥበብ ውጤቶች እና ልዩ ልዩ የፅዳት ዕቃዎች በስፋት ቀርበዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የክፍለ ከተሞቹ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የ በዛሬው ዕለት የተከፈቱትን ባዛሮች በስፍራው በመገኙት በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን፤ ዛሬ ከተከፈተው ልዩ የአዲስ ዓመት ባዛሮች በተጨማሪ በከተማዋ በሚገኙ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ላይ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው በቀጥታ እየቀረበ ይገኛል፡፡

እነዚህ የዘመን መለወጫ በዓል ልዩ ባዛሮች ከዛሬ ነሀሴ 28 ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም ድረስ በድምቀት የሚቆይ ሲሆን ነዋሪዎች ወደ ባዛሩ እና ወደ በገቢያ ማእከላት እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ገቢያ በመምጣት የቀረቡትን ሰፊ የገበያ አማራጮች በመጠቀም ተመጣጣኝ እና ጥራት ያለው ግብዓት መሸመት እንደሚችሉ ተነግሯል፡፡

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬ...
03/09/2026

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል።

‎በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል።

‎ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው።
‎ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።

Today, I oversaw the signing of a landmark Framework for Cooperation between the National Bank of Ethiopia and the IFC to establish our country’s first dedicated Mortgage Refinance Company.

Capitalized at 100 Billion ETB, with the IFC set to contribute a minimum of $200 million, this wholesale institution will resolve long-standing liquidity mismatches in our banking sector and unlock accessible mortgage financing across Ethiopia.

This partnership is a critical step toward realizing our goal of delivering 1.5 million affordable, dignified homes for Ethiopian families while expanding private-sector participation in our financial system. Ethiopia continues to build a modern, resilient, and inclusive economy.

የጳጉሜን ቀናት ስያሜዎች
03/09/2026

የጳጉሜን ቀናት ስያሜዎች

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፉ Act For Early Years  ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” ተብለው እውቅና ተሰጣቸው።ይህ እውቅና የከንቲባ አዳነች አቤቤ አመራራቸውንና...
02/09/2026

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፉ Act For Early Years ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” ተብለው እውቅና ተሰጣቸው።

ይህ እውቅና የከንቲባ አዳነች አቤቤ አመራራቸውንና የከተማ አስተዳደሩ ለሕፃናት እድገት እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት በተለይም በ"የአዲስ አበባ የወደፊት ተስፋ የቅድመ ልጅነት እድገት ተነሳሽነት" የተሰጠ እውቅና ነው።

ኢኒሼቲቩ ቀዳማይ ልጅነትን በመንግሥታት ፖሊሲዎች እና በዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት አጀንዳ ማዕከል ላይ ለማስቀመጥ በትኩረት ይሰራል።

ይህ እውቅና የተሰጠው ከቀድሞው የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም አቀፍ ትምህርት ልዩ መልዕክተኛ ጎርደን ብራውን በኩል የኢኒሼቲቭ አጋሮች በመወከል ሲሆን ፣ UNICEF እና UNESCOን ጨምሮ ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የተሰጠ ነው።

እውቅናው አዲስ አበባን በአፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት እድገት የከተማ አመራር ተምሳሌት ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያጠናክረው ይታመናል።

02/09/2026
የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎችጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
02/09/2026

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች

ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”

ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”

ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”

ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”

ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”

Address

Pissa
Addis Ababa
PISSA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን Fire and Disaster Risk Management Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን Fire and Disaster Risk Management Commission:

Shortcuts

Share