Ethiopian Federal Police

Ethiopian Federal Police በጀግንነት መጠበቅ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል ! Protect With Courage; Serve with Compassion!

We strive to build a safe, secure, and peaceful environment where all people in Ethiopia can live with confidence and dignity.

የፀጥታ ኃይሉ የህዝብን ሰላም ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኑ ተገለጸ ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠አሰኮ፣ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ...
01/09/2026

የፀጥታ ኃይሉ የህዝብን ሰላም ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆኑ ተገለጸ ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
አሰኮ፣ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፦ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ልዩ ፀረ-ሽብር ኮማንዶ አዛዥ ኮማንደር ኢብራሂም መሀመድ በምስራቅ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ከሕዝብ ጋር በተካሄደ የሰላም ኮንፈረንስ ላይ እንደገለፁት የፀጥታ ኃይሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ የህዝቡን ሰላም በጀግንነት ለማስከበር ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

አዛዡ ልዩ ፀረ-ሽብር ኮማንዶ ከሀገር መከላከያ ሠራዊትና ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት እያካሄደ ባለው ኦፕሬሽን በኦሮሚያ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ፀረ-ሰላም ኃይሎችን ለማፅዳት የጀመረውን ኦፕሬሽን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

አያይዘውም የኢትዮጵያ ህዝብ የሃይማኖትና የቋንቋ ልዩነቶች ሳይገድቡት ከልዩነት ይልቅ በአንድነት፣ በፍቅር፣ እርስ በእርስ በመከባበርና በመተባበር ለሺህ ዓመታት አብሮ የኖረበት እሴት ያለው ሕዝብ በመሆኑ የትኛውም አካል ሰላሙንና ደህንነቱን ሊያናጋው እንደማይችል ገልፀዋል።

ማንኛውንም የልዩነት ጥያቄ በኃይል ሳይሆን በውይይትና በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንደሚገባ ያሳሰቡት የልዩ ፀረ-ሽብር ኮማንዶ አዛዥ በፀረ-ሰላም ኃይሎች ተደልለውና ተገፋፍተው ወደ ጥፋት የገቡ ግለሰቦች ድርጊታቸው ሕዝብንና ሀገርን የሚጎዳ መሆኑን ተገንዝበው በፍጥነት ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል።

የአሰኮ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጋቢ ጋልቹ በበኩላቸው የፀጥታ አካላት ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ባከናወኑት የፀጥታ ማስከበር ተግባር በአካባቢው የነበረውን ስጋት በመቅረፍ አበረታች ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልፀዋል።

በምርጫ ወቅት ጠላት በአሰኮ ወረዳ የምርጫውን ሂደት ለማስተጓጎልና አካባቢውን ለማወክ ያደረገውን ጥረት ህዝቡና የፀጥታ ኃይሎች ባደረጉት ጠንካራ ቅንጅት በማክሸፋቸው ምርጫውም በሰላማዊ ሁኔታ በስኬት መጠናቀቁን አብራርተዋል።

በአሁኑ ወቅት በተካሄደው የተቀናጀ ኦኘሬሽን በአሰኮ ወረዳ አንፃራዊ ሰላም መስፈኑንና ይህም በዞንና በክልል ደረጃ ትልቅ ትኩረት ያገኘ ሥራ መሆኑን ያነሱት አስተዳዳሪው የወረዳው ሰላም ሙሉ በሙሉ ወደነበረበት እስኪመለስ የህብረተሰቡ እና የፀጥታ ኃይሉ ቅንጅት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

‎The Ethiopian Federal Police is undergoing profound reforms to become a model law enforcement agency in Ethiopia and ac...
31/08/2026

‎The Ethiopian Federal Police is undergoing profound reforms to become a model law enforcement agency in Ethiopia and across Africa. By scaling up its crime prevention capacity and organizing the General Department to comprise 87% of the total police force, the institution operates efficiently in alignment with contemporary demands. Grounded in intelligence-led and community policing principles, it continues to register remarkable achievements.

‎​The General Department leverages an integrated system combining secure digital police radio communications, CCTV, the Citizen Engagement Application (EFPApp), the 991 toll-free emergency call line, drone surveillance, and the Command and Control Center to execute operations seamlessly.
‎Furthermore, specialized units such as the Special Anti-Terrorism Commando (SAT) and the Special Program for Embassy Augmentation and Response (SPEAR) utilize advanced tactical gear and rigorous protocols to safeguard national security.

‎​To protect the national economy and public welfare, concerted operations against illicit trade and contraband between the 2013 and 2017 E.C. operational years successfully seized import-export goods valued at over 53 billion Birr. Alongside intercepting illicit financial flows, curbing artificial price inflation, and rescuing youths from human trafficking networks, the institution continues to uphold public safety and reinforce national peace.
More on

https://www.federalpolice.gov.et/en/federal/police/news

‎የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ሞዴል የሕግ አስከባሪ ተቋም መሆን የሚያስችለውን ሥር-ነቀል ሪፎርም እያካሄደ ይገኛል። በዚህም የወንጀል መከላከል አቅሙን ወቅቱን በሚመጥ...
31/08/2026

‎የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ሞዴል የሕግ አስከባሪ ተቋም መሆን የሚያስችለውን ሥር-ነቀል ሪፎርም እያካሄደ ይገኛል። በዚህም የወንጀል መከላከል አቅሙን ወቅቱን በሚመጥን ሁኔታ በማሳደግ የአጠቃላይ ፖሊስ ሠራዊቱን 87 በመቶ የሰው ኃይል በመያዝ የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያን እንደገና በአዲስ መልክ አደራጅቷል። መረጃ መር እና ማህበረሰብ አቀፍ የወንጀል መከላከል መርህን በመከተልም በርካታ ስኬቶችን እያስመዘገበ ይገኛል።

‎ጠቅላይ መምሪያው ደህንነቱ ከተጠበቀ የፖሊስ ዲጂታል ሬዲዮ ግንኙነት፣ ከሲሲቲቪ፣ ከዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp)፣ ከ991 ነፃ የስልክ መስመር፣ ከድሮኖች ቅኝት እና ከሰው አልባ ስማርት የፖሊስ ጣቢያ በተቀናጀ ስርዓት የተሰበሰበውን አስተማማኝ መረጃ በመጠቀም የወንጀል መከላከል ሥራውን በብቃት እያከናወነ ይገኛል። እንዲሁም እንደ ልዩ ፀረ-ሽብር ኮማንዶ (SAT) እና ስፒር (SPEAR) ያሉ በዘመናዊ ትጥቅና በሰለጠነ የሰው ኃይል የተደራጁ ክፍሎች የሀገርን ሰላም በፅኑ እያስከበሩ ይገኛሉ።

‎መምሪያው ሕገ-ወጥ ንግድንና ኮንትሮባንድን ለመቆጣጠር ባደረገው ርብርብ ከ2013 እስከ 2017 ዓ.ም ብቻ ከ53 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የወጪና ገቢ ኮንትሮባንድ ዕቃዎችን መያዝ ችሏል። በተጨማሪም ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን በመከላከል፣ የኑሮ ውድነትን ለማባባስ የሚሞክሩ አላስፈላጊ ንብረት አከማቾችን በቁጥጥር ሥር በማዋል እና ወጣቶችን ከሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር በመታደግ ለሀገር ኢኮኖሚ መረጋጋት እና የዜጎች ደህንነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

🔗ሙሉ መረጃውን ለማንበብ https://www.federalpolice.gov.et/am/federal/police/news ሊንኩን ይጫኑ

30/08/2026
የኦሜድላ ስፖርት ክለብ አትሌት ኮንስታብል አዲሱ ጎበና በሲድኒ ማራቶን አዲስ ክብረ ወሰን በማስመዝገብ አሸነፈ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ....
30/08/2026

የኦሜድላ ስፖርት ክለብ አትሌት ኮንስታብል አዲሱ ጎበና በሲድኒ ማራቶን አዲስ ክብረ ወሰን በማስመዝገብ አሸነፈ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፦ ​የኦሜድላ ስፖርት ክለብ አትሌት የሆነው ኮንስታብል አዲሱ ጎበና በሲድኒ ማራቶን ውድድር አዲስ የቦታውን ክብረ ወሰን በማስመዝገብ አስደናቂ ድል ተቀዳጅቷል።

​ለ24ኛ ጊዜ በተካሄደው በዚህ ታላቅ የማራቶን ውድድር አትሌት ኮንስታብል አዲሱ ጎበና ርቀቱን በ2 ሰዓት ከ04 ደቂቃ ከ42 ሰከንድ በማጠናቀቅ ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቋል።

​አትሌቱ ያስመዘገበው ሰዓት የውድድሩን የቆየ የቦታ ክብረ ወሰን ማሻሻል መቻሉን ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ለአሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው 2ኛው ዙር የ''ጽናት 21'' ስልጠና ተጠናቀቀ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ ሰንዳፋ፤ ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፦የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለአ...
29/08/2026

ለአሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው 2ኛው ዙር የ''ጽናት 21'' ስልጠና ተጠናቀቀ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ ሰንዳፋ፤ ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፦የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለአመራሮችና ለፈጻሚ አካላት ሲሰጥ የቆየውን የ2ኛ ዙር የ''ጽናት 21'' ዘርፈ ብዙ የአቅም ግንባታ ስልጠና ያጠናቀቁትን አሰልጣኞች በድምቀት አስመርቋል።

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ክቡር ፕሬዝዳንት ታምራት ሙሉጌታ (ዶ/ር) በስልጠናው ማጠቃለያ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው በሰጡት የሥራ መመሪያ የፖሊስ ሥራ ዘርፈ ብዙ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት፣ ጥራት ያለው ፖሊሳዊ ትምህርትና ስልጠና ለመስጠት እንዲሁም በፖሊሳዊ ሙያ የታነፀ መኮንን ለማፍራት ስልጠናው አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

ክቡር ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ስልጠና ያጠናቀቁት የመስክ አሰልጣኞች ፖሊሳዊ ስብዕና የሁሉም መሠረት መሆኑን በመገንዘብ ለሚያሰለጥኗቸው ሰልጣኞች አርአያ በመሆን ዘመናዊ የኢትዮጵያ ፖሊስን ለመገንባት እና ዩኒቨርሲቲው የያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል። መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ስልጠናውን አስመልክተው ሪፖርት ያቀረቡት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የወታደራዊ ስልቶችና አካል ብቃት ስልጠና ማዕከል መምሪያ የቴክኒክና ጦር መሣሪያ ዋና ክፍል ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ክንዴ አዳነ ስልጠናው ከዋናው ግቢና ከሁሉም ካምፓሶች ለተውጣጡ አሰልጣኞች የተሰጠ መሆኑን አስረድተዋል። አሰልጣኞች በቀጥታ ከሰልጣኞች ጋር የሚገናኙ በመሆናቸው ስልጠናው በተዘዋዋሪ በሰልጣኞች ዘንድ የዕውቀት፣ የክህሎትና የባህሪ ለውጥ እንዲመጣ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

የስልጠናው ዋነኛ ዓላማ በፖሊሳዊ የመስክ ስልጠናዎችና ስልቶች ላይ የሚታዩ ጥቃቅን ልዩነቶችን ማጥበብ መሆኑንም ተናግረዋል።

ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ፖሊሳዊ ስብዕናና ሥነ ምግባር፣ የአሰለጣጠን ዘዴና ተግባቦት፣ ሀገር ወዳድነት እና የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች አጠባበቅ እንዲሁም ሌሎች ስልጠናዎችን በብቃትና በተሟላ ዲሲፕሊን ያጠናቀቁ ስለሆነ ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

የቅጥር ማስታወቂያየኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2019 በጀት ዓመት የተቋሙን የሰው ኃይል ለማጠናከር በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰብና ሕዝቦች፣ የጾታ ተ...
28/08/2026

የቅጥር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2019 በጀት ዓመት የተቋሙን የሰው ኃይል ለማጠናከር በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኙ ብሔር ብሔረሰብና ሕዝቦች፣ የጾታ ተዋፅዖን ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ ተመልምለው በተቋሙ ባሉት ልዩ ልዩ የሥራ ዘርፎች ተመድበው ማገልገል የሚፈልጉ ዕጩ ፖሊሶችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል።

ዕጩ ተመልማዮቹ ምልመላው ተጠናቆ ወደ ኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ሥልጠና ማዕከል ገብተው ሥልጠና ከመጀመራቸው በፊት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 720/2004 እና ደንብ ቁጥር 268/2005 በሚያዘው መሠረት የ7 ዓመት የሥራ ውል ግዴታ በመግባት በማሰልጠኛ ትምህርት ቤቱ አማካይነት የሚሰጣቸውን ሥልጠና በሚገባ በመከታተል ማጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በሥልጠና ቆይታ ጊዜያቶችም በማሠልጠኛ ትምህርት ቤቱ በኩል የምግብ፣ የመኝታ፣ የሕክምና እና ለሥልጠናው የሚያስፈልጉ የአልባሳት፣ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችና የኪስ ገንዘብ ይሰጣል።

ሥልጠናው ሲጠናቀቅም እያንዳንዱ ተመራቂ በተቋሙ የደመወዝ ስኬል መሰረት ወርሃዊ ደመወዝና የቀለብ ሂሳብ የሚከፈለው ሆኖ በተቋሙ ልዩ ልዩ የስራ አልባሳት፣ ነፃ የሕክምና አገልግሎት፣ በካምፕ የጋራ መኖሪያ ቤት እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎት ያገኛሉ።

ተመርቀው ፖሊሳዊ የሙያ አገልግሎት በሚያበረክቱባቸው ጊዜያትም በተቋሙ ውስጥ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ማቋቋሚያ አዋጅ፣ ደንብ እና የስልጠና መመሪያዎች መሠረት በሚወጡ መመዘኛዎች አማካኝነት በልዩ ልዩ የትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራሞች በመወዳደር ተጠቃሚ የመሆን ሠፊ ዕድል የሚጠብቃቸው መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በደስታ ይገለፃል።

የምልመላ መስፈርት (መመዘኛ)

1. ዜግነት ኢትዮጵያዊ የሆነ/የሆነች፣

2. ለሕገ-መንግስንቱና ለሀገሪቱ ሕጎች ተገዥና ታማኝ የሆነ/የሆነች፣

3. ከማናቸውም ደባል ሱሶች የፀዳ/የፀዳች እና መልካም ስነ-ምግባር ያለው/ያላት፣

4. በሚመለመልበት አካባቢ ነዋሪ ስለመሆኑ የቀበሌ መታወቂያ ወይም የፋይዳ መታወቂያ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣

5. ከሚኖርበት ቀበሌ አስተዳደር፣ ከአካባቢው ፖሊስ እና ከተማረበት ትምህርት ቤት የተዘጋጁ ቅፆችን በማስሞላት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፤

6. በብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም በሃይማኖት እኩልነት የሚያምን/የምታምን፣

7. ለፖሊስነት የሚያበቃ ሙሉ ጤናማ መሆኑን/መሆኗን በህክምና የተረጋገጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣

8. ዕድሜው/ዋ ከ18 እስከ 25 ዓመት ያላነሰና ያልበለጠ/ያልበለጠች፣

9. የማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆነ/ያልሆነች፣

10. የትምህርት ደረጃ 10ኛ ክፍል እና በላይ የሆነ/የሆነች እንዲሁም ትምህርት ያጠናቀቀበት ካርድ ዋናውንና የማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣

11. ብዝሃነትንና አካታችነትን ለማረጋገጥ ሲባል ያልተካተቱና አነስተኛ ቁጥር ባለባቸው ብሔሮች አካባቢ ለሚመለመሉ ወጣቶች ቢያንስ 6ኛ ክፍል እና በላይ የሆነ/የሆነች፣

12. ቁመት ለወንድ 1.65 ሜትር በላይ የሆነ፣ ለሴት 1.60 ሜትር በላይ የሆነች፣

13. የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 720/2004 እና ደንብ ቁጥር 268/2005 በተደነገገው መሠረት የ7 ዓመት የሥራ ውል ግዴታ በመግባት ሥልጠናው ሲጠናቀቅ በየትኛውም የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ተቋም የሥራ አከባቢ ተመድቦ/ተመድባ ለመሥራት ፈቃደኛ የሆነ/የሆነች፣

14. ከአሁን በፊት በወንጀል ተከሶ ያልተቀጣ/ያልተቀጣች ወይም የወንጀል ሪከርድ የሌለበት/የሌለባት የአሻራ ምርመራ ለማድረግ ፍቃደኛ የሆነ/የሆነች፣

15. ከአሁን በፊት በማንኛውም የፖሊስ እና የመከላከያ ሰራዊት ተቋም ሥልጠና ያልተሳተፈ/ያልተሳተፈች ወይም በአባልነት ተቀጥሮ ያልሰራ/ያልሰራች፤

16. ያላገባ እና ያልወለደ ወይም ያላገባች እና ያልወለደች፣

ማሳሰቢያ፡- ማንኛውም ዕጩ ተመልማይ በምዝገባ ወቅት ከላይ የተገለፁት መመዘኛዎች እንደተጠበቁ ሆኖ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ይዞ በመቅረብ መመዝገብ ይኖርበታል፡፡

1) የትምህርት ማስረጃ ዋናውንና የማይመለስ 1 ፎቶ ኮፒ፣

2) ከ2 ዓመት በላይ ነዋሪነትን የሚያመለክት የቀበሌ ነዋሪነት መታወቂያ ወይም የፋይዳ መታወቂያ ይዞ መቅረብና መመዝገብ ይጠበቅበታል፣

3) የተመልማዩን ማንነት አጠቃላይ ሁኔታ ለመገንዘብ እንዲያስችል ታስቦ በሥልጠና ማዕከሉ አማካይነት የተዘጋጀውን ፎርም ከምዝገባ ጣቢያው በመቀበል የመጨረሻ አመት ካጠናቀቀበት ወይም ካጠናቀቀችበት ትምህርት ቤት፣ ከመኖሪያ ቀበሌና ከአከባቢው የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ጽ/ቤት ቀርቦ ወይም ቀርባ የማስሞላትና በተጠቀሰው የቀን ገደብ መሰረት ለምልመላ ጣቢያው አስቀድሞ ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

4) ሴት ተወዳዳሪዎች ይበረታታሉ።
ማንኛውም ምልምል ከ500 ብር በላይ፣ ወርቅ፣ የተለያዩ ስለታማ ነገሮችን፣ ምግብ ነክ ነገሮች እና ከሁለት ቅያሪ ልብስ በላይ ይዞ ወደ ማሰልጠኛው ማዕከል መግባት የተከለከለ ነው፡፡

የምዝገባ ጊዜው ከጳጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 18 ቀን 2019 ዓ.ም ባሉት ተከታታይ የሥራ ቀናት የሚካሄድ ሲሆን፣ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በየክልሉ በሚገኙ ዞኖች፣ ወረዳዎች እና በምልመላ ጣቢያዎች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች የ27ኛ ዙር መደበኛ ፖሊስ ምልመላ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠አዲስ አበባ፣ ነሐሴ...
28/08/2026

የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች የ27ኛ ዙር መደበኛ ፖሊስ ምልመላ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢፌፖሚ)፦ የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የ27ኛ ዙር መደበኛ ፖሊስ ምልመላ ዕቅድ ላይ በዋና መሥሪያ ቤት ውይይት አካሂደዋል፡፡

በውይይቱ ዘመኑን የዋጀ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መጠቀም የሚችልና የማድረግ አቅሙ ያደገ ኢትዮጵያን የሚመስል የፖሊስ ሠራዊት የመገንባት ጉዞን በስኬት ለማስቀጠል ከሁሉም ክልሎች ሕብረ-ብሔራዊ ተዋፅኦንና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ያደረገ የተሻለ የትምህርት ዝግጅት ያላቸውን ወጣቶች በመመልመል፣ በማሰልጠንና ስምሪት በመስጠት የተቋሙን የሰው ኃይል ፍላጎት ማሟላት አስፈላጊ መሆኑ ተነስቷል፡፡

በማሰልጠኛ ተቋማት ብዝሃነትን፣ አካታችነትን እንዲሁም ቁጥርና ጥራትን ባገናዘበ መልኩ፤ የተሟላ ጤንነትና የአካል ብቃት ያላቸው፤ የሚሰጣቸውን መሠረታዊ ፖሊሳዊ ሥልጠና በብቃት ወስደው ሀገራቸውን በፖሊስ ሙያ ለማገልገል የተዘጋጁ፣ ለሕገ-መንግሥቱ ታማኝ የሆኑ፣ ከዘር፣ ከሃይማኖት፣ ከፖለቲካና ከሌብነት የፀዱ፣ ማኅበረሰቡን በእኩልነት የሚያገለግሉ እና በሥነ-ምግባራቸውም የተመሰገኑ ወጣቶች ተመልምለው ወደ ማሰልጠኛ እንዲገቡ በከፍተኛ ትኩረት እየተሠራ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የ27ኛ ዙር መደበኛ ምልምል ፖሊሶችን በጥራት ለመመልመልና ወደ ማሰልጠኛ ለማስገባት የተዘጋጀው ዕቅድ ከክልል አስተዳደር አካላት ጋር በመቀናጀት ለመተግበር አስፈላጊው ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን የክልል ፖሊስና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎችም ለምልመላው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ትብብርና ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ተቀጥረው ለማገልገል መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶች፣ በየክልሉ በሚገኙ ዞኖች፣ ወረዳዎችና የምልመላ ጣቢያዎች ከጳጕሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምረው መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡

"የኢትዮጵያ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ሀገራችንን ሠላም እና ደህንነት ማስጠበቅ  የሚያስችል ተቋማዊ አቅም ገንብተዋል" የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠...
28/08/2026

"የኢትዮጵያ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ሀገራችንን ሠላም እና ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ተቋማዊ አቅም ገንብተዋል" የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢፌፖሚ)፦የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የኢትዮጵያ የፀጥታና ደህንነት ተቋማት ሀገራችንን ሠላም እና ደህንነት ማስጠበቅ የሚያስችል ተቋማዊ አቅም ገንብተዋል ያሉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮችና የሰላምና ፀጥታ ኃላፊዎች ሀገራዊ የጋራ የፀጥታ መድረክ ማጠቃለያ ላይ ነው፡፡

የፀጥታ ኃይሉ ከውስጥና ከውጭ በሽብርተኞች እና በፅንፈኛ ቡድኖች የተጠነሰሱ በርካታ ሴራዎችን በማክሸፍ ኢትዮጵያ የማትበገር ሀገር መሆኗን በተግባር ያረጋገጠበት ጊዜ እንደነበር ክቡር ኮሚሽነር ጀነራሉ ተናግረዋል፡፡

የፀጥታ ኃይሉ በዘረጋው ቅንጅታዊ አሠራር ሀገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም-አቀፋዊ ሁነቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ ማድረጉን ያስታወሱት ጠቅላይ አዛዡ በቅርቡ በሀገራችን የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር በሰላም እንዲጠናቀቅ የፀጥታ አካላት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውንም ገልፀዋል።

አያይዘውም በቀጣይ በሀገራችን የሚከበሩ የአዲስ ዓመት፣ የመስቀል፣ የእሬቻ በዓላት እና የመንግስት ምስረታ ሁነቶችም በስኬት እንዲጠናቀቁ ግልፅ የሆነ ስትራቴጂካዊ እቅድ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል::

በሌላ በኩል የሀገራችንን ማንሠራራት የማይፈልጉ ባንዳዎችና ባዳዎች የሕዝቡን አንድነት ለመሸርሸር፣ የብሔርና የሃይማኖት ግጭቶችን ለማስነሳት፣ እንዲሁም የሐሰት መረጃዎችንና ፕሮፓጋንዳዎችን በማሰራጨት የሀገራችንን ገጽታ ለማበላሸት ቢጥሩም የፀጥታ ኃይሉ ሕዝቡን በማሳተፍ እኩይ ዓላማቸውን እያከሸፈ የሕግ የበላይነትን የማስከበር ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Federal Police posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Federal Police:

Shortcuts

Share