የካ ወረዳ 1 ብልፅግና ፓርቲ ሚዲያ

የካ ወረዳ 1 ብልፅግና ፓርቲ ሚዲያ መንገዳችን መደመር መዳረሻችን ብልፅግና ነዉ።

የጳጉሜን 2፦ማንሠራራት ቀንየሀገራችንን ብሩህ ተስፋና የተገበሩ ትልልቅ እቅዶችን የምናስብበት፣ የታሪክ ጉዞአችንን አቅጣጫ የቀየሩ ሁለንተናዊ የልማት ስኬቶቻችንን የምናመሰግንበት ልዩ ዕለት ነ...
07/09/2026

የጳጉሜን 2፦ማንሠራራት ቀን

የሀገራችንን ብሩህ ተስፋና የተገበሩ ትልልቅ እቅዶችን የምናስብበት፣ የታሪክ ጉዞአችንን አቅጣጫ የቀየሩ ሁለንተናዊ የልማት ስኬቶቻችንን የምናመሰግንበት ልዩ ዕለት ነው።

በባለፉት ጥቂት ዓመታት ሀገራችን በብዙ ፈተናዎች ውስጥ አልፋ፣ በጽናትና በትጋት በሰራቻቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች አማካኝነት እውን ያደረገቻቸው የልማት ስኬቶች የኢትዮጵያን የማንሠራራት መንፈስ በግልጽ ያሳያሉ። በታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ በግብርናው ዘርፍ በተመዘገበው የስንዴ ምርታማነትና በሌሎች ሀገራዊ የልማት ኢኒሼቲቮች የተመዘገቡት ስኬቶች ሀገራችን በራሷ አቅምና ጥረት ወደ ተሻለ የዕድገት ደረጃ መሸጋገር እንደምትችል በተግባር ያረጋገጡ አበይት ማረጋገጫዎች ናቸው።

​መዲናችን አዲስ አበባ የዚህ ሁለንተናዊ ማንሠራራት እና የለውጥ ጉዞ ዋነኛ ማዕከል በመሆን ድንቅ የልማት ምሳሌነቷን አስመስክራለች። የተቀናጀው የኮሪደር ልማት፣ የሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ግንባታ፣ የወንዝ ዳርቻ ማደስና የጽዳት ሥራዎች፣ የትራፊክና የመሠረተ ልማት ማሻሻያዎች እንዲሁም የነዋሪዎችን ማኅበራዊ አገልግሎት ያደራጁ የልማት ሥራዎች የከተማዋን ገጽታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።

አዲስ አበባ አሁን ላይ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለውጭ እንግዶችና ለቱሪስቶች ደግሞ ማራኪ፣ ዘመናዊና ጽዱ አፍሪካዊት መዲና ሆና በመገንባት ላይ ትገኛለች።

የየካ ክፍለ ከተማ ትራንስፖርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች፣ ሰራተኞች እና የፀጥታ አካላት የጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀንን በማስመልከት የቀበና ወንዝ ዳርቻ የልማት ፕሮጀክትና የቀበና ፕላዛ የመኪና ማቆሚያን ጎብኝቷል።
#የካ

ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀንየተሻለ ከተማን በመጎብኘት፣ የተሻለ ነገን እንገንባ!ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን አስመልክቶ የወረዳው መንግሥት ሰራተኞች በወረዳችን የሚገኙ የተለያዩ የቱሪዝም መዳ...
07/09/2026

ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን

የተሻለ ከተማን በመጎብኘት፣ የተሻለ ነገን እንገንባ!

ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን አስመልክቶ የወረዳው መንግሥት ሰራተኞች በወረዳችን የሚገኙ የተለያዩ የቱሪዝም መዳረሻዎችን እና የወንዝ ዳርቻ ልማቶችን በመጎብኘት የልማቱን ውጤት ተመልክተዋል።

ጉብኝቱ የልማት ውጤቶችን ከመመልከት ባሻገር፣ ማንሰራራት ማለት ያለፈውን በመገምገም አዲስ ሀሳብ፣ አዲስ ተስፋ እና አዲስ የሥራ ትጋት ይዞ ወደፊት መጓዝ ነው የሚለውን መልዕክት ያጠናከረ ነበር።

የወረዳው ሰራተኞችም በጉብኝታቸው ያዩት የልማት ውጤት አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ አዲስ አበባን የቱሪዝም፣ የመዝናኛ እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ እየተከናወነ ያለውን ሁለንተናዊ ልማት በሙሉ አቅማቸው ለመደገፍና የድርሻቸውን በትጋት ለመወጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የየካ ወረዳ 01 መንግሥት ሰራተኞች በአዲስ አበባ ከአንጦጦ ኪዳነምህረት እስከ ሀምሌ 19 ድረስ የተሰሩትን የወንዝ ዳርቻ ልማትን ጉብኝተዋል:: ሰራተኞቹ የመዲናዋን አዲስ ገጽታና የቱሪዝም ሳቢነት የሚያጎሉ የመሰረተ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ተመልከተዋል። በአካባቢው የተከናወኑ የከተማ ውበት፣ የአረንጓዴ ልማት፣ የመዝናኛ እና የቱሪዝም ልማቶች ለነዋሪዎች እና ለጎብኚዎች የተሻለ አካባቢ እየፈጠሩ መሆናቸውን ተመልክተዋል።

ማንሰራራት ከትዝታ ወደ ተስፋ፣ ከተስፋ ወደ ተግባር የሚያሻግረን ጉዞ ነው። ዛሬ የምናየውን ልማት በጋራ በመጠበቅና በማስፋት፣ ነገ የተሻለች አዲስ አበባን እንገንባለን!

ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን፤ ያለፈውን እናያለን፣ ዛሬን እንገነባለን፣ ነገን በተስፋ እንደርሳለን!
yeka w_1

ጳጉሜን  2 የማንሰራራት ቀን! ጳጉሜን የአስራ ሶስት ወር ፀጋ የሆነችው ሀገራችን በረከቶች፣ ከዘመን ዘመን መሸጋገሪያ ድልድል፣ የአዲስ ዓመት መዳረሻ ብሩህ ተስፋ አብሳሪ ተጨማሪ ቀናት እና ...
07/09/2026

ጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን!


ጳጉሜን የአስራ ሶስት ወር ፀጋ የሆነችው ሀገራችን በረከቶች፣ ከዘመን ዘመን መሸጋገሪያ ድልድል፣ የአዲስ ዓመት መዳረሻ ብሩህ ተስፋ አብሳሪ ተጨማሪ ቀናት እና ወር ናት።

ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ የዘመን አቆጣጠር ያላት ጥንታዊት ሀገር መሆኗን ጠቋሚ ምልክቶች፣ የአዲስ ዓመት መዳረሻ ብስራት ናቸው የጳጉሜን ቀናት።

የጳጉሜን ቀናት ከ2011 ዓ/ም ጀምሮ የህዝባችንን ወንድማማችነት እና እህትማማችነት በሚያጎለብቱ፣ የመጪውን አዲስ ዓመት ተስፋዎች በሚያንፀባርቁ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች ሲከበሩ ቆይተዋል።

የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናትም እንደ ሀገርም ሆነ በመዲናችን ለአዲስ ዓመት የላቁ ድሎች ተነሳሽነትን ከፍ በሚያደርግ መልኩ ‹‹ የኢትዮጵያ ማንሰራራት!›› በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ህዝባዊ ሁነቶች እየተከበሩ ይገኛሉ።

በተለወጠ አዲስ እሳቤ፣ በዳበረ የስራ ባህል የብልፅግና ፓርቲን አሻጋሪ እሳቤዎች በተግባር በመተርጎም ኢትዮጵያን ከነበረችበት ጥልቅ ጉስቁልና በማውጣት ወደ ማንሰራራት ማሸጋገር ተችሏል፡፡

ብልሹ አሰራሮችን በማስወገድ፣ አዳዲስ አቅጣጫዎችን በመተለም፣ ለዓለም አቀፍ ጫናዎች ያልተበገረ ዲፕሎማሲያዊ ድል በማስመዝገብ፣ ባለፈው ዓመት በተባበሩ እጆቻችን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዕውን ማድረግ መቻላችን ይታወሳል፡፡

በህብረ ብሔራዊቷ መዲናችን በገበታ ለሸገር የጀመረው ታሪካዊ አሻራ፣ በገበታ ለሀገርና በገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ማበራከት አስችሏል፡፡

እየተገነባ የሚገኘው ግዙፉ የማዳበሪያ ፋብሪካም ለምርትና ምርታማነት ማደግ በሚኖረው ጉልህ ሚና የምግብ ዋስትናችንን እና የምግብ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ ለምናደርገው ርብርብ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው፡፡

የአፍሪካውያን ኩራት፣ ዓለም አቀፍ መዲና በሆነችው በአዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመዘገበው የልማት አብዮትም ለኢትዮጵያ ማንሰራራት ጉልህ ሚና እያበረከተ ይገኛል፡፡

ከዘመናዊ የከተማነት እሳቤ እርቃ የቆየችው መዲናችን በኮሪደር ልማቶች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን ከፍ አድርጋለች፡፡ በተጨባጭ ኮስምነው በስም ብቻ ገዘፍ ብለው የሚታወቁት ፒያሳን እና ካዛንችስን የመሳሰሉ ሰፈሮችም እንደ አዲስ በመገንባታቸው የህዝባችንን የኑሮ ደረጃ አሳድገዋል፡፡

ተግባራዊ በተደረገው የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክትም የህልውና አደጋ ተጋርጦባቸው የቆዩ ቀበናን የመሳሰሉ የከተማችን ወንዞች እንደ አዲስ ማንሰራራት ጀምረዋል፡፡

በአዲስ አበባ በ2018 በጀት ዓመት ብቻ ከ60 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለህዝባችን ግልጋሎት እየሰጡ ሲሆን፤ በርካታ ዜጎችም የቋሚና የጊዜያዊ የስራ ዕድሎች ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

የተገነቡ ግዙፍ ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን ጥረት ማፋጠን ችለዋል፡፡

ስታንዳርዳቸውን ጠብቀው የተገነቡ ጥራታቸውን የጠበቁ ግዙፍ መንገዶችም ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴውን አሳልጠዋል፡፡

ከመደበኛ ስራዎች ጎን ለጎን የጳጉሜን ቀናት ስናከብርም፣ የመጪውን ጊዜ ተስፋ የሚያለመልሙ፣ የህዝባችንን ማህበራዊ መስተጋብር የሚያጠናክሩ፣ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት ፅኑ መሰረት የሚሆኑ ስራዎችን በማከናወን ሊሆን ይገባል፡፡

በአዲሱ ዓመት በግለሰብ ደረጃም ሆነ በከተማችንና በሀገራችን ለሚከናወኑ ተግባራት እንዲሁም ለሚመዘገቡ ድሎች ሙሉ ዝግጅትን አጠናቆ ወደ ተግባር መግባትም ከሁላችንም ይጠበቃል።


በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕ...
07/09/2026

ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የጳጉሜን 2 የማንሠራራት ቀን!በየካ ክፍለ ከተማ የማንሠራራት ቀንን በማስመልከት ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ነው።የጳጉሜን 2 የማንሠራራት ቀን አገራችን ኢትዮጵያ በብዙ ፈተናዎች ...
07/09/2026

የጳጉሜን 2 የማንሠራራት ቀን!

በየካ ክፍለ ከተማ የማንሠራራት ቀንን በማስመልከት ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ነው።

የጳጉሜን 2 የማንሠራራት ቀን አገራችን ኢትዮጵያ በብዙ ፈተናዎች ውስጥ አልፋ እንደ አዲስ የላቀ ከፍታን መያዝ እንደምትችል ያረጋገጥንበት፣ የጽናት እና የድል ምልክት ነው።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተገነቡት እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት እና የዲጂታል ኢኮኖሚ መሰረተ-ልማቶች እንዲሁም ሀገራዊ የግብርና ምርታማነት ማሻሻያዎች ኢትዮጵያ በራሷ አቅምና ሀብት ትልቅ ታሪክ መስራት እንደምትችል በተግባር ያሳዩ ናቸው።

እነዚህ ግዙፍ ሀገራዊ ኢኒሼቲቮች የሀገርን ሉዓላዊነትና ኢኮኖሚያዊ ነፃነት ከማረጋገጣቸው በላይ፣ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የኃይልና የኢኮኖሚ ማዕከል ሆና እንድትወጣ ዘላቂና ጠንካራ መሰረት ጥለዋል።​

የማንሠራራት ቀን ያለፉ ስኬቶቻችንን የምናደንቅበት ብቻ ሳይሆን፣ ለነገው የበለጠ ትልቅ ስራ የምንነሳሳበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።አሁን የተመዘገቡት ውጤቶች ኢትዮጵያና አዲስ አበባ ወዴት እየገሰገሱ እንደሆነ የሚያሳዩ የማእዘን ድንጋዮች ናቸው።

ይህንን የጀመርነውን የእድገትና የብልፅግና ጉዞ አፋጥነን ለማስቀጠል፣ ሁላችንም በያለንበት ሙያና የኃላፊነት ዘርፍ በበለጠ ትጋት፣ አንድነትና ቁርጠኝነት በመቆም ለተሻለ ነገ መስራት ይኖርብናል።
#የካ

ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን በአብሮነት እንሻገር፤ በብልፅግና እንልማ!ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀን ያለፈውን በጥበብ በመገምገም፣ የተሳካውን በማጠናከር፣ የተሳሳተውን በማረምና በአዲስ ተስፋ ወ...
07/09/2026

ጳጉሜ 2 — የማንሰራራት ቀን በአብሮነት እንሻገር፤ በብልፅግና እንልማ!

ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀን ያለፈውን በጥበብ በመገምገም፣ የተሳካውን በማጠናከር፣ የተሳሳተውን በማረምና በአዲስ ተስፋ ወደ ተሻለ ነገ ለመሻገር የሚያነሳሳ ቀን ነው።

ማንሰራራት የግለሰብ ጥረት ብቻ ሳይሆን የጋራ ኃይልን የሚያሰባስብ፣ ልዩነትን እንደ ጥንካሬ የሚቀበልና በጋራ ግብ ዙሪያ ሕዝብን የሚያሰልፍ የአብሮነት መንገድ ይሆናል። በጋራ ሲንቀሳቀስ ማህበረሰብ የበለጠ የለውጥ ኃይል ይሆናል።

የአብሮነት ቀን ማለትም ከመልዕክት ወደ ተግባር መሻገር፣ የሕዝብን ተሳትፎ ማጠናከር፣ የሚታዩ ችግኝቶችን በጋራ መለየትና በጋራ መፍትሔ መፈለግ ነው።

አብሮነት በቃል ብቻ አይገለጽም፤ በሥራ ይገለጻል። አካባቢን በማስዋብ፣ ንፅህናን በመጠበቅ፣ በጎ ተግባራትን በማስፋፋት፣ ወጣቶችን በፈጠራና በሥራ በማሳተፍ እና የሕዝብን ተሳትፎ በማሳደግ የማንሰራራት መንፈስ ወደ ተጨባጭ ውጤት ይቀየራል።

ዛሬ የምንገነባው አብሮነት የነገ ትውልድ መሠረት ነው፤ ዛሬ የምናደርገው የጋራ ጥረት የነገ ውጤት ነው። ስለዚህ ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን ስናከብር፣ ያለፈውን ከማስታወስ ባለፈ አንድነታችንን አጠናክረን፣ በጋራ ተሳትፈን፣ በተግባር ተረባርበን የተሻለች ማህበረሰብና ከተማ የመገንባት ቃልኪዳናችንን እናድስ።

ጳጉሜ 2 ማንሰራራት ቀንን ምክኒያት በማድረግ በወረዳ የሚገኙ ሀሉም ጽ/ቤቶች በአንድ ማዕከል ወርቃማ ሰኞን ውይይት ተካሄደ ።

‎‎እለቱን አስመልክቶ የወረዳ 01 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አዲስ አጎናፍር የተዘጋጅውን የውይይት ሰነድ አቅርበዋል

የማንሰራራት ቀን የአብሮነት ቀን!
በመደመር ኃይላችንንእናጠናክር፤ በጋራ ጥረታችን የተሻለ ነገን እንገንባ!

"ትናንት 'ኢትዮጵያ ተነሥታለች' ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው”ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
07/09/2026

"ትናንት 'ኢትዮጵያ ተነሥታለች' ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው”

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የማንሠራራት ቀን ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ! ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ...
07/09/2026

የማንሠራራት ቀን

ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!

ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።



Guyyaa Bayyanannaa

Itoophiyaa jecha bira darbuun milkaa'ina qabatamaadhaan dhaabbatte!

Kaleessa "Itoophiyaan Kaateetti" gaafa jennu hawwii utuu hin ta'iin dhugaa har'a qabatamaadhaan mirkaneessinedha! Ijaarsa Hidha Haaromsaa Guddicha irraa hanga misooma kooriidarii ammayyaatti, Buufata Xiyyaaraa Bishooftuu guddichaa hanga riifoormii dinagdee maakrootti dadammaqinsi biyya keenyaa gochaan dhugoomeera. Jijjiiramni kun sadarkaa jireenyaa lammiilee keenyaatiin, ammayyoomuu magaalotiifi carraa hojii uumuutiin ifa dhugaa ta'uurraayyuu, mul'ata guddaa abdii egeree ijoollee keenyatti horudha. Kana booda duubatti hin deebinu! Imala bayyanannaa seena-qabeessa eegalleen humna misoomaa keenya caalaatti saffisiisuudhaan olka'insa Itoophiyaa gara badhaadhina waaraatti ol ni kaafna.

ጳጉሜ 2የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን፡ ቃልን በተግባር ያረጋገጠ  ጉዞ!   #የካ
07/09/2026

ጳጉሜ 2
የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን፡ ቃልን በተግባር ያረጋገጠ ጉዞ!
#የካ

ጳጉሜ 1፦የእመርታ ቀንከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበጥ ብርሃን!የዕዳ ጫናን መቀነስና የገቢ አቅምን ማሳደግ ዘላቂ የምጣኔ ሀብት ነፃነት መሠረት ነው። ባለፉት ዓመታት የተተገበሩት ጠንካራ የፋይናን...
06/09/2026

ጳጉሜ 1፦የእመርታ ቀን

ከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበጥ ብርሃን!

የዕዳ ጫናን መቀነስና የገቢ አቅምን ማሳደግ ዘላቂ የምጣኔ ሀብት ነፃነት መሠረት ነው። ባለፉት ዓመታት የተተገበሩት ጠንካራ የፋይናንስ ማሻሻያዎች ሀገራዊ የምርት አቅማችንን ከማሳደጋቸውም በላይ ኢኮኖሚያችን በራሱ እግር ላይ እንዲቆም ትልቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል። ይህ የፋይናንስ ጥንካሬ ለነገዋ ኢትዮጵያ አስተማማኝ መሠረት ጥሏል።

​ፕሮጀክቶችን በተቀመጠላቸው ጊዜና በጀት አጠናቆ ማስረከብ የሥራ ባህላችን አዲስ መገለጫ ሆኗል። ግዙፍ ሀገራዊና አካባቢያዊ ፕሮጀክቶች ያለ ብክነትና በከፍተኛ ጥራት መጠናቀቃቸው የታለመላቸውን የልማት ግብ በፍጥነት እንዲመቱ አድርጓቸዋል። ይህ አሰራር ሀገራዊ ሀብትን በአግባቡ የመጠቀምና የውጤታማነታችን ማረጋገጫ ነው።

​በታዳሽ ኃይል ልማት ረገድ የተመዘገበው ስኬት ሀገራችንን ከማብራት አልፎ ለቀጠናው አገራት ዋና የኃይል ምንጭ እንድትሆን አስችሏታል። የአረንጓዴ ኤሌክትሪክ አቅርቦታችን ለቀጣናዊ ትስስርና ለአካባቢያዊ የኢኮኖሚ ውህደት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ የወጭ ንግዳችንንም በማጠናከር ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ እያስገኘ ይገኛል።

​የአገልግሎት ዘርፉን በዲጂታል አሰራር ማዘመናችን ሌላው ትልቅ የእመርታችን ማሳያ ነው። ዲጂታላይዜሽን አላስፈላጊ ወጪዎችን በማስቀረት የበጀት ጉድለትን ያጠበበ ከመሆኑም በላይ ለዜጎች ቀልጣፋ፣ ግልጽና ከሙስና የጸዳ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል። እነዚህ ሁሉ ድሎች የጋራ ቁርጠኝነታችን፣ ጥረታችንና የእመርታችን ውጤቶች ናቸው።
#የካ
​ #ጳጉሜ1 #የእመርታቀን #ኢትዮጵያ

Address

አዲስ አበባ
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የካ ወረዳ 1 ብልፅግና ፓርቲ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share