የቱሪዝም ሚኒስቴር-ኢትዮጵያ Ministry of Tourism-Ethiopia

የቱሪዝም ሚኒስቴር-ኢትዮጵያ  Ministry of Tourism-Ethiopia Official Corporate page of the F.D.R.E. Ministry of Tourism – Dedicated to Realizing Ethiopia’s Full Tourism Potential 🇪🇹

ኢትዮጵያ፡ የተፈጥሮ፣ የታሪክ እና የዘመናዊነት....!ጥንታዊቷና ውቢቷ ኢትዮጵያ፤ በተፈጥሮ ጸጋዎቿ፣ በታሪኳና ማህበራዊ እሴቶቿ ታላቅ የቱሪዝም ገነት ስለመሆኗ ምስክር አያስፈልገውም። ከተራሮ...
02/09/2026

ኢትዮጵያ፡ የተፈጥሮ፣ የታሪክ እና የዘመናዊነት....!

ጥንታዊቷና ውቢቷ ኢትዮጵያ፤ በተፈጥሮ ጸጋዎቿ፣ በታሪኳና ማህበራዊ እሴቶቿ ታላቅ የቱሪዝም ገነት ስለመሆኗ ምስክር አያስፈልገውም።

ከተራሮች እስከ ዝቅተኛው የጨው ሜዳ፣ ከጥንታውያን የድንጋይ ውቅር ሕንጻዎች እስከ ዘመናዊ የከተማ መዝናኛዎች ድረስ ኢትዮዽያ ለዓለም ህዝብ የምታቀርበው አስደናቂ እይታና የማይረሳ ገጠመኝ እጅግ ብዙ ነው።

የኢትዮጵያን ተፈጥሮአዊ ውበት ልዩ ከሚያደርጉት መዳረሻዎች መካከል የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።

በአስደናቂ የተራራ ሰንሰለቶቹ የሚታወቀው ይህ ስፍራ እንደ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እና የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮ ያሉ ብርቅዬ እንስሳት መኖሪያ ነው።

በተመሳሳይ መልኩ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የአፍሮ-አልፓይን ሥነ ምህዳር መገለጫ በመሆን ለተፈጥሮ አፍቃሪያን ልዩ እርካታን ይሰጣል።

ወደ ምስራቁ የሀገራችን ክፍል ስናቀና ደግሞ በአፋር ክልል የሚገኙት ኤርታአሌ እና ዳሎል የተፈጥሮ ተአምራትን ይገልጡልናል።

ኤርታአሌ በዓለም ላይ ካሉ ጥቂት ንቁ የእሳተ ገሞራ ሐይቆች አንዱ ሲሆን ዳሎል ደግሞ በተለያዩ ቀለማት ባበቡ የጨው ሜዳዎቹ የሚታወቅ ልዩ ተፈጥሮ ነው።

በተጨማሪም የዓባይ ምንጭ የሆነው ጣና ሐይቅ በዙሪያው ከሚገኙት ደሴት ገዳማትና ከታላቁ የዓባይ ፏፏቴ ጋር ተደምሮ ጎብኚዎችን በምትሐታዊ ውበቱ ያፈዝዛል።

የሰው ልጅ መገኛ ብቻ ሳትሆን የጥንታዊ ሥልጣኔዎች ባለቤትም የሆነችው ኢትዮጵያ ከድንጋይ ተፈልፍለው የተሰሩት የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት እና የአክሱም ሐውልቶች የኢትዮዽያን የገዘፈ ጥንታዊ ሥልጣኔ ይመሰክራሉ።

እንዲሁም የጎንደር ፋሲል አብያተ መንግሥታት የመካከለኛውን ዘመን ታሪክ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። በቅርቡ የተከናወነው የቅርስ እድሳት ደግሞ ታሪክን ከውበት ጋር በማጣመር ለጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርጎታል።

በዩኔስኮ የተመዘገበችው የሐረር ከተማ በኮሪደር ልማት በተዋቡ ጎዳናዎቿ፣ በቀለም ባሸበረቁ ባህላዊ ቤቶቿ እና እንግዳ ተቀባይ ባህሏ ልዩ ውበትን ትፈነጥቃለች።

ከዚህ በተጨማሪ በቅርብ ዓመታት ውስጥ የመዲናዋ አዲስ አበባ ከተማ ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ እየተቀየረ ይገኛል።

የከተማ ቱሪዝምን በአዲስ መልክ ያደሱት ብሔራዊ ቤተ መንግሥት፣ አንድነት ፓርክ እና ወዳጅነት ፓርክ ታሪካዊ እሴቶችን ከዘመናዊ የመዝናኛ ስፍራዎች ጋር አጣምረው ለህዝብ ክፍት ሆነዋል።

ከዚህም በተጨማሪ የታሪክ ታላቅነት የሚያወሳው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ ከተፈጥሮ ጋር ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን የሚያጣመረው እንጦጦ ፓርክ እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ከቱሪዝም ጋር የሚያገናኘው የሳይንስ ሙዚየም የመዲናዋን የወደፊት ራዕይ እና የፈጠራ አቅም ለዓለም የሚያሳይ ድንቅ እይታዎች ሆነዋል።

ኢትዮጵያ የተፈጥሮ፣ የታሪክ፣ የባህል እና የዘመናዊነት ውህደት የሆነች፣ እያንዳንዱ እርምጃ አዲስ ታሪክና ውበት የሚተርክባት፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደር የሌላት እውነተኛ የቱሪዝም ገነት ናት።

የቱሪዝም ዘርፍ በሀገራዊ የሪፎርም ለውጥ ላይ ስኬታማ ጉዞ በማድረግ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ተሸጋገረ።ነሀሴ 2018 ዓ.ምአዲስ አበባ፤የቱሪዝም ሚኒስቴር የሙያ ምድብ፣ የሥራ ፍሰት አደረጃጀት እና ...
01/09/2026

የቱሪዝም ዘርፍ በሀገራዊ የሪፎርም ለውጥ ላይ ስኬታማ ጉዞ በማድረግ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ተሸጋገረ።

ነሀሴ 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፤

የቱሪዝም ሚኒስቴር የሙያ ምድብ፣ የሥራ ፍሰት አደረጃጀት እና የቴክኒካል ብቃት ማዕቀፍ ዝግጅት በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች የግምገማ መድረክ ተካሄደ።

በመድረኩ ላይ የተገኙት እንደገና አበበ (ዶ.ር) የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ፣ ዘርፊ ለኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማላቅ ሪፎርሙ ትልቅ እድል እንደፈጠረለት ይህንንም በብቃት መፈጸም የሚችል ጠንካራ ሲቪል ሰርቫንት በመገንባት ዘርፊን ወደተሻለ ምዕራፍ ማሸጋገር ለነገ የማይባል ሥራ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም፣ የላቀ ሀገራዊ እድገትን ለማረጋገጥና ዘመናዊ አሰራርን ለማስፈን ያለሙ የሪፎርም ሥራዎች በበለጠ ቁርጠኝነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

ለተደረገው ክትትልና ድጋፍ ለኮሚሽኑ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ሚኒስትሩ፣ የተቋሙን አደረጃጀትና የሥራ ፍሰት ማሻሻል ለሕዝብ እና ለባለድርሻ አካላት የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና ለማረጋገጥ ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አንስተዋል።

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሪፎርም ትግበራው ባሳየው የላቀ ርብርብ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የተግባር ምዕራፍ መሸጋገሩን በግምገማ መድረኩ ላይ አብስረዋል።

ኮሚሽነሩ ለተገኘው የላቀ ውጤት የተቋሙ ከፍተኛ አመራር ላሳየው ቁርጠኝነትና መሪነት ምስጋና አቅርበው፣ በቀጣይም ከሪፎርሙ የሚጠበቀውን ውጤት ለማምጣት ተቋማቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

በመድረኩ የቀረበው የሪፎርም ጥናት የተቋሙን አሰራር ለማዘመን፣ የሙያ ብቃትን ለማሳደግ እና የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሳለጥ የሚያስችሉ ቁልፍ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን አመላክቷል።

ይህ ስኬታማ የሪፎርም ምዕራፍ መሸጋገር ተቋሙ ወደፊት ለሚያከናውናቸው የዲጂታልና የቴክኖሎጂ ትራንስፎርሜሽን ሥራዎች ጠንካራ መሠረት የሚጥል ነው።

ለክልሎችና ከተማ አስተዳደር  የቱሪዝም ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ቱሪዝም ፖሊሲ አተገባበር ላይ  የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።ነሃሴ 25/2018 ዓ.ም -አዳማ የኢትዮጵያን የቱሪ...
31/08/2026

ለክልሎችና ከተማ አስተዳደር የቱሪዝም ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ቱሪዝም ፖሊሲ አተገባበር ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።

ነሃሴ 25/2018 ዓ.ም -አዳማ

የኢትዮጵያን የቱሪዝም ፖሊሲ አተገባበር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማጠናከር፣ በፌዴራልና በክልል ተቋማት መካከል ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር ለማጎልበት እና በፖሊሲው ላይ የጋራ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ የንቅናቄና የአቅም ግንባታ ስልጠና ለክልልና ከተማ አስተዳደር የቱሪዝም ቢሮ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሰጥቷል።

የቱሪዝም ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ስልጠናውን የሰጡት የስትራቴጂክ ዩኒቲ ክፍል አስተባባሪ አቶ ቴዎድሮስ ደርበው እንደገለጹት፣ የቱሪዝም ፖሊሲው የቱሪዝም ተወዳዳሪ እና ዘላቂ የቱሪዝም ልማትን ለማረጋገጥ ፓሊሲው ዋና መሰረት መሆኑን ጠቅሰዋል።

አክለውም በፖሊሲው ሰነድ ላይ በዝርዝር የተቀመጡትን የነባርና አዳዲስ የቱሪዝም መስህቦች ልማት፣ የመሠረተ ልማት መስፋፋት፣ የገበያና ማስተዋወቅ ስራዎችን ማጠናከር፣ የአገልግሎት ጥራትን ማሻሻል እና የዘርፉን ተቋማዊ አቅም ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች በፖሊሲው በተቀመጡት አዳዲስ ስልቶች ላይ ሰፊ ገለጻና ውይይት ተካሂዷል።

በስልጠናው ወቅት የቱሪዝም ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የፖሊሲው ዋነኛ የትኩረት መስክ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ዘርፉን ከጥንታዊ አሰራር ለማላቀቅ የሚያስችል የዲጂታል ቱሪዝም ሮድማፕና ስትራቴጂ በተግባር እንደሚውል ተብራርቷል።

ዘመናዊ የቱሪዝም መዳረሻዎችን (Smart Tourism Destinations) በማልማት የጎብኚዎችን ተመክሮ ለማሻሻልና የመዳረሻዎችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራም ተጠቁሟል።

በመጨረሻም፣ ፖሊሲው በመንግሥት፣ በግሉ ዘርፍ፣ በማህበረሰብ እና በልማት አጋሮች መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እና ሀገሪቱን በአፍሪካና በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው በስልጠናው ተገልጿል።

በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከክልል ቱሪዝም ቢሮዎች እና  ከከተማ አስተዳደሮች  ጋር የዕቅድ ትስስርና የተመክሮ ልውውጥ ወይይት ተደረገ።ነሀሴ 24/22018 ዓ.ም አዳማ ዉይይቱ የክልሎች...
30/08/2026

በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ከክልል ቱሪዝም ቢሮዎች እና ከከተማ አስተዳደሮች ጋር የዕቅድ ትስስርና የተመክሮ ልውውጥ ወይይት ተደረገ።

ነሀሴ 24/22018 ዓ.ም
አዳማ

ዉይይቱ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ዕቅዶች ከቱሪዝም ሚኒስቴር እና ከዘርፉ ስትራቴጂያዊ ግቦች ጋር ተናብበው እንዲፈጸሙ እንዲሁም የተሻለ ቅንጅትና ትብብር እንዲኖር ያስችላል ተብሏል።

የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የቱሪዝም ቢሮ የ2019 የቱሪዝም ዘርፍ እቅዳቸውን አቅርበው ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል።

በውይይቱ የ2019 የሪፖርት አቀራረብ ፎርማት፣ የዕቅድ አፈጻጸምን ለመለካት የሚያስችሉ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓቶች፣ የመለኪያ መስፈርቶች እና የፕሮጀክቶች አፈጻጸም ደረጃዎች ላይ ሰፊ ምክክር ተካሂዷል።

በተለይም በአገልግሎት ጥራት ማሻሻያ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ የቱሪስት አገልግሎቶች ቁጥጥር፣ የእውቅናና የደረጃ ማረጋገጫ ሥርዓት፣ የአጠቃላይ የጥራት አስተዳደር ፣ የሆስፒታሊቲ ባለሙያዎች ምዘና እንዲሁም የመዳረሻዎች መረጃ ሥርዓት ድጋፍ ጉዳዮች በውይይቱ ተዳሷል።

እንዲሁም በሚኒስቴሩ እና በክልሎች ደረጃ የፖሊሲ ትግበራ፣ የስትራቴጂያዊ ግቦች አፈጻጸም፣ የትልልቅ ፕሮጀክቶች ክትትል እና የፋይናንስ አጠቃቀም ቁጥጥር ሂደቶች ቀርበው ልምድ ልውውጥ ተደርጓል።

በመጨረሻም በቱሪዝም ሚኒስቴር የእቅድና በጀት ክትትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብስራት ታደሰና በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ  ወደ ላቀ ደረጃ ለማሽጋገር በተቀናጀ አሰራር፣ በጋራ እቅድ እና በተናበበ ሪፖርት  መተግበር እንደሚገባ ተገለጸ። እንደገና አበበ(ዶ.ር) ሚኒስትር ዴኤታቱሪዝም ሚ...
29/08/2026

የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሽጋገር በተቀናጀ አሰራር፣ በጋራ እቅድ እና በተናበበ ሪፖርት መተግበር እንደሚገባ ተገለጸ።
እንደገና አበበ(ዶ.ር) ሚኒስትር ዴኤታ

ቱሪዝም ሚኒስቴር
አዳማ፣ ነሐሴ 2018 ዓ.ም.

በቱሪዝም ዘርፍ የመካከለኛ ዘመን የልማት ኢንቨስትመንት ዕቅድና 2019-2021 በተዋረድ ዕቅድ ትስስር ላይ የፌደራል፣ የክልልና የቱሪዝም ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ያሳተፈ ወይይት በአዳማ እየተካሄደ ነው።

የቱሪዝም ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ጉልህ ድረሻ አስተዋጽኦ ብሎም ለሥራ እድል ፈጠራና ለሀገር ገጽታ ግንባታ ያለውን ሚና ለማጠናከር የተቀናጀ አሰራር ተግባራዊ ማድግር አስፈላጊነትን ተገልጿል።

በተለይም በፌደራል፣ በክልልና በከተሞች የሚከናወኑ የቱሪዝም ሥራዎች የጋራ እቅድ፣ የጋራ ትግበራና የጋራ ክትትል ስርዓት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በአንክሮ አመላክተዋል ።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ.ር ) እንደገለጹት ከ2019 እስከ 2021 ዓ.ም. በሚተገበረው የመካከለኛ ዘመን የልማት እቅድ መነሻነት የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የፖሊሲ፣ የስትራቴጂ፣ የሀብት ልየታ እና የተቋማዊ አቅም ግንባታ ሥራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ፣ የእቅዱ ስኬት በሁሉም አስተዳደራዊ እርከኖች ባለው የትብብር ደረጃ እንደሚወሰንም ገልጸዋል።

አክለውም የኢትዮጵያን የቱሪዝም ሀብቶች በተቀናጀ ሁኔታ ለዓለም አቀፍ ገበያ ማስተዋወቅ፣ አዳዲስ የቱሪስት ምንጭ ገበያዎችን መለየት፣ የጋራ የማስተዋወቂያ መድረኮችን ማዘጋጀትና የዲጂታል ማስተዋወቂያ አሰራሮችን ማጠናከር በቀጣይ ጊዜ ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።

በተጨማሪም የቱሪዝም አገልግሎት ጥራትን ማሻሻል፣ የዘርፉን ኢንቨስትመንት ማበረታታት፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር እና የጎብኚዎችን እርካታ ማሳደግ የቅድሚያ ትኩረት የሚያገኙ ጉዳዮች መሆናቸው ተጠቅሷል።

መድረኩ በየክልሉ ያሉ ልዩ የቱሪዝም አቅሞችን በመጠቀም የባህል፣ የኮንፈረንስና የንግድ ጉባኤ (MICE)፣ የጤና፣ የምግብና የስፖርት ቱሪዝም ምርቶችን በጥራት ለማበልጸግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን መለየትና እነዚህ የቱሪዝም ምርቶች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገቢ ከማሳደግ ባሻገር የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም ለኢኮኖሚው ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቶት እንዲኖራቸው ታሳቢ አድረጎ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

የመካከለኛ ዘመን የልማት ኢንቨስትመንት ዕቅድና በ2019-2021 ዕቅድ ትስስር የተመለከተው ሰነድ በአቶ ብስራት ታደስ የእቅድና በጀት ክትትል ስራ አስፈጻሚ በኩል ቀርቦ ውይይት ተደረጎበታል።

በመጨረሻም በተነሱ ጥያቄዎች ላይ በአቶ ግርማ መላኩ የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ እና በሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች በኩል ምላሽና ማብራሪያ የተሰጡ ሱሆን የመድረኩ ተሳታፊዎች የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ በጋራ እቅድ ዝግጅት፣ በተቀናጀ ትግበራ፣ በመደበኛ ክትትልና ግምገማ እንዲሁም በተቋማት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከየክልሉ ለተውጣጡ የምግብና የመስተንግዶ ተቋማት የደረጃ አሰጣጥ መስፈርት ውይይት አካሄደ፤ነሀሴ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባየኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴር ከሀገሪቱ ልዩ ልዩ ክ...
27/08/2026

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከየክልሉ ለተውጣጡ የምግብና የመስተንግዶ ተቋማት የደረጃ አሰጣጥ መስፈርት ውይይት አካሄደ፤

ነሀሴ 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴር ከሀገሪቱ ልዩ ልዩ ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለተውጣጡ የሆቴል እና የምግብ አቅርቦት (Catering) ተቋማት ባለቤቶችና ተወካዮች የተዘጋጀ የምግብና መስተንግዶ አገልግሎት መስጫ ተቋማት የደረጃ አሰጣጥ መስፈርት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተቋማቱን አገልግሎት ጥራት ለማሳደግ፣ የንጽህና እና የምግብ ደህንነት ደረጃዎችን ለማሻሻል እንዲሁም የደንበኞችን እርካታ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የደረጃ መስፈርቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የደረጃ አሰጣጡ ዋና ዋና ትኩረቶች፦
· የምግብ ደህንነትና ንጽህና፦ የኩሽና፣ የዕቃዎችና የሰራተኞች ንጽህና አጠባበቅ ደረጃዎች።
· የአገልግሎት ጥራትና ሙያዊ ብቃት፦ የምግብ አዘጋጆችና የመስተንግዶ ሰራተኞች የሙያ ብቃትና የደንበኞች አያያዝ።
· የተቋማት መሰረተ-ልማት፦ የሆቴሎችና የኬተሪንግ ተቋማት ቁሳቁስ፣ የቦታ ምቹነትና የደህንነት መመዘኛዎች።
ይህ የደረጃ አሰጣጥ አሰራር በሀገር አቀፍ ደረጃ በዘርፉ የሚሰጡ አገልግሎቶችን አንድ አይነትና ደረጃቸውን የጠበቁ በማድረግ የሀገሪቱን የቱሪዝምና የመስተንግዶ ዘርፍ ይበልጥ ለማፎካከርና ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ሴት አርቲስቶች ማህበር ለቱሪዝም ሚኒስቴር የሻደይ፣ አሸንድዬ፣ አሸንዳ፣ ሶለል እና የሽኖዬ በዓል የመልካም ምኞት መግለጫ አቀረቡ።አዲስ አበባነሀሴ 20/2018የኢትዮጵያ ሴት አርቲ...
26/08/2026

የኢትዮጵያ ሴት አርቲስቶች ማህበር ለቱሪዝም ሚኒስቴር የሻደይ፣ አሸንድዬ፣ አሸንዳ፣ ሶለል እና የሽኖዬ በዓል የመልካም ምኞት መግለጫ አቀረቡ።

አዲስ አበባ
ነሀሴ 20/2018

የኢትዮጵያ ሴት አርቲስቶች ማህበር አባላት በቱሪዝም ሚኒስቴር በአካል በመገኘት ለሶለል/ሻደይ/አሸንዳ/አሸንድዬ እና ሽኖዬ በዓላት እንኳን አደረሳችሁ የሚል የመልካም ምኞት መግለጫ አቅርበዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች እንደገና አበበ (ዶ.ር) እና ስለሺ ግርማ የተገኙ ሲሆን፣ ለማህበሩ አባላት ስለ ተደረገው ጥሪና ላቀረቡት መልካም ምኞት ምስጋና አቅርበዋል።

በስነ-ስርዓቱ ወቅት እንደተገለጸው የቱሪዝም ሚኒስቴር አሸንዳ፣አሸንድዬ፣ ሽኖዬ፣ ሻደይ፣ ሶለል እና እንግጫ ነቀላን ጨምሮ በርካታ የሀገሪቱን ባህላዊ በዓላት ዋና ዋና የቱሪዝም ሀብቶች (Tourism Products) አድርጎ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ቱሪስቶች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል።

የሴት አርቲስቶች ማህበር ያደረገው ይህ ጥረት የሀገሪቱ የባህል እሴቶች ሳይበረዙና ሳይበላሹ ለተከታይ ትውልድ እንዲተላለፉ እንዲሁም በቱሪዝም መስክ ጎልተው እንዲወጡ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተመልክቷል።

በ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤ (RC76) "ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ" ተ አስተዋወቀች::​ነሐሴ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ​ኢትዮጵያ ያሏትን እምቅ የቱሪዝም ሀብቶች በማል...
25/08/2026

በ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤ (RC76) "ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ" ተ አስተዋወቀች::

​ነሐሴ 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

​ኢትዮጵያ ያሏትን እምቅ የቱሪዝም ሀብቶች በማልማትና በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ረገድ ከዘርፉ ተዋናዮች ጋር በቅርበት እየሰራች ይገኛል። በዚህም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚዘጋጁ አውደርእዮች፣ የቱሪዝም ንግድ ትርኢቶች፣ የቢዝነስ ለቢዝነስ (B2B) መድረኮች እና ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በመጠቀም የቱሪዝም ማስተዋወቅና የሀገር ገጽታን የመገንባት ሥራዎች በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወኑ ነው።

​በዚህ መሠረት በአድዋ ድል መታሰቢያ ተከፍቶ ለ3 ቀናት በሚቆየው 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤ (RC76) ላይ ከ47 የአፍሪካ አባል ሀገራት የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ የዓለም ጤና ድርጅት አመራሮች፣ የተባበሩት መንግሥታት ኤጀንሲዎች፣ የልማት አጋሮችና በርካታ ዓለም አቀፍ እንግዶች ተገኝተዋል።

​በዚሁ ጉባኤ ላይ የቱሪዝም ሚኒስቴር በመገኘት «ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያን» ለታዳሚዎቹ የማስተዋወቅና ባህላዊ የኢትዮጵያን ቡና የማቅመስ መርሐ ግብር አካሂዷል።

24/08/2026
በመዲናዋ የተተገበሩ የኮሪደር እና ወንዝ ዳርቻ ልማቶች የነዋሪዎችን ጤና እና የአኗኗር ዘይቤ የሚያዘምኑ ናቸው************በአዲስ አበባ እየተተገበሩ ያሉ የኮሪደር እና ወንዝ ዳርቻ ልማ...
23/08/2026

በመዲናዋ የተተገበሩ የኮሪደር እና ወንዝ ዳርቻ ልማቶች የነዋሪዎችን ጤና እና የአኗኗር ዘይቤ የሚያዘምኑ ናቸው

************
በአዲስ አበባ እየተተገበሩ ያሉ የኮሪደር እና ወንዝ ዳርቻ ልማቶች ከገጽታ ግንባታ ባለፈ የነዋሪዎችን ጤና እና የአኗኗር ዘይቤ የሚያዘምኑ መሆናቸውን የ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ ተሳታፊዎች ተናገሩ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶች ጎስቋላ ገጾቿን አስውበው ወንዞቿንም ከተፈጥሮ ጋር አስታርቀው የዓለም የስበት ማዕከል አድርገዋታል፡፡

የ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ስብሰባ ተሳታፊዎች ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከልና ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን ለማስፋፋት ዓላማ ያደረገ የጋራ የእግር ጉዞ አካሂደዋል፡፡

ከ56 አገራት የመጡ የጤና መሪዎች እና ባለሙያዎች የተሳተፉበት የእግር ጉዞው ከአድዋ ድል መታሰቢያ ተነስቶ በከተማዋ የእግረኛ መንገድ በመከተል መስቀል አደባባይ ላይ የተጠናቀቀ ነው።

የእግር ጉዞው “ንግግርን ወደ ተግባር” በሚል መሪ ሐሳብ የ3.5 ኪሎ የሸፈነ ሲሆን፣ የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ እየተተገበሩ ያሉ የኮሪደር እና ወንዝ ዳርቻ ልማቶች ከገጽታ ግንባታ ባለፈ ለነዋሪዎች ጤና እና የአኗኗር ዘይቤ የሚያዘምኑ መሆናቸውን ለኤ ኤም ኤን ተናግረዋል፡፡

ኮሪያዊቷ ካይ ሚን ኪን እና ኢንዶኔዥያዊዉ አይረማን ትሪታማ እንዲሁም ጃፓናዊቷ ኤኒቢስኪ የመዲናዋ ዝና በተለያዩ አማራጮች ከመከታተል ባለፈ በአካል ተግኝተን ስንመለከት ግርምትን ፈጥሮብናል ብለዋል፡፡

የከተማዋን ውበት፣ ጽዳት እንዲሁም የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶችን ያደነቁት ተሳታፊዎቹ ይህም ለነዋሪዎች የኑሮ ዘይቤ ለማሻሻል እና ጤና ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በከተማዋ ሁለንተናዊ ለዉጥ መደመማቸዉን የገለጹት ደግሞ ከተማዋን በተዳጋጋሚ የጎበኙ ሴራዊሊዮናዊዉ ቲቪን ካግባ እና ጊኒያዊዉ ዶክተር ሻማሪ ኪፔላ ናቸው፡፡

በከተማዋ የተገነቡ መሰረተ ልማቶች መዲናዋ ለጤና ዘርፉ ተመራጭ ጤናማ ትዉልድም የሚገነባባት ትሆን ዘንድ እድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡

ከተማዋ ፕሮጀክቶችን በጥራት እና በፍጥነት የማጠናቀቅ ተግባር ለሌሎች ሀገራትም በተሞክሮ መልክ የሚቀመር ነዉ ብለዋል፡፡

አዲስ አበባ ከተማ ላይ ሆነዉ ወዳጅ ዘመድ እና ጓደኞቻቸዉ ከመላዉ ዓለም አዲስ አበባን ይጎበኙ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በከተማዋ ፕሮጀክቶችን በጥራት እና በፍጥነት የማጠናቀቅ ተግባር ለሌሎች ሀገራትም ተሞክሮ የሚሆን ነውም ብለዋል፡፡

Address

Africa Avenue
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:45 - 05:45

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቱሪዝም ሚኒስቴር-ኢትዮጵያ Ministry of Tourism-Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የቱሪዝም ሚኒስቴር-ኢትዮጵያ Ministry of Tourism-Ethiopia:

Shortcuts

Share