26/05/2023
የኮልፌ ቀራኒዮ እና የፉሪ ክፍለ ከተማ አስተዳደሮች በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች ላይ በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል የፊርማ ስነ_ ስርአት ተካሔደ፡፡
ግንቦት 18ቀን 2015 ዓ.ም
ሁለቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደሮች በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች ማለትም በከተማ ጽዳት፤ በመሰረተ ልማት እና በመሰል ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት የሁለቱም ክ/ከተሞች ዋና ስራ አስፈጻሚዎች፣ ዋና ስራ አስኪያጆች እና የሚመለከታቸው የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት የፊርማ ስነ ስርአት ተካሒዷል።
አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ በበኩላቸው ክፍለ ከተሞቹ አጎራባች በመሆናቸው የጋራ አገልግሎት መስጠት ስለሚገባ ሕዝቡን የሚያስተሳስር ስራ በልማት ፤በፅዳትና በሌሎች ስራዎች ላይ እንደ አስተዳደር ከእናንተ ጋር ተቀናጅትን እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል፡፡
የፉሪ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ወይንሸት ግዛው በተፈራረምነው ስምምነት መሰረት ያለንን አቅም በመጠቀም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ ያጋራ አላማችንን ማሳካት አለብን ለዚህም በቀጣይ ዕቅዶቻችን ውስጥ አካተን በልማትና በሌሎች ዘርፎች አብረን ተባብረን አንሰራለን ያሉ ሲሆን እናንተም ይህን ተረድታችሁ እዚህ በምጣታችሁ በክፍለ ከተማው ስም አመሰግናለሁ ብለዋል፡፡
አመራርነት ሁሉንም ህዝብ በእኩልበማገልገል ያሉትን ችግር በመካፈል መፍትሄ ለመስጠት ነው ያሉት አቶ አዱኛ ማሩ የሸገር ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ ሲሆኑ ዛሬ የጀመርነውን ስራ በከተማ ደረጃ ማስፋት አለብን እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማና ክፍለ ከተማዎቿ ጋር በአንድነት ለጋራ እድገት መስራት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ አስተዳደሮቹ በጋራ በሚሰሩባቸው ተግባራት ላይ ገለጻ በማድረግ የተወያዩ ሲሆን ከመድረኩም በተለያዩ የጋራ ጉዳዮች ላይ ህብረተሰቡን አስተባብረን በማሳተፍ በአንድነት ለማደግ እንሠራለን ሲሉም ተሳታፊዎች ሀሳባቸውን ሰተዋል፡፡