Ethiopian Cooperative Commission

Ethiopian Cooperative Commission The Ethiopian Cooperative Commission is a governmental organization that works in and around cooperatives in Ethiopia.
(1)

ጳጉሜን 1 የእመርታ ቀንእመርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት!ከጳጉሜ ቀናት አከባበር መርሐ-ግብሮች አንዱ የሆነው "የእመርታ ቀን"  ዛሬ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሠራራት!...
06/09/2026

ጳጉሜን 1
የእመርታ ቀን
እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት!
ከጳጉሜ ቀናት አከባበር መርሐ-ግብሮች አንዱ የሆነው "የእመርታ ቀን" ዛሬ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሠራራት!" በሚል መሪ ቃል በኢኮኖሚ ዘርፍ ተቋማት አዘጋጅነት በግብርና ሚኒስቴር የኮንፈረንስ ማዕከል በመካሔድ ላይ ይገኛል፡፡

መርሐ-ግብሩን የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በክብር እንግድነት ተገኝተው ያስጀመሩት ሲሆን በመቀጠልም "እምርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል ርዕስ የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡

ምንጭ፦ ግብርና ሚኒስቴር



------
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ስለኅብረት ሥራ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት👇

✅ ዩቲዩብ፦https://www.youtube.com/
**
✅ ቴሌግራም፦https://t.me/ethiocoopnews
**
✅ ትዊተር (X)፦https://x.com/Ecccoop
**
✅ ፌስቡክ፦http://facebook.com/EthiopianCooperativeCommission
**
✅ ድረ-ገጽ፦ www.fca.gov.et

ለ200 ተማሪዎች ወደ 1 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ***ኮሚሽኑ በክረምቱ የበጎ አድራጎት መርሐግብር ሶስት ኅብረት ሥራ ማኅበራትን በማስተባበር  በኦሮሚያ ክልል ጉ...
05/09/2026

ለ200 ተማሪዎች ወደ 1 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
***
ኮሚሽኑ በክረምቱ የበጎ አድራጎት መርሐግብር ሶስት ኅብረት ሥራ ማኅበራትን በማስተባበር በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን አዶላ ከተማ ለሚገኙ 200 ተማሪዎች ወደ 1 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በዛሬው እለት አድርጓል።

በተጨማሪም በኅብረት ሥራ ማኅበራት ድጋፍ እየተገቡ ያሉ 6 የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች የግንባታ ሁኔታ በከፍተኛ አመራሩ ተጎብኝቷል።

በመርሐግብሩ ላይ ኮሚሽነር ጌትነት ታደሰ ድጋፍ ያደረጉ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን (አሚጎስ፣ ንቁ ፣ የግብርና ሸማቾች ኅብረት ሥራ ማኅበራት) አመስግንዋል።

በተጨማሪም፣ በክረምቱ መርሐግብር እየተካሄዱ ያሉ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባራት መንግስታዊ ተልዕኮዎች እየሆኑ መምጣታቸውን ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።

ኅብረት ሥራም መረዳዳት እና መደጋገፍ አንዱ መገለጫው መሆኑን የተናገሩት ኮሚሽነር ጌትነት፣ ኮሚሽኑ በዘንድሮው መርሐግብር በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ኅብረት ሥራ ማኅበራትን በማስተባበር እየስንገባ ካለው 6 የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት በተጨማሪ ለ200 ተማሪዎች የትምኅርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን እና እየተደረጉ ያሉ ድጋፎችን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ነጋሽ ቡላላ በበኩላቸው ለተደረገው ድጋፍ ከልብ ያመሰገኑ ሲሆን፣ አያይዘውም ዞኑ በግብርና፣ በቡና፣ በእንስሳት ሃብት፣ በደን ሽፋን እና በሌሎች ሃብቶች የታደለ መሆኑን ተናግረዋል ።

በዞኑም በተጠቀሱት ሃብቶች ላይም በኅብረት ሥራ ዘርፍ በስፋት የመስራት ፍላጎት እንዳለ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል፣ የበጎ ፈቃድ መርሐግብሩ በቀጣይ በሸገር ዙሪያ በቡራዮ ክፍለ ከተማ እና በኮሚሽኑ ውስጥ ለሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰራተኛ ልጆች ቁሳቁሶቹን የማከፋፈል ስራ እና የማዕድ ማጋራት ሥራ እንደሚሰራም የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሃመልማል ክብሬ ተናግረዋል።



------
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ስለኅብረት ሥራ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት👇

✅ ዩቲዩብ፦https://www.youtube.com/
**
✅ ቴሌግራም፦https://t.me/ethiocoopnews
**
✅ ትዊተር (X)፦https://x.com/Ecccoop
**
✅ ፌስቡክ፦http://facebook.com/EthiopianCooperativeCommission
**
✅ ድረ-ገጽ፦ www.fca.gov.et

04/09/2026
ስምንት ኅብረት ሥራ ማኅበራት ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ***በክረምቱ የበጎ አድራጎት መርሐግብር ኮሚሽኑ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራትን እያከና...
04/09/2026

ስምንት ኅብረት ሥራ ማኅበራት ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
***
በክረምቱ የበጎ አድራጎት መርሐግብር ኮሚሽኑ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራትን እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል።

ከነዚህም መካከል ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ አንዱ ሲሆን ለዚህም ከተለያዩ ኅብረት ሥራ ማኅበራት ድጋፍ እያሰባሰበ ይገኛል።

በዚህም 8 ኅብረት ሥራ ማኅበራት የተደረገላቸውን ጥሪ በመቀበል ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል።

ድጋፍ ያደረጉት ማኅበራትም፦ አሚጎስ፣ አፍሪካ የምግብ ደህንነት፣ ከፍታ፣ ላይፍ፣ ንቁ ፣ ኢትዮ ጥሪት፣ አዲሲቷ ኢትዮጵያ የቁጠባ እና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት እና የግብርና ሸማቾች ኅብረት ሥራ ማኅበራት ናቸው ።

የተሰበሰቡ ቁሳቁሶችም ለተማሪዎች የማስረከብ ስራ የተጀመረ ሲሆን፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ ሃየሎም አርአያ ት/ቤት ተማሪ ለሆኑ 70 ተማሪዎዎች ሙሉ ፖኬጅ 70 ደርዘን ደብተር፣ እስኪሪብቶና 70 ቦርሳ ድጋፍ ተደርጓል።

በቀጣይም በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን፣ በሸገር ዙሪያ በቡራዮ ክፍለ ከተማ እና በኮሚሽኑ ውስጥ ለሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰራተኞች ልጆች ቁሳቁሶቹን የማከፋፈል እና የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሃመልማል ክብሬ ተናግረዋል።

03/09/2026
ከ20 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ተደራሽ መደረጉ ተጠቆመ*****የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን በተከናወኑ ተግባራት ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓ...
02/09/2026

ከ20 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ተደራሽ መደረጉ ተጠቆመ
*****
የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን በተከናወኑ ተግባራት ሀገራዊ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የግብርና ሚኒስቴር በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ላይ ግምገማ እያካሄደ ነው።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በ2017/18 የምርት ዘመን የግብርና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።

በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ የግብርና ግብዓቶች በተሳለጠ መልኩ ተደራሽ መደረጋቸውን በመግለጽ፤ ከ20 ሚሊየን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል።

ይህም ለምግብ ሉዓላዊነት መረጋገጥ ዓይነተኛ ሚና ከመጫወቱም ባለፈ ሀገራዊ የማምረት አቅም እያደገ መምጣቱን አመላካች ነው ብለዋል።

የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ባህል እየሆነ መምጣቱን ገልጸው፤ ለዚህ ውጤት መገኘት በየደረጃው ያለው የዘርፉ አመራር ቁርጠኝነት ትልቅ ሚና መጫወቱን አንስተዋል።

በሌማት ትሩፋት ኤኒሼቲቭ የወተትና የእንቁላል ምርትን በማሳደግ አመርቂ ውጤቶች እየተገኙበት መሆኑን ተናግረዋል።

ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የደን ሽፋንን ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ከፍ እንዲል ማድረግ መቻሉን ገልጸው፤ ይህ የተፋስስ ልማትም ለወጣቶች እና ሴቶች ሰፋፊ የስራ ዕድል በመፍጠር ትልቅ ውጤት የተገኘበት መሆኑን አብራርተዋል።

እንደ ሚኒስትር ዴኤታዋ ገለጻ፤ ወደ ውጭ ከተላኩ የግብርና ምርቶች 4 ነጥብ 55 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል።

ከዚህ ውስጥ 3 ነጥብ 1 በሊዮን ዶላሩ የተገኘው ከቡና መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህ ደግሞ አረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር የላቀ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።

በቀጣዩ በጀት ዓመት በግብርናው ዘርፍ የላቀ ውጤት ለማምጣት ከግብዓት አቅርቦት፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በተሻለ መልኩ ለመተግበር መረባረብ አለብን ብለዋል።

የዛሬው የግምገማ መድረክም የባለፈው ዓመት አፈጻጸም ላይ በመወያየት ለተሻለ ስኬት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑንም ተናግረዋል።

በመድረኩ የክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በበጀት አመቱ ወደ ውጭ ከተላኩ የግብርና ምርቶች 4 ነጥብ 55 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱ ይታወሳል፡፡
ምንጭ፦ ኢ.ዜ.አ

02/09/2026
የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ከግብርና ባለስልጣን ጋር በዲጂታል ሽግግር  ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አደረገ****የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን አመራሮች ከኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ጋር በዲ...
01/09/2026

የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን ከግብርና ባለስልጣን ጋር በዲጂታል ሽግግር ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አደረገ
****
የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን አመራሮች ከኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ጋር በዲጂታል ቴክኖሎጂ፣ ተቋማዊ አሠራርና የአገልግሎት ሽግግር ዙሪያ የልምድ ልውውጥ አድርገዋል።

በልምድ ልውውጡ የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሂደትና ከማኑዋል አሠራር ወደ ዲጂታል አገልግሎት የተደረገው ሽግግር ቀርቧል።

የባለስልጣኑ የአይሲቲ ዳይሬክተር አቶ መርሃዊ ክብሩ እንደገለጹት፣ ተቋሙ የ2030 የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫን በመከተል የተለያዩ የሶፍትዌር ፕላትፎርሞችን በመጠቀም ለተጠቃሚዎች ዲጂታል አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

ቀደም ሲል በማኑዋል ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶች ለተጠቃሚዎች የጊዜና የገንዘብ ወጪን ከማብዛታቸው በተጨማሪ የፋይል መጥፋት፣ መረጃን በፍጥነት ማግኘት አለመቻል፣ የአገልግሎት መጓተትና ደካማ የቁጥጥር ሥርዓት የመሳሰሉ ችግሮች ይስተዋሉባቸው እንደነበር ገልፀዋል።

አሠራሩ ለብልሹ አሠራርና ለሙስና ተጋላጭ ከመሆኑም በተጨማሪ የሀሰተኛ ማስረጃ መበራከት ችግር እንደነበረው ተመላክቷል።

በአንፃሩ ዲጂታል ሽግግሩ በርካታ መዝገቦችን ዲጂታል በማድረግና አገልግሎቶችን በፕላትፎርሞች በማደራጀት ፋይሎችን በቀላሉ ማግኘትና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንዲቻል አድርጓል ብለዋል።

የዲጂታላይዜሽን ሂደቱ በአንድ ጊዜ የተከናወነ ሳይሆን በደረጃዎች የተተገበረ ሲሆን፣ አገልግሎቶችን መለየት፣ ለዲጂታል አሠራር ማዘጋጀት፣ ተገቢውን ፕላትፎርም መለየትና መተግበር ዋና የሂደቱ ክፍሎች መሆናቸው ተብራርቷል።

አስቀድመው የተቋቋሙ የመንግሥት ዲጂታል ፕላትፎርሞችን ከመጠቀምና ከማገናኘት በተጨማሪ አስፈላጊ ሆነው የተገኙ ሶፍትዌሮችም በተቋሙ የማልማት ሥራ እንደተከናወነ ተጠቁሟል።

በዚህ ሂደት 462 አገልግሎቶች ተለይተው 259 ያህሉ ዲጂታል የተደረጉ ሲሆን፣ 156 አገልግሎቶች በአሁኑ ወቅት በቀጥታ እየሰሩ መሆናቸው ተገልጿል።

ይህም የአገልግሎት ፍጥነትንና ቀልጣፋነትን ከማሻሻሉም በላይ ግልፀኝነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን አስተዋፅዖ ማድረጉ ተገልጿል።

የዲጂታል ሽግግሩ በአንድ ጊዜ ሊጠናቀቅ የማይችል በመሆኑ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች ቅድሚያ በመስጠት፣ በፓይለት በመጀመርና በተግባር በመፈተሽ ቀጣይነት ባለው መልኩ ማሻሻል እንደሚገባ በልምድ ልውውጡ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን በበኩሉ በተቋማዊ አሠራርና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ እያከናወነ ላለው ሪፎርም ዲጂታል ቴክኖሎጂን ወሳኝ አቅጣጫ መሆኑን ገልጿል።

ከግብርና ባለስልጣን የተገኘው ተሞክሮም የኮሚሽኑን የዲጂታል ሽግግር ሂደት ለማፋጠን፣ አገልግሎቶችን ቀልጣፋና ግልፀኛ ለማድረግ እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር ጠቃሚ ግብዓት እንደሚሆን ተጠቁሟል።

ለኮሚሽኑ ሰራተኞች በሻማ እና ሳሙና አሰራር ላይ ለ2 ቀናት ስልጠና ተሰጠ*****የኢትዮጵያ  ኅብረት ሥራ ኮሚሽን የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ አስተባባሪነት የኮ...
01/09/2026

ለኮሚሽኑ ሰራተኞች በሻማ እና ሳሙና አሰራር ላይ ለ2 ቀናት ስልጠና ተሰጠ
*****
የኢትዮጵያ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ አስተባባሪነት የኮሚሽኑ ሰራተኞች በእረፍት ግዜያቸው ተጨማሪ ስራ በመስራት ኑሯቸውን መደጎም እንዲችሉ ለ2 ቀናት በሻማ እና ሳሙና አሰራር ላይ ስልጠና ሰጥቷል።

በስልጠናው ላይ በመገኘት ምክትል ኮሚሽነር አቶ አብዱ ሙመድ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የተሰጠው ስልጠና የመንግስት ሰራተኞች በትርፍ ግዜያቸው በመስራት ኑራቸውን እንዲደጉሙ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

ስልጠናው በዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ያሉት ምክትል ኮሚሽነር፣ የሰራተኛውን ክፍተት መሰረት ያደረጉ ችግር ፈቺ ስልጠናዎች ሊበረታቱ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የኮሚሽኑ የሥራ አመራር መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳሬቦ ቡሴር በበኩላቸው ስልጠናውን የወሰዱ ሰራተኞች በፍጥነት ወደስራ በመግባት ለሌሎች ሞዴል ሆነው መውጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሃመልማል ክብሬ በበኩላቸው ስለጠናው ለ45 ሠራተኞች መሰጠቱን ጠቁመው በቀጣይም ማምረቻ ማሽኑን በመግዛት እና ሰራተኞች በእረፍት ቀናቸዉ እንዲያመርቱ የማስቻል ስራዎች እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

የተመረተውን ምርትም ከኅብረት ሥራ ማኅበራት ጋር የገበያ ትስስር በመፍጠር የማጠናከር ስራዎችም እንደሚሰሩም ጨምረው ተናግረዋል።



------
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ስለኅብረት ሥራ ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት👇

✅ ዩቲዩብ፦https://www.youtube.com/
**
✅ ቴሌግራም፦https://t.me/ethiocoopnews
**
✅ ትዊተር (X)፦https://x.com/Ecccoop
**
✅ ፌስቡክ፦http://facebook.com/EthiopianCooperativeCommission
**
✅ ድረ-ገጽ፦ www.fca.gov.et

Address

Bole Road
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Cooperative Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Cooperative Commission:

Shortcuts

Share