𝙨𝙪𝙛𝙞𝙮𝙖𝙣 𝙟𝙚𝙢𝙞𝙡

𝙨𝙪𝙛𝙞𝙮𝙖𝙣 𝙟𝙚𝙢𝙞𝙡 Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from 𝙨𝙪𝙛𝙞𝙮𝙖𝙣 𝙟𝙚𝙢𝙞𝙡, Public School, Ethiopia , addis ababa, Addis Ababa.

﴿ رَبَّنَآ أَفْرِغْ عَلَيْنَا صَبْرًۭا وَتَوَفَّنَا مُسْلِمِينَ ﴾
Our Lord, pour out on us patience and cause us to die as Muslim
🤲🤲🤲🤲🤲❤🤲🤲🤲🤲
ጌታችን ሆይ! በእኛ ላይ ትዕግስትን አፍስስ፡፡ ሙስሊሞች ኾነን ግደለን፡፡

| Surah Al-A’raf (7:126)

30/07/2026

በቂያማ እለት ሚዛን ላይ የከበዱ ተግባራቶች!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿بَخٍ بَخٍ لِخمسٍ ما أثقلَهُنَّ في الميزانِ: لا إلهَ إلّا اللهُ، وسبحانَ اللهِ، والحمدُ للهِ، واللهُ أكبرُ، والولَدُ الصالِحُ، يُتوَفّى للمرْءِ المسلِمِ فيَحتَسِبُهُ﴾

“አምስት ነገሮች በመልካም ስራ ሚዛን ላይ ሲቀመጡ ክብደታቸው ምነኛ ታላቅ ነው! ምነኛ ድንቅ ናቸው! ላኢላአሃ ኢለላህ፣ ወሱብሃንአላህ፣ ወልሃምዱሊላህ፣ ወላሁ አክበር የሚሉት የዚክር ቃላቶችና አንድ ሙስሊም መልካም (ሷሊህ) የሆነ ልጁ ሞቶበት አላህ ዘንድ ምንዳን በመሻት የሚያደርገው ትዕግስት።”

📚 ሶሂህ አልጃሚ፡ 2817

☑ በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦

Telegeram፦ https://bit.ly/4ayf0xJ

Whatsup፦ https://bit.ly/486xnrS

Facebook፦ https://bit.ly/41zEZkk

Instagram፦ https://bit.ly/4arMbTx

X፦ https://bit.ly/41tIUPv

Youtube፦ https://bit.ly/3UTTSwh

Tik tok፦ https://bit.ly/442V9nM

30/07/2026

ኢየሱስ የተለከ ነቢይ ነው!

እኔ በራሴ ሥልጣን አልተናገርኩም፤ እኔ የምለውንና የምናገረውን ትእዛዝ የሰጠኝ የላከኝ አብ ነው።

— ዮሐንስ 12:49

Facebook :- ጥሪያችን Tiriyachen

30/07/2026

ያልተወለደ አምላክ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

112፥3 አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ

ጥንት ላይ የነበሩ ነቢያት እንዲሁ ኢየሱስ እና ሐዋርያት አሓዳዊያን"Unitarian" የነበሩ ሲሆን ከሐዋርያት ኅልፈት በኃላ የተነሱ የቤተክርስቲያን አበው ደግሞ በሂደት "አንድ አምላክ አብ ነው፥ ኢየሱስ ሁለተኛ አምላክ ሌላ አምላክ ነው" የሚል አቋም ያላቸው "ክልዔታውያን"Binitarian" ነበሩ። ከክልዔታውያን አበው መካከል ከ 100 እስከ 165 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው ዮስጦስ ሰማዕቱ"Justin Martyr" ስለ አልተወለደው አምላክ "ብቸኛውን ያልተወለደ አምላክ"The only unbegotten God" በማለት እንዲህ ይለናል፦
"እኛም እንዲሁ ደግሞ በቃሉ ስላሳመንን ከእነርሱ(ከአጋንንት) ርቀን ቆመን "ብቸኛውን ያልተወለደ አምላክ" በልጁ እንከተላለን"።
The First Apology (St. Justin Martyr) Chapter 14

"ብቸኛውን ያልተወለደ አምላክ" የሚለው ይሰመርበት! ይህ አምላክ ብቻ የማይወለድ እና የማይሞት ነው፥ ምክንያቱም እርሱ አምላክ ነው። ነገር ግን ከእርሱ ወዲህ ያሉት ሁሉም ነገሮች የተፈጠሩ እና የሚሞቱ ናቸው፦
"አምላክ ብቻ የማይወለድ እና የማይሞት ነው፥ ምክንያቱም እርሱ አምላክ ነው። ነገር ግን ከእርሱ ወዲህ ያሉት ሁሉም ነገሮች የተፈጠሩ እና የሚሞቱ ናቸው"።
Dialogue with Trypho (Justin Martyr) Chapter 5

አስቂም አሰቃቂም የሚሆነው ይህ ያልተወለደ አምላክ "የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል ላይ ታየ" የማይባል መሆኑን መናገሩ ነው፦
"በጣም ትንሽ ዕውቀት ያለው ሰው ካልሆነ በቀር፦"የሁሉም ነገር ፈጣሪ እና አባት የሰማይ ነገርን ሁሉ ትቶ በትንሽ የምድር ክፍል ላይ ታየ" ብሎ ለማስረገጥ አይደፈርም"።
Dialogue with Trypho (Justin Martyr) Chapter 60

ከ 130 እስከ 202 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው ኢራንዮስ ዘልዮን"Irenaeus of Lyon" ይህ አንድ አምላክ "ለተፈጠሩ ነገሮች ሁሉ አይገዛም" በማለት ተናግሯል፦
"አምላክ ለተፈጠሩ ነገሮች ሁሉ አይገዛም፥ ነገር ግን የተፈጠሩ ነገሮች ሁሉ ለአምላክ ይገዛሉ"።
Against Heresies (St. Irenaeus) Book V(5), Chapter 5 Number 2

ከ 169 እስከ 183 ድኅረ ልደት የአንጾኪያ ኤጲስ ቆጶስ የነበረው ቴዎፍሎስ ዘአንጾኪያ"Theophilus of Antioch" ደግሞ አንዱ አምላክ ጅማሮ የሌለው፣ ያልተወለደ፣ የማይለወጥ፣ የማይሞት እንደሆነ ነግሮናል፦
"እርሱ ጅማሮ አልባ ነው፥ ምክንያቱም ያልተወለደ ነው። እርሱ የማይለወጥ ነው፥ ምክንያቱም እርሷ የማይሞት ነው"።
To Autolycus (Theophilus of Antioch) Book I(1) Chapter 4

ከ 313 እስከ 386 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም"Cyril of Jerusalem" አንድ አምላክ የሚለው የክርስቶስን አባት ሲሆን ስለ አልተወለደው አንዱ አምላክ፦ "አምላክ አንድ፣ ብቻውን ያልተወለደ፥ መጀመሪያ፣ ለውጥ፣ ወይም ልዩነት የሌለው ነው" ይለናል፦
፨ "አንድ አምላክ አለ፥ እርሱም የክርስቶስ አባት ነው"።
Catechetical Lectures (Cyril of Jerusalem) Lecture 4 Number 16
፨ "በመጀመሪያ ስለ አምላክ ያለው ትምህርት በነፍስህ ውስጥ እንደ መሠረት ይኑር! አምላክ አንድ፣ ብቻውን ያልተወለደ፥ መጀመሪያ፣ ለውጥ፣ ወይም ልዩነት የሌለው ነው"።
Catechetical Lectures (Cyril of Jerusalem) Lecture 4 Number 4

እንደ ክልዔታውያን እምነት አንዱ አምላክ ያልተወለደ አብ ሲሆን ኢየሱስ ግን "ሁለተኛ አምላክ" "ሌላ አምላክ" ነው፦
፨ "ቢሆንም እኛ "ሁለተኛ አምላክ" ብለን ልንጠራው እንችላለን፥ "ሁለተኛ አምላክ" በሚለው ቃል ስንጠራው ሌሎችን በጎነቶችን የማካተት ችሎታ ካለው በጎነት በቀር ምንም ማለት እንዳልሆነ ይወቁ።
Origen Against(Contra) Celsum, Book 5 chapter 39
፨ "መጻሕፍትን ስለ ተረዳችሁ ላሳምናችሁ እሞክራለሁ፥ እኔ ከምለው ነገር አለ እና አለ ከተባለው፣ ለሁሉን ነገር ፈጣሪ የሚገዛ "ሌላ አምላክ" እና ጌታ አለ። እርሱም መልአክም ተብሎም ተጠርቷል"።
Justin Martyr, Dialogue with Trypho, chapter 56

በዚህ ዳራ በ325 ድኅረ ልደት በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት የተጠራው የኒቂያ ጉባኤ የማታ ማታ ኢየሱስን "ቴዎን ኤክ ቴዉ" Θεὸν ἐκ Θεοῦ ብሎታል፥ "ቴዎን ኤክ ቴዉ" Θεὸν ἐκ Θεοῦ ማለት "ከአምላክ የተገኘ አምላክ ነው" ማለት ነው። "አምላክ አምላክን አህሎ እና መስሎ፣ ከባሕርይ ባሕርይ ወስዶ፣ ከአካል አካል ወስዶ ተወለደ" በማለት "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዮስ" Ο Θεός ο γιος ብለውታል፥ "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዮስ" Ο Θεός ο γιος ማለት "እግዚአብሔር ወልድ"God the Son" ማለት ነው።

"ሞኖጌኔስ" μονογενὴς የሚለው ቃል "ሞኖስ" μόνος እና "ጌኑስ" γένος ከሚል ሁለት ቃላት ውቅር ነው፥ "ሞኖስ" μόνος ማለት "ብቸኛ" ማለት ሲሆን "ጌኑስ" γένος ማለት ደግሞ "የተወለደ" ማለት ነው። ኮዴክስ አሌክሳንድሪነስ ኢየሱስን "ሞኖጌኔስ ሁዮስ" μονογενὴς υἱός ይለዋል፦
ዮሐንስ 1፥18 መቼም ቢሆን አምላክን ያየው አንድ ስንኳ የለም፥ በአባቱ እቅፍ ያለ ብቸኛ የተወለደ "ልጅ" ተረከው። Θεὸν οὐδεὶς ἑώρακεν πώποτε· μονογενὴς υἱός ὁ ὢν εἰς τὸν κόλπον τοῦ Πατρὸς, ἐκεῖνος ἐξηγήσατο.

"ሁዮስ" υἱός ማለት "ልጅ" ማለት ሲሆን "ሞኖ ጌኔስ ሁዮስ" μονογενὴς υἱός ማለት "ብቸኛ የተወለደ ልጅ"the only begotten son" ማለት ነው። ኮዴክስ ቫቲካነስን ደግሞ ኢየሱስን "ሞኖጌኔስ ቴዎስ" μονογενὴς υἱός ይለዋል፦
ዮሐንስ 1፥18 መቼም ቢሆን አምላክን ያየው አንድ ስንኳ የለም፥ በአባቱ እቅፍ ያለ ብቸኛ የተወለደ "አምላክ" ተረከው። Θεὸν οὐδεὶς ἑώρακεν πώποτε· μονογενὴς Θεὸς ὁ ὢν εἰς τὸν κόλπον τοῦ Πατρὸς, ἐκεῖνος ἐξηγήσατο.

"ቴዎስ" Θεὸς ማለት "አምላክ" ማለት ሲሆን "ሞኖ ጌኔስ ቴዎስ" μονογενὴς Θεὸς ማለት "ብቸኛ የተወለደ አምላክ"the only begotten God" ማለት ነው። "አንዱ አምላክ ሌላ እና ሁለተኛ አምላክ ወለደ" ማለትስ ጤነኛ ትምህርት ነውን? አምላክ አምላክን ከወለደ ያልተወለደ አምላክ እና የተወለደ አምላክ ካለ ስንት አምላክ አለ? በእርግጥ የእነርሱ እምነት "ያልተወለደ እግዚአብሔር" እና "የተወለደ እግዚአብሔር" የሚል ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 25 ቁጥር 2
"ወንድሞቻችን እኛስ እንዲህ እናምናለን፤ "ያልተወለደ እግዚአብሔር" አብ በተለየ አካሉ አንድ ነው፥ "የተወለደ እግዚአብሔር" ወልድ ዋሕድ ኢየሱስ ክርስቶስም በተለየ አካሉ አንድ ነው።

በ381 ድኅረ ልደት በንጉሥ ቀዳማይ ቴዎዶስዮስ ሊቀ መንበርነት የተጠራው የቆስጠንጢኒያ ጉባኤ የማታ ማታ መንፈስ ቅዱስን "ሆ ቴዎስ ሆ ኑማ ቶ ሐጊዎን" Ο Θεός ο Πνεῦμα τὸ Ἅγιον ብሎታል፥ "ሆ ቴዎስ ሆ ኑማ ቶ ሐጊዎን" Ο Θεός ο Πνεῦμα τὸ Ἅγιον ማለት "እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ"God the Holy Spirit" ማለት ነው። እንደ ሥላሴአውያን አስተምህሮት መንፈስ ቅዱስ የሚባለው አምላክ ያልወለደ እና ያልተወለደ ነው፥ ይህ አምላክ በባሕርይ ግብሩ አይወልድም አይወለድም።
እኛ ሙሥሊሞች፦ "አሏህ አልወለደም፤ አልተወለደምም" ስንል እርር እና ምርር ብለው የሚያጨረጭራቸው እና የሚያንተከትካቸው በክርስትና ያልወለደ እና ያልተወለደ አምላክ መኖሩን ሲያውቁ ምን ይውጣቸው ይሆን? በእርግጥም እውነተኛው አምላክ አሏህ አልወለደም፤ አልተወለደምም፦
112፥3 አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ

ያልተወለደ አምላክ አብ፣ የተወለደ አምላክ ኢየሱስ፣ ያልወለደ እና ያልተወለደ አምላክ መንፈስ ቅዱስ ከሚል እሹሩሩ እና እሽኮለሌ ውዝግብ ወጥታችሁ አንዱን እና እውነተኛውን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። የኢየሱስ አምላክ አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
ጥሪያችን Tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም

Address

Ethiopia , Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when 𝙨𝙪𝙛𝙞𝙮𝙖𝙣 𝙟𝙚𝙢𝙞𝙡 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to 𝙨𝙪𝙛𝙞𝙮𝙖𝙣 𝙟𝙚𝙢𝙞𝙡:

Shortcuts

Share

Category