Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ

Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ, Government Organization, �, Addis Ababa.

ኮሚሽኑ በማኅበራዊ ሚዲያ አሳሳች መረጃዎች እንዳይሠራጩ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳሰበ++++++++++++++++   የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የውይይቱ የመጀመሪያ ደረጃዎች ስሜት የተሞላባ...
24/07/2026

ኮሚሽኑ በማኅበራዊ ሚዲያ አሳሳች መረጃዎች እንዳይሠራጩ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳሰበ
++++++++++++++++

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የውይይቱ የመጀመሪያ ደረጃዎች ስሜት የተሞላባቸው ሊሆኑ ስለሚችሉ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ አሳሳች መረጃዎች እንዳይሠራጩ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳሰበ።

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር (ፕ/ር) መስፍን አርዓያ የምክክሩን ሂደት አስመልክቶ ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳሉት፤ ተሳታፊዎች በውይይቱ ያለ ምንም ፍራቻና ገደብ ስሜታቸውን ሲገልጹ ነው ሂደቱ አካታች የሚሆነው።

ያልተባሉና ያልተሄደባቸው ጉዳዮች በስሜት እንዳይወጡ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ የገለጹት ዋና ኮሚሽነሩ፤ ለዚህም ተሳታፊዎቹ ስልክ ይዘው እንደማይገቡ ገልጸዋል። ይህ ውሳኔ ተሳታፊዎቹም ተስማምተውበት እንደተደረገ አስረድተዋል።

#ፕሬስመረጃማጣሪያ #ሀገራዊምክክር

ጄኤ ፍኤም 106.7 ሬድዮ ሞገድ ለስድስት ወራት ታግዷል++++++++++   -ለጄኤፍኤም 106.7 በፈቃድ ውሉ የተዘረዘሩ ግዴታዎች ሙሉ ለሙሉ ተሟልተዉ ተግባራዊ እስኪደረጉ ድረስ የሬድዮ ጣቢ...
22/07/2026

ጄኤ ፍኤም 106.7 ሬድዮ ሞገድ ለስድስት ወራት ታግዷል
++++++++++

-ለጄኤፍኤም 106.7 በፈቃድ ውሉ የተዘረዘሩ ግዴታዎች ሙሉ ለሙሉ ተሟልተዉ ተግባራዊ እስኪደረጉ ድረስ የሬድዮ ጣቢያዉ ለቀጣይ 6 ወራት ከስርጭት ሙሉ ለሙሉ ታግዶ እንዲቆይ ተወስኗል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 በተሰጠዉ ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት መገናኛ ብዙሃን ተግባራቶቻቸውን በሕግ መሰረት ማከናወናቸውን ማረጋገጥ፣ ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ፣ የመገናኛ ብዙሃን የእርስ በእርስ ቁጥጥርና ግምገማ እንዲጠናከር ተገቢውን ድጋፍ መስጠት፤ ለብሮድካስት አገልግሎት ፈቃድ መስጠት፣ የአገልግሎቱ ተጠቃሚነት፣ ባለቤትነት፣ ዝግጅትና ሥርጭት ላይ ብዝሃነት እንዲጠበቅና እንዲስፋፋ መሥራት፤ ማደስ፤ማገድ እና መሰረዝ ይገኝበታል፡፡

በዚህም መሰረት ጄኤፍኤም 106.7 አስመልክቶ ባለስልጣኑ ባደረገዉ የይዘት ክትትልና በአካል ተገኝቶ ባከናወነዉ የኢንስፔክሽን ምልከታ የሚከተሉ ግኝቶችን ለይቷል፡-

✍️ በአንቀጽ 64/4/ ሀገራዊ ይዘቶችን የማካተት ግዴታ ከሳምንታዊ የስርጭት ጊዜው 60 በመቶውን ፈቃድ ለወሰደበት አካባቢ የሚመለከት ሲሆን ቀሪውን ጊዜ ለሀገራዊ፣ ክልላዊና ሌሎች ፕሮግራሞች ማዋል እንደሚገባ ቢደነግግም ይህንኑ ተግባራዊ ያለማድረግ፣

✍️አንቀፅ 55/1/ - ህዝብን የሚያስተምር፣ የሚያሳውቅና የሚያዝናና ፕሮግራሞችን አለማቅረብ፣

✍️ ለፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት እንዲሁም በህገ መንግስቱና በሌሎች የሕዝብ ጥቅምና የጋራ ሀገራዊ እሴቶች እንዲጠናከሩ አስተዋፅኦ የሚያደርግ የብሮድካስት አገልግሎት የመስጠት ግዴታን አለማክበር፣

✍️ አንቀፅ 56/6/ መሰረት ሀገራዊ ይዘት ያላቸው ፕሮግራሞችን የማቅረብ ግዴታ አለመወጣቱ፣

✍️ በፈቃድ የዉል ስምምነት መሰረት ያለመስራት የሚሉ ዋና ዋና ክፍተቶች በመስተዋላቸዉ በተደጋጋሚ ግብረ መልስ፣ የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያዎች ቢሰጡትም መሻሻሎች ሊታዩ አልቻሉም፡፡

በመሆኑም በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 መሰረት ለጄኤፍኤም 106.7 በፈቃድ ዉሉ የተዘረዘሩ ግዴታዎች ሙሉ ለሙሉ ተሟልተዉ ተግባረዊ እስኪደረጉ ድረስ የሬድዮ ጣቢያዉ ከረቡዕ ሐምሌ 01/2018 በጀት ዓመት ጀምሮ ታሳቢ የሚደረግ ለቀጣይ 6 ወራት ከስርጭት ሙሉ ለሙሉ ታግዶ እንዲቆይ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በኩል የተወሰነና በኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ለጄኤፍኤም የተመደበው 106.7 የሬድዮ ሞገድ እግድ ፀንቶ እስከሚቆይበት ጊዜ ድረስ ፍሪኩዌንሲውን ጥቅም ላይ ማዋል እንደማይቻል ለጣቢያው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡

ስለሆነም የሬድዮ ጣቢያው ይህን ውሳኔ በማክበር እና ለህግ ተገዢ በመሆን ስርጭቱን እንዲያቆም እያሳሰብን፤ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በዚሁ ውሳኔ አግባብ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እናሳዉቃለን፡፡

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን
ሐምሌ 15 2018 አ.ም

ለመላው ኢትዮጵያዊያን የተላለፈ መልዕክት+++++++++  - በሀገራችን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከናወነ ያለውና ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች...
19/07/2026

ለመላው ኢትዮጵያዊያን የተላለፈ መልዕክት
+++++++++

- በሀገራችን ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከናወነ ያለውና ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሀገራዊ ፋይዳ ባላቸው እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ የሚመካከሩበት ታሪካዊ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ እንዲሳካ ዜጎች ራሳቸውን ከሀሰተኛ መረጃ በመጠበቅ እና በኮሚሽኑ ላይ ሙሉ እምነት በማሳደር ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሪ ያቀርባል፡፡

ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረውን ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በተመለከተ አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች በማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች አማካኝነት ከእውነታ የራቁ መረጃዎችን እያሰራጩ መሆኑን ኮሚሽኑ ደርሶበታል፡፡

ኮሚሽኑ የመናገር ነጻነትን ሙሉ በሙሉ የሚያከብር ገለልተኛ ተቋም እንደመሆኑ ገንቢ የሆኑ ሃሳቦችንና ውይይቶችን የሚቀበል ቢሆንም ሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ በሀሰተኛ መረጃዎች እንዳይታለል አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ ለህዝብ ይፋ ለማድረግ ይገደዳል፡፡

ሀገራዊ ምክክሩ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ነው። የዚህ ሂደት ስኬት የሚወሰነው ዜጎች በትዕግስት፣ በጥበብ እና በጋራ የኃላፊነት ስሜት ለመሳተፍ በሚያሳዩት የጋራ ቁርጠኝነት ላይ ነው። ይህም እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ሂደቱ ተጀመረ እንጂ ውጤቱ ገና ነው፡፡ ይህንን ውጤት በትዕግስት መጠበቅ ደግሞ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚጠበቅ ይሆናል፡፡

ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የተጀመረው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ኮሚሽኑ ባወጣቸው የአሰራር ሂደቶች መሰረት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በዚህ መሰረት ባለፉት አራት ቀናት ኮሚሽኑ የጉባኤው ተሳታፊዎች የተጣለባቸውን ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ እርስ በእርስ እንዲተዋወቁ ማድረግን ጨምሮ ለሂደቱ ጠቃሚ በሆኑ የእውቀት እና የስነ-ልቦና ዝግጅቶች እንዲያደርጉ መደላድሉን ፈጥሯል፤ ይህም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው አንድ አካል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡

ይህ እየሆነ ባለበት አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ኮሚሽኑ ምክክሩን ለመጀመር እክል እንደገጠመው የተሳሳተ መረጃ ሲያሰራጩ ተመልክተናል፡፡

በመሆኑም መሰል የተሳሳቱ መረጃዎች የራሳቸው ዓላማ ባላቸው ግለሰቦችና ቡድኖች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ስለሚችሉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በየእለቱ የሚኖሩ የምክክር ሂደቶችን ኮሚሽኑ ከሚሰጣቸው መግለጫዎችና የምክክሩን ሂደት ለመዘገብ በስፍራው ከተገኙ መገናኛ ብዙኃን ብቻ በመከታተል ራሱን ከተሳሳቱ መረጃዎች በመጠበቅ የምክክሩን ሂደት እንዲደግፍ ኮሚሽኑ ጥሪ ያቀርባል፡፡

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም

የማስተርስ ትምህርት የቆይታ ጊዜ የመራዘም ጉዳይ+++++++++++   | የማስተርስ ዲግሪ ትምህርት የሚሰጥበት የጊዜ ርዝማኔ ወደ አራት ዓመት ተራዝሟል የሚሉ መረጃዎች በማኅበራዊ ሚዲያዎች ሲ...
11/07/2026

የማስተርስ ትምህርት የቆይታ ጊዜ የመራዘም ጉዳይ
+++++++++++

| የማስተርስ ዲግሪ ትምህርት የሚሰጥበት የጊዜ ርዝማኔ ወደ አራት ዓመት ተራዝሟል የሚሉ መረጃዎች በማኅበራዊ ሚዲያዎች ሲሰራጩ ተስተውለዋል።

መረጃዎቹ ከሰሞኑ የተካሄደውን የኢፌዴሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ዋቢ አድርገው ሲጠቅሱ ነበር።

ባለስልጣኑ በሰጠው ማብራሪያ የ11 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማቅረቡንና የአረዳድ ችግር መፈጸሙን ጠቅሷል፡፡

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሰኞ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት የ11 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረበ መሆኑን ጠቅሶ፤ ከኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ጋር የተያያዙ ሃሳቦች ተነሰተው እንደነበር አብራርቷል።

እነዚህን የተነሱ ሃሳቦች በስህተት በመረዳት “የማስተርስ ትምህርት ወደ 4 ዓመት ሊያድግ ይገባል” በሚል ርዕስ በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ሀሰተኛ መረጃ ተሰራጭቷል ብሏል፡፡

የማስተርስ ትምህርትን የቆይታ ጊዜ በሚመለከት እየወጡ ያሉ መረጃዎች የተዛቡ መሆናቸውንም ዕወቁልኝ ብሏል።

ባለስለጣኑ ጨምሮም ሲዘዋወር የዋለው መረጃ የአረዳድ ችግር እንጂ ምንም ዓይነት ህጋዊ መሠረት እንደሌለው ገልፆ፤ የሁለተኛ ዲግሪ (Master Degree) ትምህርትን በተመለከተ ምንም የተቀየረ ደንብ የለም ሲል አፅንኦት ሰጥቷል፡፡

ለተጨማሪ መረጃም ከዚህ በታች የሚገኘውን “የኢትዮጵያ የትምህርትና ሥልጠና የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ ደንብ ቁጥር 561/2016” እንድትመለከቱ ሲልም አክሏል፡፡

በጋዜጣ ፕላስ መረጃ ማጥሪያ
#ትምህርት

ደመወዝ ማሻሻያ ከመስከረም 1 ይጀምራል የሚለው ደብዳቤና የገንዘብ ሚኒስቴር ምላሽ+++++++++++++   | ከሰሞኑ የሰራተኞች የኑሮ ውድነት ጫና ማስታገሻ የደመወዝ ማሻሻያ ጥናት የሚል ደብ...
08/07/2026

ደመወዝ ማሻሻያ ከመስከረም 1 ይጀምራል የሚለው ደብዳቤና የገንዘብ ሚኒስቴር ምላሽ
+++++++++++++

| ከሰሞኑ የሰራተኞች የኑሮ ውድነት ጫና ማስታገሻ የደመወዝ ማሻሻያ ጥናት የሚል ደብዳቤ የገንዘብ ሚኒስቴር እንደጻፈው ተደርጎ በማኅበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር ታይቷል።

ፕሬስ_መረጃ_ማጣሪያ ጉዳዩን አስመልክቶ ባደረገው ማጣራት በማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ ከገንዘብ ሚኒስቴር እንደወጣ ተደርጎ የሚሰራጨውና የደመወዝ ጭማሪ ጥናትን የሚመለከተው ደብዳቤ ሙሉ በሙሉ ሀሰተኛ መሆኑን ደርሶበታል።

ደብዳቤው “በቅርቡ ትግበራው የተጀመረውን የሀገራችንን የተሟላ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ተከትሎ የመንግስት ሰራተኞች በተለይም ዝቅተኛ የደመወዝ ተከፋይ ሰራተኞች በኑሮ ውድነት እንዳይጎዱ እና ሊደርስ የሚችለውን የኑሮ ጫና በመጠኑም ቢሆን ለመቋቋም እንዲችሉ ከመንግስት በተሰጠ አቅጣጫ መሰረት የሰራተኞች የኑሮ ውድነት ጫና ማስታገሻ የደመወዝ ማሻሻያ ጥናት መካሄዱን ያነሳል።

አክሎም ለደመወዝ ጭማሪው የሚያስፈልገው ተጨማሪ የወጪ በጀት ከመጠባበቂያው ብር 91,439,368,014 /ዘጠኝ አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ሚሊዮን ሶስት መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ከእንድራ አራት ብር/ ሲሆን የደመወዝ ማሻሻያ የተደረገላቸው አካላትን ዝርዝርም ለይቶ ያስቀምጣል።

የደመወዝ ጭማሪው ከመስከረም 1 ቀን 2019 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ እንዲደረግ ውሳኔ የቀረበ ሲሆን ዝርዝር ትግበራውን የገንዘብ ሚኒስቴር እና የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በጋራ የሚያስፈጽሙት ይሆናል” በሚል ያትታል።

ሆኖም የገንዘብ ሚኒስቴር ይህን ደብዳቤ አላውቀውም፤ ከእኔም የወጣ ዓይደለም ብሏል። ሕዝብን ለማደናገር ሀሰተኛ ሰነድ ተዘጋጅቶ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ የቀረበው ደብዳቤ ፊጹም ሀሰት መሆኑንና ህብረተሰቡ ሊያምነው እንደማይገባም ገልጿል።

ይልቁንም ከገንዘብ ሚኒስቴር የሚወጡ ትክክለኛ መረጃዎችን ለመከታተል በሜታ ኩባንያ የተረጋገጠውን (Verified) ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ እና ተአማኒነት ያላቸውን የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎችን ብቻ መጠቀም እንደሚገባ አሳስቧል።

በጋዜጣ ፕላስ መረጃ ማጥሪያ
#ደመወዝ

በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚለቀቁ የሕክምና መሣሪያ ማስታወቂያዎች ሕጋዊ ፈቃድ እንደሌላቸው የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ+++++++++++++  |  ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚ...
03/07/2026

በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚለቀቁ የሕክምና መሣሪያ ማስታወቂያዎች ሕጋዊ ፈቃድ እንደሌላቸው የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ
+++++++++++++

| ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚለቀቁ የሕክምና መሣሪያ ማስታወቂያዎች ሕጋዊ ፈቃድ ሲለሌላቸው ማስታወቅያዉን በፊጥነት እንዲያነሱ የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ።

በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ የተለያዩ የሕክምና መሣሪያዎችን የሚያስተዋውቁና ጥቅማቸውን የሚገልጹ ይዘቶች በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ። እነዚህ ማስታወቂያዎች ከሚመለከተው የመንግስት አካል የእውቅና ፈቃድ የሌላቸው መሆኑን የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) አስታዉቋል።

ባለሥልጣኑ ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ዋና ዋና የብዙኃን መገናኛዎችንና እንደ ቲክቶክ (TikTok)፣ ዩቲዩብ (YouTube)፣ ፌስቡክ (Facebook) እና ሌሎችንም የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮችን ጨምሮ ከማንኛውም ዓይነት የማስታወቂያ ማሰራጫ መንገዶች ላይ የሕክምና መሣሪያ ማስታወቂያዎችን እንዲያነሱ አሳስቧል።

አንዳንድ የሕክምና መሳሪያዎች ለሕዝብ በማስታወቂያ መልክ እንዳይቀርቡ በሕግ የተከለከሉ ናቸው ያለው ባለስልጣኑ፣ ማሳሰቢያውን በመጣስ ያለሕጋዊ ፍቃድ የሕክምና መሳሪያዎችን ማስተዋወቅ በሚቀጥሉ አካላት ላይ ሕጋዊ ርምጃ እንደሚወስድም አስትውቋል።

ዕውን ወደ ካናዳ የሥራ ስምሪት ተጀምሯል?+++++++++++++   | ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከሰሞኑ "ወደ ካናዳ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ጀምሯል" በማለት የተሳሳተ መረጃ እየተሰጠ ነው ብሏል። ...
17/06/2026

ዕውን ወደ ካናዳ የሥራ ስምሪት ተጀምሯል?
+++++++++++++

| ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከሰሞኑ "ወደ ካናዳ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ጀምሯል" በማለት የተሳሳተ መረጃ እየተሰጠ ነው ብሏል።

ይህም ብቻ ዓይደለም "ወደ ካናዳ እንልክዎታለን" በማለት ከፍተኛ ገንዘብ ከሚጠይቁ "ከሚኒስቴሩ ህጋዊ ውክልና ተሰጥቶናል" የሚሉ እንዳሉ አስረድቷል።

ወደ ካናዳ ምዝገባም ሆነ ስምሪት አልተጀመረም ያለው መሥሪያ ቤቱ፤ ይህን መሰል መረጃ ከሚሰጡ አጭበርባሪዎች ራሳችሁን ጠብቁ ሲልም አስጠንቅቋል።

ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ እንዳስታወቀው በአሁኑ ወቅት ዜጎች በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (lmis.gov.et) ላይ በመመዝገብና ህጋዊ ሂደቶችን በመከተል፣ ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ስምምነት ወደ ተፈራረመችባቸው ሀገራት የሥራ ስምሪት እየወሰዱ ነው።

ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ ጆርዳን፣ ኳታርና ሊባኖስ ዜጎች በህጋዊ መንገድ የሥራ ስምሪት እየወሰዱባቸው የሚገኙ ሀገራት መሆናቸውንም ሚኒስቴሩ ጠቅሷል።

በአንጻሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል" (FUTURE FIT INTERNATIONAL INC.) ጋር ስምምነት የፈጸመው በዋነኛነት ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ነው ብሏል።

የተደረገው ስምምነት ከካናዳ ኮሌጆች ጋር በመተባበር ተማሪዎችን በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ በሚፈለጉ ክህሎቶች ማሰልጠን፤ ብቁ የሆኑ ተማሪዎች በካናዳ በሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የነፃ ትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማመቻቸት ላይ የሚያተኩር እንደሆነም አብራርቷል።

ሚኒስቴሩ ከፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ጋር የተደረገው ስምምነት ወደ ተግባር ሲገባ፤ ዝርዝር መረጃው በሚኒስቴሩ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና በብሔራዊ ሚዲያዎች ብቻ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

ለዚህ ፕሮግራም ተጠቃሚ ለመሆን ምንም ዓይነት ክፍያ መፈጸም እንደማይጠበቅ በመጠቆም፤ ክፍያ የሚጠይቁ አካላት ሁሉ አጭበርባሪዎች መሆናቸውን እወቁልኝ ብሏል።

አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን ሲመለከቱ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ (9138 በነፃ የስልክ መስመር ወይም [email protected]) እና በአቅራቢያዎ ለሚገኙ የህግ አስከባሪ አካላት ይጠቁሙም ነው ያለው።

በጋዜጣ ፕላስ መረጃ ማጥሪያ
+++++++++++++++++++++

ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመርን በተመለከተ ከንግድ ባንክ የተሰጠ መግለጫ +++++++++++++++++++++   የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት በዋና ዋና ከተሞች በሚገኙ የባ...
06/06/2026

ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመርን በተመለከተ ከንግድ ባንክ የተሰጠ መግለጫ
+++++++++++++++++++++

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት በዋና ዋና ከተሞች በሚገኙ የባንካችን ቅርንጫፎች የተከፈቱ የባንክ ሒሳቦች ባለቤቶች የሆኑ እና እስከ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ሳያጣምሩ የቀሩ ደንበኞች በቀጣይ እስኪያጣምሩ ሒሳባቸው በጊዜያዊነት እንዳይንቀሳቀስ መደረጉ ይታወቃል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መኖሪያቸውን ከኢትዮጵያ ውጭ ያደረጉ ደንበኞች የባንክ ሒሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማጣመር ሳያስፈልጋቸው በጊዜያዊነት በልዩ ሁኔታ መስተናገድ የሚችሉበትን አሠራር ዘርግቷል።

በዚህ መሠረት ከዚህ በፊት ሒሳብ በሚከፍቱበት ወቅት የመኖሪያ አድራሻቸው ከኢትዮጵያ ውጭ እንደሆነ በባንካችን የመረጃ ቋት የተመዘገበ ማስረጃ ያቀረቡ ደንበኞች ሒሳብ ያልታገደ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታውቋል።

በተለያየ ምክንያት ውጭ ሀገር እንደሚኖሩ በባንኩ የመረጃ ቋት ላይ ያላስመዘገቡ እና የባንክ ሒሳባቸው የታገደባቸው ደንበኞች ከዚህ በታች በተገለፀው አግባብ መስተናገድ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል፦

1. ከኢትዮጵያ ውጭ መኖራቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ለምሳሌ - የትምህርት ማስረጃ፣ የሕክምና ማስረጃ፣ የውጭ ሀገር መንጃ ፈቃድ፣ ከውጭ ሀገር የተሰጠ ውክልና፣ የመኖሪያ ፈቃድ (የሎው ካርድ)፣ የሥራ ፈቃድ ወይም ሀገር ውስጥ እያሉ የተሰጠ ውክልና ሆኖ ነገር ግን ውክልናው ላይ ውጭ ሀገር መኖራቸውን የሚገልጽ ሐሳብ ካለ በሕጋዊ መኪሎቻቸው አማካኝነት በማቅረብ እግዱን ማስለቀቅ ይችላሉ፤

2. ዲፕሎማቶች የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ መታወቂያቸውን በማሳየት ወይም ሒሳቡ የተከፈተው በዲፕሎማት መታወቂያ ከሆነ እግዱ ተነስቶላቸው ሒሳባቸውን ማንቀሳቀስ ይችላሉ፤

3. ደንበኛው በውጭ ሀገር እንደሚኖር የሚያረጋግጥ የኢሜይል መልእክት በኢምባሲ/ቆንስላ በኩል ከመጣ እግዱ በጊዜያዊነት ተነስቶላቸው መሰተናገድ ይችላሉ፤

4. ደንበኞች በውጭ ሀገር መኖራቸውን ሊያስረዱ የሚችሉ ማስረጃዎችን በቀጥታ የባንክ ሒሳቡ በተከፈተበት ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ የኢ-ሜል አድራሻ ወይም በዲያስፖራ ባንኪንግ ክፍል የኢ-ሜል አድራሻ [email protected] በመላክ እግዱን በጊዜያዊነት ማስነሳት ይችላሉ ብሏል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በአምስት ወራት ለ70 የመገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አገልግሎቶችን ሰጠ ++++++++++++++  -  የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባለፉት አምስት ...
05/06/2026

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በአምስት ወራት ለ70 የመገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አገልግሎቶችን ሰጠ
++++++++++++++

- የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባለፉት አምስት ወራት ለ70 የመገናኛ ብዙኃን በፍቃድና ክትትል ዘርፍ የፍቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት እንዲሁም የዕድሳት አገልግሎት መስጠቱን አስታወቀ።

ባለሥልጣኑ በአዋጅ በተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መሰረት የሚዲያ ዘርፉን እድገት የሚመጥን ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ሁለን አቀፍ የሪፎርም ስራዎች እያካሄደ እንደሚገኝ አመልክቷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘም የሀገሪቷን መገናኛ ብዙኃን በቁጥር፣ በዓይነት እንዲሁም በተደራሽነት እድገት እንዲያስመዝግቡም የበኩሉን አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ እንደሆነም ገልጿል።

በዚህም መሰረት ባለፉት አምስት ወራት (ከጥር እስከ ግንቦት ወራት 2018 ዓ.ም) በባለሥልጣኑ የሀገር ውስጥ ፈቃድ ምዝገባና ብቃት ማረጋገጫ የተሰጣቸውና ዕድሳት የተደረገላቸው የንግድ መገናኛ ብዙኃን፣ የማህበረሰብ እና የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን እንዲሁም የሚዲያ ፕሮግራም ዝግጅትን ጨምሮ 33 ተቋማት ናቸው።

የውጭ ሚዲያን በተመለከተ ደግሞ 16 ቋሚ የዜና ወኪሎች እና 21 በአጭር ጊዜ ዘገባ ፈቃድ የወሰዱ እና የዘጋቢ ፊልም ቀረፃ ፈቃድ የወሰዱ የውጭ ድርጅቶች እንደሚገኙበት ከባለስልጣኑ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ

ለመንግስት ሠራተኞች 15 በመቶ የግብር ቅናሽ ተፈቀደ በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑ ተገለፀ+++++++++++++++   - የገንዘብ ሚኒስቴርን ስምና መለያ በመጠቀም ተዘጋጅቶ በተለያዩ...
21/05/2026

ለመንግስት ሠራተኞች 15 በመቶ የግብር ቅናሽ ተፈቀደ በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑ ተገለፀ
+++++++++++++++

- የገንዘብ ሚኒስቴርን ስምና መለያ በመጠቀም ተዘጋጅቶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ለመንግስት ሠራተኞች 15 በመቶ የግብር ቅናሽ ተፈቅዶ በሥራ ላይ ውሏል በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አሰታወቀ።

በሚኒስትሩ ፊርማና ማኅተም፣ ለሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች እንደተላከ ተደርጎ የተሰራጨው ይህ ደብዳቤ፤ "ለአገሪቱ የመንግሥት ሠራተኞች 15 በመቶ የሥራ ግብር ቅናሽ ተደርጓል" የሚል መረጃ ተሰራጭቷል።

ለመንግስት ሠራተኞች 15 በመቶ የግብር ቅናሽ ተፈቅዶ በሥራ ላይ ውሏል በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ተገልጿል።

የገንዘብ ሚኒስቴር ማንኛውንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን የተመለከቱ መረጃዎችን በራሱ ማህበራዊ ሚድያዎችና ከትክክለኛ የመረጃ ምንጮች ላይ የሚያወጣ በመሆኑ ሕብረተሰቡ ከመሰል አሳሳች መረጃዎች እንዲጠነቀቁ አሳስቧል።

በሀና እጅጋየሁ

#ኢትዮጵያመገናኛብዙኃን

Address


Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ:

Shortcuts

Share