26/12/2020
sheikh hussein jibril prophecy
Most of his poems were predictions about the
upcoming rulers of Ethiopia and sociopolitical
situations of the country starting from the times of
Zemene Mesfaent ( Era of the Princes, of 1769) to
the present regime. For one who
knows Ethiopian history well, the prophetic poems hit a
100% right. The poems are colloquial in writing and
double-edged in meaning so they need to be read
between the lines and with a deep knowledge of the
Amharic language, Ethiopian history and religions . For
eg, he terms Christianity as Amara instead of calling
it Christianity and similar kinds of usages.
If anyone can please post a copy of their intact
"branna" scripture please share it or post a link in the
comments because ከዚህ በታች የቀረቡት ግጥሞች የተገኙት
በእጅ ተጽፎ ፎቶ ኮፒ ከተደረገ አንድ አነስተኛ
ደብተር ላይ ነው :: so may not have the parts about our
current regime. i know many verses are left.
1. ዋርዳው መጣና ቆይ አለኝ አንድ ዓመት
ጫትክን እየበላህ ሳታድር ከሴት
አምሬን እየሞላህ ጠጅን ሳታሸት
ደረሳህን ይዘህ ሳትወጣ ከቤት
እኔም ኸልዋ ገባሁ ቆየሁ አንድ ዓመት::
2. አንድ ዓመት ጫት ቅመን ዓለሙን ስንድር
ንጉሥ እየፈራኝ ሳይጠላኝ አሽከር
ወዲያው ስሜ ታውቆ ሸዋና ሐረር
እኔም በመስታወት ዓይኔን ሳሳምር
ቃሌ ሳይዛነፍ ሳልደናገር::
3. አላህ ሲያሳምረው ሰው እጣው ሲወጣ
ዓመት አስቀመጠኝ ከኸለዋ ሳልወጣ
ወዲያው መናም አየሁ አንበሳ ሲወጣ
ነብር እየመራኝ ጅብ ከፊቴ መጣ
ግመል ተሸክሞኝ የሆነ መላጣ::
4. መናቡ አይቼ ለሰው ሳላወራ
በሰባተኛው ቀን መጣ አንድ ቀብራራ
መሰንቆና ዋሽንት በእጁ ይዞ ጭራ
ከኔ ጋራ አደረ ጫት ሲቅም ሲያወራ
መሰንቆ እየመታ ሲዘፍን ሲያቅራራ::
5. አላህ ሲያሳድገው ነገሩ ሲሰላ
በስምንተኛው ቀን ጫት ስንቅም ስንበላ
ድቤ ተሸክሞ መጣ አንድ ሻንቅላ
ጫት በጨርቅ ይዞ ጠጅ በሸክላ
ሁሴን ቡን አፍላልኝ ነገሩ እንዲሰላ::
6. ስምንት ቀን ከደምኩ ሳትናገር አፌ
የቤቴን ግድግዳ ግንዱን ተደግፌ
ፊቴን እያጠብኩኝ እንዳይመጣ እንቅልፌ
እንዲቀመጡበት ጋቢዬን አንጥፌ
አይገርማችሁም ወይ ሳልነግድ ማትረፌ::
5
7. መናውን ፈሰርነው አንተ ሳትናገር
ድቤውም ዋሽንቱም መሰንቆው ጭራ አይቀር
ጠጅና ጉማሬ ጫት ስንቅም እንደምር
ጀባ ብለንሃል በዟሂር መነጸር
ሐሲድ የሚመታ አንድ እንኩዋን ሹም ሳይቀር::
8. አላህ ካደረገን የኸልቁ ወዳጅ
በድቤና በጫት ልጀምር በጠጅ::
መሰንቆ እየመታሁ ልወዝወዘው እንጅ
በጭራ በዋሽንት ሰው ባልነካው እጅ
አውሊያ እምጠራበት ሶላት ሳልሰለች::
9. ጫት ባፋችን ይዘን ጠጅ እየጠጣን
ጥቁር ጭራ ይዘን ድቤ እየመታን
ሐሲድ እንዳይነካን አውሊያ እየጠራን
አምስት አውቃት ሶላት እየሰጋገድን
ሰው ያልነካው እቃ ጀሊሉ ሰጠን::
10. መጪውን አየነው ጉድ አጃኢበት
ዓለም ስትስቅብኝ እኔ ሳቅኩባት
ለአዳም መህሉቃት ከወንድም ከሴት
ካለቁት በስተቀር ያሉት በሐያት
ተከትቦ አየዋለሁ ስሙን ወደፊት::
11. ስሙን ይነግረኛል ዋሪዳው ሳይስት
ገና በእናቱ ሆድ ሳኸለቅ ፊት
ለወልይ ለንጉሥ፣ ለራስ መሳፍንት
ምን አስለፈለፈኝ ሊታይ ወደፊት
እኔም በል ብሎኝ ነው የምወሸክት::
12. ሃምሳ ዓመት ስናገር ሰምተው ጉድ እያሉ
እንደ ፍልፈል አፈር ሰው ሲፈለፍሉ
(ሰምተው እንዳልሰሙ አላየንም አሉ
እንደ ፍልፈል አፈር ሰው ሲፈለፍሉ)
እኛም ሰደድናቸው ከአፈር እንዲተሉ
ቀሩ እንደፈራነው ውሸታም እንዳይሉ::
13. ሃምሳ ዓመት ከደመኝ መሐመድ ኑር ዒሳ
መድና ወረቀት ከእጁ ሳይነሣ
ይከትበው ነበረ ዋሪዳው ሲነሣ
የፈረድኩትን አንድ ቀን ሳይረሳ
መጪውን ፈርጃለሁ ዓለም እስቲከሳ::
14. ቃሊቾችም ጠሉኝ ጠጅ ይጠጣል ብለው
ደብተራውም ጠላኝ ሹም ተጠጋው ብሎ
ባለዛሩም ጠላኝ ሰው ሄደበት ብሎ
ፋቅራውም ተጠጋኝ ምን ይፈርዳል ብሎ
እኒህን ችዬ ነው የሰጠኝ ጀሊሉ::
6
15. ጀግና አጼ ዮሐንስ ያበሶች ወንድም
የዛሬን ማርልኝ ያለ ዛሬ አይለምድም
በነገረ ሠሪ ሰው አይታረድም
እንዲህ ከሆነማ አንድ ስው አይተርፍም
እየደነገጡ ይሄዳሉ የትም::
16. ዓባይ በጣና ላይ መሄዱ ለምን ነው?
ትንሹ ሲያጠፋ ትልቁ ሊችል ነው፣
ቢያከፋም ቢያበጅም ዓባይ ማለፋ ነው
ሰውን በግዴታ የሚገዛው ማነው?
ከምክር በስተቀር የቀረው ከንቱ ነው::
17. ማረዱ ከፋ እንጅ ጀግንነት አያጣም
እስላም እሚያርድ እንጅ እሚወድ አይመጣም፣
የፈራህ ሰው ወጣ እኔ መልስ አላጣም
ይዘገያል እንጅ ሰው የጁን አያጣም
መተማ ከሄደ ተመልሶ አይመጣም::
18. አንተም እድሜህ አጭር ወይ ዘርህ አይገዛ
(ጎርፍ ደርሶ አይወስድም አለቅጥ ካልበዛ)
እንጨት ከደረቀ ቢቀቡት አይወዛ
(ሐበሻ ክፉ ነው አይምሰልህ ዋዛ)
መተማ እስቲጠራህ በብልሃት ግዛ::
19. እመክርህ ነበረ መች እሺ ትላለህ
ሀሳብህ ብዙ ነው መንገድ ታበዛለህ
መተማ ለመዝመት አሁን ትሄዳለህ
(መመልስክን እንጃ እዛው ትቀራለህ)
በድርቡሽ ጎራዴ ራስህን ታጣለህ::
20. አንድ ዓመት ሲቀረው ምኒልክ ሊነግሥ
አላህ መተማ ላይ ይስላል መቀስ
በደም አጨማልቃ የምትቆራርስ
እራስ የምትቆርጥ ያውም የንጉሥ
አንደዜ ተመታች የማታላውስ::
21. አራት ወር ሲቀረው ምኒልክ ሊነግሥ
በመተማ በኩል ትጨሳች ጭስ
ጭሷ በራስ ገብታ (የምታስነጥስ) ትጨርሳለች ጭስ
እጅግም አትበጀው ለአጼ ዮሐንስ
አላህ ሽቶበታል አንገቱን ሊቀምስ::
22. እውቀትም የላቸው አሉን ጥንብ እርኩስ
ብለው ሰደቡን ደብተራና ቄስ
ሄጄ ልናገረው ለአጼ ዮሐንስ
ፈርጀለት ነበር መቅደላ ሲፈርስ
እንዴት የነቢ አሽከር ይሆናል እርኩስ?
7
23. የሰማም ያልሰማም ያልቅስ
መች እኔ እፈራለሁ ደብተራና ቄስ
መተማን ድል አድርጎ እሱ ቢመለስ
እንግዲህ የኔ ጫት ጥንብ ናት እርኩስ?
መተማ ካልሄደ እኔም ጫት አልቀምስ::
24. ጦሩን አስከትሎ መተማ ሲደርስ
ከበቅሎው ወረደ አጼ ዮሐንስ
የጦሩን መከታ ጋሻውን ሊለብስ
እሱ እራሱን አጥቶ ሰውን ሊያስጨርስ
በጥረት አይድንም ጥፋ ያለው ነፍስ::
25. እንዴት በገዛ እጁ ሞት ይመኛል ሰው?
መተማ አትሂድ ብዬ ብመክረው
መቸ ይመለሳል ያዘዘበት ሰው
(ደም እየሸተተው ሞት እየጠራው
እንዴት ሰው ለአንገቱ አያዝንም ወይ ሰው)
26. ፈረሱን ጫጭነው ድርቡሾች ዘለቁ
ኸሊፋና ዑመር ድባጢን ዘለቁ
ከዚያም ከዚህ ያሉት ተደበላለቁ
ዮሐንስ ከጭፍራው ፈርተው ተጨነቁ
የሚያስታርቅ ጠፍቶ ስንት ሰው አለቁ::
27. የአህያ ልጅ በቅሎ በብር ተሸልማ
ዮሐንስን ይዛ ወረደች መተማ
ከጌታዋ ራስ ጋር በቁም ልትቀማ
ስንቱን ሰው ፈረጀው ደጉ አገር መተማ
ስንቱን አርዶት ነበር እስላም እንዳይለማ::
28. ምኒልክ ደስ አለው ምጡን ሲፈረጅ
እኔም ጫት በመቃም ነጀ ወጣሁ እንጅ
እስላምን የሚወድ ወደፊት ይምጣ እንጅ
ዮሐንስ ክፉ ነው የለውም ወዳጅ
መተማ ደጉ አገር ገላገለን እንጅ::
አላህ ገላገለን በዟሂር መከራ
እንግዲህ ምኒልክ አይዞህ እንዳትፈራ
ዮሐንስ ሊሄድ ነው ጦሩን እየመራ
ማረድ የለመደ መቼም ሞት አይፈራ::
ሞቱ ብላሽ ሆነ እንዲህ ሲንጠራራ::
29. አንተም ጨካኝ ነበርክ ጨካኝ ወረደብህ
እንደ ፍሪዳ ላም በቁምህ አረዱህ
በቅሎና ገጧ ጋር በቁሟ ማረኩህ
እራስክን ቋንጣ አርገው ሥዕል አደረጉህ
አላፊው አግዳሚው እንዲሰደድብህ::
8
30. አልሐምዱሊላሂ ለዚህ አበቃህ
ዮሐንስ እራስህን በችንካር መቱህ
አላፊው አግዳሚው እስቲተፋብህ
ሰው የጁን አያጣም እንዲህ አረጉህ
የወሎን መሻኢህ እያረድክ ሰቅለህ::
31. አጠቋቆራቸው ከሰል ይመስላሉ
ከመሕሉቁ ብሰው በጣም ይጠቁራሉ
መተማን ድል አርገው ጎንደር ይገባሉ
ደቆራና ዳይንት ብዙ ሰው ያርዳሉ
ከሺህ ታቦት በላይ በእሳት ያነዳሉ::
32. ማረድ ተጀምሮ ድራና ፎገራ
ምን ይበጀው ይሆን የጎንደር አማራ?
አይተኸው የማታውቅ መጣብህ መከራ
ብዙ ሰው ይጠፋል ካልሰለመ አማራ
ይለበልበዋል ያርደዋል በካራ::
33. ወደ ሱዳን አገር ዋሪዳው ካመራ
ደፈረኝ ካልሉ ሳዳቶችን ልጥራ
አሁን ድረሱልኝ ይዞኛል ደብተራ
ወትሮም የመሐዲ ዘር አስላችሁ አይኮራ
ገላገላችሁኝ አልቅሼ ብጣራ::
34. ቢደፍሯቸው እዳ ዝም ብል ችግር
ዋሪዳው መጣና አለኝ ተናገር፣
እንግሊዝ ከሱዳን ካልለቀቀ አገር
ይዘገያል እንጅ ኋላ አለ ነገር
መሕዲ ዘር ባለቃ ሲል ደንገር ደንገር::
ሱዳን ብሎ ማለት ተፍሲሩ ሻንቅላ
(ከነሱ ካልሆነ አይጋቡም ሌላ
መጠጥ ይወዳሉ ሐራራም አይጠላ)
ዘራቸው ልዩ ነው ናቸው የአላህ ሰባት በላ
ሰባት ቋንቋ አላቸው ሁሉም በጠቅላላ::
35. የሱዳንን ነገር በስንቱ ላውሳቸው
ካላስፈነደዱ ፈርጅም አይመስላቸው
ከእኛም ሰው አይተፋ ነጭ ያስተማራቸው
የወንዱስ መላ አልቋል ሴቱ አላህ ያብጀው
ስንቡል እያጠበች ገልባ ከሰጠችው::
36. ድርቡሽና ሱዳን መልካቸው ጥቁር ነው
አገሩ አንድ ቢሆን ቋንቋው እየቅል ነው
ጥንቱም ፍጥረታቸው ዘራቸው ልዩ ነው
በዟሂር ሲጠሩ ስማቸው እስላም ነው
ቸርነት አያጡም እጃቸው ለጋስ ነው::
37. ድርቡሽ ጥሩ እስላም ልባቸው የጠራ