Akaki Kality woreda 10 communication -አቃቂ ቃሊቲ

Akaki Kality woreda 10 communication -አቃቂ ቃሊቲ የወረዳ 10 አስተዳደር በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ስር የሚገኝ ሲሆን ልዩ ስሙ ገላን ጉራ ይባላል -አቃቂ ቃሊቲ

በወረዳው የተቋቋመው የሰንበት ገበያ የኑሮ ዉድነትን ከመዋጋት አኳያ ትልቁን ሚና እየተጫወተ እንደሆነ ተገለፀ!ነሐሴ 25/2018   /ወረዳ 10 ኮሙኒኬሽን/በወረዳ 10 አስተዳደር የተቋቋመው ...
31/08/2026

በወረዳው የተቋቋመው የሰንበት ገበያ የኑሮ ዉድነትን ከመዋጋት አኳያ ትልቁን ሚና እየተጫወተ እንደሆነ ተገለፀ!

ነሐሴ 25/2018 /ወረዳ 10 ኮሙኒኬሽን/

በወረዳ 10 አስተዳደር የተቋቋመው የሰንበት ገበያ አምራቾችንና ሸማቾችን በቀጥታ በማገናኘት የኑሮ ውድነትን ከመቋቋም አኳያ ትልቁን ሚና እየተጫወተ መሆኑ ተገለጸ።

የሰንበት ገበያው ለወረዳው ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ከወረዳው ውጭ ካሉ አጎራባች አካባቢዎች ለሚመጡ ሸማቾችም ምቹ የግብይት አማራጭ ሆኖ እያገለገለ መሆኑ ታውቋል። በዚህም በገበያው ላይ የሚቀርቡ ምርቶች ጥራታቸውን የጠበቁ ሲሆኑ፣ ሸማቾችም የሚፈልጓቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ዕድል ፈጥሯል።

በተለይም በገበያው የሚሸጡ ምርቶች ከመደበኛው የገበያ ዋጋ አንፃር በቅናሽ መቅረባቸው የሸማቾችን የግዢ አቅም ለማጠናከር እና የኑሮ ውድነት የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪም ህብረተሰቡ የሰንበት ገበያውን የመጠቀም ልምዱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ ታውቋል። ይህም ገበያው በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱንና ለተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን ለማቅረብ ያለውን ሚና እያጠናከረ መሆኑን ያሳያል።

የሰንበት ገበያው አምራችና ሸማችን በቀጥታ በማገናኘት፣ የመካከለኛ ደላላ ሰንሰለትን በመቀነስ እና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ የኑሮ ውድነትን በመቋቋም ረገድ ያለውን አስተዋፅኦ እያጠናከረ መሆኑ ተገልጿል።

 #ማስታወቂያየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሐኒት ባለስልጣን የአቃቂ  ቃሊቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት  የጤና ተቋማት እና የመድሃኒት ተቋማት ምዝገባ በማከናወን ላይ ይገኛል።በመሆኑን ም...
31/08/2026

#ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሐኒት ባለስልጣን የአቃቂ ቃሊቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የጤና ተቋማት እና የመድሃኒት ተቋማት ምዝገባ በማከናወን ላይ ይገኛል።

በመሆኑን ምዝገባው እስከ ነሀሴ 30/2018 ዓ.ም ብቻ በኦንላይ licence.AAFDA.gov.et ላይ organization የሚለውን በመምረጥ አስፈላጊ መረጃ አሟልቶ በመመዝገብ ቀኑ በመጠናቀቁ ከሚመጣ አላስፈላጊ ቅጣት መዳን እንደሚገባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ አስታውቋል።

ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ

መጪው የአዲስ ዓመት በዓል አስመልክቶ በቂ የዶሮ እና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶችን ለማህበረሰቡ ለማቅረብ ሰፊ ስራ እየሰራ ይገኛል።ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲየአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተ...
31/08/2026

መጪው የአዲስ ዓመት በዓል አስመልክቶ በቂ የዶሮ እና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶችን ለማህበረሰቡ ለማቅረብ ሰፊ ስራ እየሰራ ይገኛል።

ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለመጪው የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት በዓል በበዓላት ወቅት የምርት አቅርቦት እጥረትና ያልተገባ የዋጋ ንረት አስቀድሞ ለመግታት የአካባቢውን አርሶ አደሮች ፣ ሸማች ማህበራትና የተለያየ አምራቾችን በማቀናጀት የዶሮ እና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶችን ለማቅረብ ሰፊ ስራ እየሰራ ይገኛል።

ይህንኑ ዝግጅት ስኬታማ ለማድረግም ምርቶችን በቀጥታ ከአምራች ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ በክፍለ ከተማው በሚገኙ የእሁድ ገበያዎች እና የበዓል ባዛሮች ላይ የተለያዩ የእንስሳት ተዋፅኦዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪው እንዲቀርቡ ለማድረግ ከወዲሁ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች አጠናቋል።

ይህ አሰራር ነዋሪው ምርቶችን በቅርበትና በዝቅተኛ ዋጋ እንዲገዛ ከመደገፉም በላይ አምራቾች ምርቶቻቸውን በቀጥታ ለገበያ የሚያቀርቡበትን ዕድል ይፈጥራል።

ዛሬ የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት  መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል። በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የ...
30/08/2026

ዛሬ የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል።

በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የሰጠንን ሃላፊነት መነሻ ያደረገ ስትራቴጂክ እቅድ ነድፈን ቃላችንን በተግባር ቆጥረን ፈፅመን የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ከተማችን ደግሞ ተወዳዳሪ እንድትሆን አድርገናል።

ይህንኑ መነሻ በማድረግ የከተማችን ነዋሪ እምነት አድሮበት ዳግም መርጦን ሀላፊነት ሰጥቶናል።
የዛሬው ውይይትም የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት መነሻ ያደረገ፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ዝርዝር ግቦች ላይ ተወያይተን በማዳበር የባለፉት አምስት ዓመታት አፈፃፀምን በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጁነታችንን የምናረጋግጥበት መድረክ ነው።

እነዚህን ዝርዝር ውይይቶች ስናደርግ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ በማሳደግ፣ አመራራችን ከፊት ሆኖ የበለጠ እየሮጠ ህዝባችንንና የልማት አጋሮቻችንን በማስተባበርና ተሞክሮዎችን በማስፋት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በሀገራዊ ማንሰራራት ውስጥ የአዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌትነት ለማረጋገጥ እንተጋለን።

በተጨማሪም በክረምት የያዝናቸው የ90 ቀን ስራዎች ውስጥ የ60 ቀናት አፈፃፀማችንንም የምንገመግምበት የውይይት መድረክ ነው።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና የህብረተሰቡን የገበያ ጫና ለመቀነስ ያለመ በቅዳሜ እና እሁድ ገበያ የምርት አቅርቦት በስፋት እየተካሄደ ይገኛል።ነሀሴ 24/201...
30/08/2026

መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋትና የህብረተሰቡን የገበያ ጫና ለመቀነስ ያለመ በቅዳሜ እና እሁድ ገበያ የምርት አቅርቦት በስፋት እየተካሄደ ይገኛል።

ነሀሴ 24/2018 ዓ/ም አቃቂ ቃሊቲ

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የበዓል መዳረሻን አስመልክቶ በቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች የህብረተሰቡን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ በርካታ የግብርና እና የፍጆታ ምርቶች በስፋት እየቀረቡ ይገኛሉ።

የበዓል ገበያው አርሶ አደሩን እና ሸማቹን በቀጥታ ያገናኘ በመሆኑ ለህብረተሰቡ ጥራት ብዛት ያላቸውን መሰረታዊ የምግብ ሸቀጣ ሸቀጦች እና የግብርና ውጤቶች ከተለመደው የችርቻሮ ገበያ በተሻለና በቅናሽ ዋጋ እንዲሸምት አጋጣሚ ፈጥሯል።

በመሆኑም የክ/ከተማዋ ነዋሪዎች በተዘጋጁት የገበያ አማራጮች በመጠቀም የበዓል ፍላጎታቸውን ያለ ዋጋ ጫና እና ያለ ስጋት እንዲያሟሉ ጥሪ ተላልፏል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እግር ኳስ ፌደሬሽን አዘጋጅነት ሲካሄድ በቆየው ከ20 ዓመት በታች የተስፋ ቡድን የእግር ኳስ ውድድር ላይ ሲሳተፍ የቆየው የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር...
29/08/2026

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እግር ኳስ ፌደሬሽን አዘጋጅነት ሲካሄድ በቆየው ከ20 ዓመት በታች የተስፋ ቡድን የእግር ኳስ ውድድር ላይ ሲሳተፍ የቆየው የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከ20 ዓመት በታች ተስፋ እግር ኳስ ቡድን አበረታች ውጤት ዉጤት አስመዘገበ።

የተስፋ ቡድኑ ከተቋቋመ ገና የመጀመሪያ ዓመቱ መሆኑን የገለፁት የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብሩክ ዘርጋው ቡድኑ በተቋቋመ በአንድ ዓመት ውስጥ ለፍፃሜ በመድረስ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቅ መቻሉን በቀጣይ ይህ ቡድን ለክፍለ ከተማው ዋና ቡድን መጋቢ እና ተተኪ እንደመሆኑ መጠን አጠናክሮ የማስቀጠል ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

አክለዉም ለቀጣይ ዓመት ቡድኑን የበለጠ በማጠናከርና ጠንካራ ስብስብ ይዞ በመውጣት ሻምፒዮን ለመሆን በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል ።

የተስፋ ቡድኑ በዛሬው ዕለት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከአየር ሀይል ንብ ተስፋ ቡድን ጋር ተጫውቶ 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት ድል ሳንቀናዉ ቢቀርም ሁለተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።

ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም | አቃቂ ቃሊቲ

"ፈተናን በስኬት ቃልን በተግባር!"

52 አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የG+5   ግንባታ ተጀመረ።ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲየአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር "በጎነት ለአዲስ አበባ ከፍታ "በሚል መሪ ቃል 52 ...
29/08/2026

52 አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የG+5 ግንባታ ተጀመረ።
ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም አቃቂ ቃሊቲ

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር "በጎነት ለአዲስ አበባ ከፍታ "በሚል መሪ ቃል 52 አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የG+5 የበጎነት መንደር ግንባታ ልዩ ቦታዉ ወረዳ 02 ወንድማማች ጊቢ አካባቢ ተጀመረ።

በግንባታ ማስጀመርያዉ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀንጋቱ መሀመድ፣ የክ/ከተማዉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተሃድሶ አበባዉን ጨምሮ የክፍለ ከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ፣ የክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች ፣ ባለሀብቶች ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።

መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት እየተከናወነ የሚገኘው የበጎነት መንደር የቤት ግንባታ የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ችግር በመፍታት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የገለፁት የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሀንጋቱ መሀመድ በክፍለ ከተማው ባለፉት ዓመታት በርካታ አዳዲስ የመኖሪያ ቤቶች ተገንብተው ለነዋሪዎች መተላለፋቸው አውስተዋል።

ወ/ሮ ሀንጋቱ መሀመድ አያይዘውም መንግስት ሊሸፍን ባልቻለባቸው አካባቢዎች ህብረተሰቡን በማሳተፍ ባለሀብቶችንና በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር በርካታ ቤቶችን መገንባት መቻሉንና በዛሬው ዕለትም የተጀመረው የበጎነት መንደር ፕሮጀክት በቅን አሳቢ ባለሀብቶች ድጋፍ መጀመሩን ጠቁመዋል።

አያይዘውም በጎነት ለራስ የሚደረግ ታላቅ ስጦታ በመሆኑ ተግባሩ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትና ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ጥራቱን ጠብቆ ለተጠቃሚዎች እንዲተላለፍ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በጎነት የልቦና ቅንነትን የሚጠይቅ ተግባር ነዉ ያሉት የክ/ከተማዉ ህ/ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበርያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይቻላል አይኔ በጎነት መንደሩ የነዋሪዎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻል የማህበራዊ ተጠቃሚነታቸዉን ከማሳደግ አኳያ ትልቅ ድርሻ እንዳለዉ ገልፀዋል።

ከባለሀብቶች መካከል አቶ ነጋሲ ብርሀኔ በበኩላቸው የበጎነት መንደር ዓላማው ሰፊና ጥልቅ እንዲሁም የዜጎችን ችግር የሚፈታና ለቀጣይ ስራዎች የሚያነሳሳ መሆኑን በመጥቀስ መሰል ስራዎችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ቃል ገብተዋል።

" !"

ለበለጠ መረጃ፦ https://linktr.ee/akaki_kality_communication

3ተኛውን ቀን የያዘው "ከስክሪን ቀንሰን መፅሐፍን እንግለፅ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው የንባብ ሳምንት በድምቀት እየታሰበ ይገኛል።ለምን እንፅፉለን በሚል የዕለቱ መሪ ቃል በቀን 23/...
29/08/2026

3ተኛውን ቀን የያዘው "ከስክሪን ቀንሰን መፅሐፍን እንግለፅ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው የንባብ ሳምንት በድምቀት እየታሰበ ይገኛል።

ለምን እንፅፉለን በሚል የዕለቱ መሪ ቃል በቀን 23/12/18 ዓ.ም ክፍለ ከተማው ላይ ከሚገኙ የተለያዩ ደራሲያን እንዲሁም የወጣት አደረጃጀቶች ጋር ንባብን ባህል በማድረግ ዙርያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በውይይቱም የማንበብ ጥቅምን እና በአቃቂ የህዝብ ቤተመፅሐፍት የነበራቸውን ትዝታዎች እንዲሁም ቤተመፅሐፍቱን እንዴት እንደግፋለን የሚሉ ሀሳቦች የተንሸራሸሩ ሲሆን በእለቱ ከተገኙ ደራሲያን የመፅሐፍ ስጦታም ተበርከቷል።

በመጨረሻም በተለያዩ ወቅቶች ለቤተመፅሐፍቱ በሀሳብም በጉልበትም እንዲሁም መፅሐፍትን በማሰባሰብ ሲለግሱ ለቆዩ አካላት በክ/ከተማዉ ባህልና ኪነ-ጥበብ ፅ/ቤት የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቷል።

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ም

"ፈተናን በስኬት ቃልን በተግባር!"

ለበለጠ መረጃ፦ https://linktr.ee/akaki_kality_communication

የሰንበት ገበያ ለማህበረሰቡ ጉልህ ጥቅም እያበረከተ መሆኑ ተገለፀ።ነሀሴ23/2018(ወረዳ 10 ኮሙኒኬሽን) በሰንበት ገበያ የሚካሄደዉ ግብይት  ለአካባቢው ማህበረሰብ በርካታ ጥቅሞችን እያበረ...
29/08/2026

የሰንበት ገበያ ለማህበረሰቡ ጉልህ ጥቅም እያበረከተ መሆኑ ተገለፀ።

ነሀሴ23/2018(ወረዳ 10 ኮሙኒኬሽን)

በሰንበት ገበያ የሚካሄደዉ ግብይት ለአካባቢው ማህበረሰብ በርካታ ጥቅሞችን እያበረከተ መሆኑ ታዉቋል።

ግብይቱ አርሶ አደሮች ያመረቱትን
ምርት በቀጥታ ለሸማቾች እንዲያቀርቡ ዕድል በመፍጠር የገቢ ምንጫቸውን እንዲያሳድጉ እያገዘ ሲሆን በተጨማሪም ለአካባቢዉ ማህበረሰብ የማሰጠዉ ጠቀሜታ ለመረዳት ተችሏል።

የተለያዩ የምግብና የፍጆታ ምርቶችን በቀላሉ የሚያገኝበት አጋጣሚ በመሆኑ በአካባቢው የንግድ እንቅስቃሴን እያነቃቃ መምጣቱ ተጠቁሟል።
የሰንበት ገበያ ለወጣቶችና ለሴቶች የማህበረሰቡ ክፍሎች የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ በአካባቢው የሚመረቱ ምርቶች የገበያ ተደራሽነት እንዲያገኙ አስተዋፅዖ እያደረገ ነው።

ማህበረሰቡ ገበያው ያለውን ጥቅም በማስቀጠልና በማሳደግ ለአካባቢው ኢኮኖሚ የበለጠ አስተዋፅዖ እንዲያደርግ ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግለት ጠይቋል።

Address

Akakiy Kalitiy W10
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Akaki Kality woreda 10 communication -አቃቂ ቃሊቲ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Akaki Kality woreda 10 communication -አቃቂ ቃሊቲ:

Shortcuts

Share