FDRE Defense Engineering Industry Corporation

FDRE Defense Engineering Industry Corporation ራዕይ (Vision)
• የወታደራዊና የደህንነት ቴክኖልጂ የበላይነት?

የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጀ አህመድ ሀምዛ በተቋሙ ውስጥ ለሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ማእረግ የማልበስ ስነስረአት አከናወኑ፡፡የማእረግ ሹመት አሰ...
04/02/2022

የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጀ አህመድ ሀምዛ በተቋሙ ውስጥ ለሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ማእረግ የማልበስ ስነስረአት አከናወኑ፡፡
የማእረግ ሹመት አሰጣጥ ላይ ንግግር ያደረጉት ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጀ አህመድ ሀምዛ የዛሬው ሹመት የተሰጣቹ የኢንዱስትሪያችን የሰራዊት አባላት በነበራቹ ሀላፊነት፣ባስመዘገባቹት አፈጻፀም እና በቀጣይም የላቀ ውጤት ያስመዘግባሉ በሚል ውጤት መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡

የእቅድ አፈጻጸም ተገመገመየ 2014 ዓ.ም የተጀመረው የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ኮርፖሬሽንየ6 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የሁለተኛ ሩብ አመት እቅድ ክለሳ ውይይት ሲገመገም ...
25/01/2022

የእቅድ አፈጻጸም ተገመገመ
የ 2014 ዓ.ም የተጀመረው የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ኮርፖሬሽንየ6 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የሁለተኛ ሩብ አመት እቅድ ክለሳ ውይይት ሲገመገም ቆይቶ ተጠናቀቀ፡፡
ለኮርፖሬሽኑ ተጠሪ የሆኑ ጋፋት አርማመንት ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን፤ሆሚቾ አሙኔሽን ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን፤ብራና ማተሚያ ድርጅት ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡
በሁሉም ተጠሪ ክፍሎች መከናወን ሲገባቸው ያልተከናወኑ ስራዎች ምክንያቶቹ የተገመገሙ ሲሆን በሁለተኛው ሩብ አመት ክለሳ ተደረጎ እንዲፈጸሙ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

እንኳን ለብርሀኑ ልደቱ በሰላም አደረሳቹ።የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ኮርፖሬሽን ለ ክርስትና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የኢንዳስትሪ ሰራተኞች መልካም በአል እንዲሆንላቹ ይመኛል።
07/01/2022

እንኳን ለብርሀኑ ልደቱ በሰላም አደረሳቹ።
የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ኮርፖሬሽን ለ ክርስትና እምነት ተከታይ ለሆናችሁ የኢንዳስትሪ ሰራተኞች መልካም በአል እንዲሆንላቹ ይመኛል።

ኅዳር 28 ቀን 2014«አሸባሪው ቡድንን እና ባንዳን መንቀል ያለብን ሰርገው ካሉበት ቦታ ብቻ ሳይሆን ከምንጩ ነው » ሜ/ጄ አህመድ ሀምዛ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዳይሬ...
10/12/2021

ኅዳር 28 ቀን 2014
«አሸባሪው ቡድንን እና ባንዳን መንቀል ያለብን ሰርገው ካሉበት ቦታ ብቻ ሳይሆን ከምንጩ ነው » ሜ/ጄ አህመድ ሀምዛ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዳይሬክተር ፡፡
ኮርፖሬሽኑ በአለም ለ18ኛ በኢትዮጵያ ለ17ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን ባከበረበት ወቅት ሜ/ጄ አህመድ ሀምዛ እንደተናገሩት ፣ ሽብርተኛው በሙስናና በራስ ወዳድነት መኖሩ ሳያንስ ሀገር ለማፍረስ ቢዘጋጅም በመላው ኢትዮጵያዊ ጥረት እየከሸፈ ሲሆን ፣ አሸባሪውን ቡድን እና ባንዳን ከምንጩ ማጥፋት አለብን ብለዋል፡፡፡
በዝግጅቱ ላይ የፌደራል ስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽንን መልዕክት ያስተላለፉት ወ/ሪት ሳምራዊት ተሾመ ፣ ሙስና እና ብልሹ አሰራር ካለ ሠላምና መረጋጋት አይኖርም ፡፡ ሙስና ጠንካራ የሥራ ባህል እንዳይኖር ያደርጋል ፡፡ ሀገራችን በውስጥና በውጭ የተጋረጠባትን የህልውና አደጋ በፅናት ተቋቁማ ወደ ዕድገት የምታደርገው ጉዞ በሙስናና ብልሹ አሰራር ሊደናቀፍ አይገባም ፡፡ በተለይ አመራሩ ጠንክሮ ሊሠራ ይገባል ብለዋል፡፡
ያነጋገርናቸው የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞችም ፣ ከቀድሞው ይልቅ አሁን ያለው ሀገራዊ አንድነታችን ከፍተኛ ነው ፡፡ አሸባሪውን የህወሃት ቡድንን ለማጥፋት በጋራ እንደተነሳን ሁሉ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ብሎም ለማጥፋት አንድነታችንን አጠናክረን ልንሠራ ይገባል ብለዋል፡፡
«በሥነ-ምግባር የታነፀ አመራር ከሙስና ለፀዳች ኢትዮጵያ» በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው መድረክ ዕለቱን የተመለከተና ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር ጥናታዊ ጽሑፍ ፣ ግጥም ፣ መነባነብ ፣ ድራማና ሙዚቃዎች ለታዳሚያን ቀርቧል፡

የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን    የሎጎ (የአርማ) መግለጫ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በወታደራዊና የደህንነት ቴክኖሎጂ ምርትና አገልግሎት ተመራጭናተፅእኖ ...
28/11/2021

የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን
የሎጎ (የአርማ) መግለጫ
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በወታደራዊና የደህንነት ቴክኖሎጂ ምርትና አገልግሎት ተመራጭና
ተፅእኖ ፈጣሪ ብሔራዊ አቅም መሆንን ራዕዩ አድርጎ የሚሰራ ተቋም ነው። በተጨማሪም የተቋሙ ተልዕኮ የሆኑትን
• የወታደራዊ ትጥቆችን በማምረት፣ በማደስ፣ በማሻሻል እና በማዘመን የሰራዊቱን አቅም ማሳደግና
የመከላከያን ተልዕኮ መደገፍ
• የወታደራዊና ደህንነት ቴክኖሎጂ ምርት ባለቤትነትን ማረጋገጥ የሚያስችል የምርምርና ልማት አቅም
መገንባት፤
• የወታደራዊና ደህንነት ቴክኖሎጂ ውጤት የሆኑ ምርትና አገለግሎቶች በመሽጥ የመንግስትን ስትራቴጂክ
የልማት እቅድ የሚደግፍ ሃብት ማመንጨት
• አለማቀፋዊነትን
መሰረት በማድረግ ለተቋሙ ዲዛይን የተደረገው የሎጎ (የአርማ) መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል።
ጋሻ
መከታ (ከለላ) መሆንን፣ መከላከልን፣ ሃላፊነትን፣ ቤተሰባዊንነትን፣ ራስን ሳልፎ መስጠትን፣ መጠበቅን፣ መከላከያን፣
ባህላዊ እሴትን፣ ጥንካሬን/ አይበገሬነትን፣ ደህንነትን፣ ተስፋን፣ ራዕይን፣ እምነትን ይገልፃል (ይዎክላል)።
ԜўӤёӤ ԟӞӑԶӌѰӑՁӞӑԥѻҴѰӪ ѳևѲ҃ӑ
Defense Engineering Industry Corporation



ቀስት / ጀት
እድገትን፣ ብልፅግናን፣ ፍጥነትን፣ ተደራሽነትን፣ ራእይን፣ ቀዳሚነትን፣ ተፋስን፣ የአየር ሃይልን፣ አመላካች፣
ተግባራትን(ክንውንን)፣ ጉዞን፣ ምርምርን፣ ዩሮ ስፔስን፣ አየር ሃይልን፣ እውቀትን፣ አርቆ አሳቢነትን፣ ውጤታማነትን፣
አቅምን፣ ባህላዊ እሴትን . . . ያሳያል።



የሚወነጨፉ መስመሮች
የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ኢንዱስትሪው
በዋነኝነት የሚያተኩርባቸው በከባቢ አየር እና በህዋ የሚበሩ ቴክኖሎጂዎችን እና ተጓዳኝ ስርዓቶችን የምህንድስና
/Design/፣ የማምረት /Manufacturing/ù የውህደት /Integration/፣ የድጋፍ /Support/፣ የጥገና አገልግሎት
/Maintenanceù service/ù እና ምርትን የማሻሻል /Upgrading/ù ተግባራት ናቸው። ከኢንዱስትሪው ምርቶችና
አገልግሎቶች መካከልም ፊክስድ እና ሮተሪ ክንፍ ያላቸውና በሰው እና ያለሰው የሚበሩ ቴክኖሎጂዎችን እና ተዛማጅ
ሶፍትዌሮችን ፣ የተለያዩ አይነት ተምዘግዛጊ መሳሪያዎች፣ ሮቦቲክሶች ፣ የሰው ሰራሽ ክህሎቶች፣ ምስለ እውነታ
ስርዓት(AugmentedùRealityùSystem)፣ የነጥብ መጠቆሚያ ስርዓት (LocalùPositiningùSystem)፣ የፀረ ሰው አልባ
ስርዓት (Anti-DroneùSystem)፣ የሰው እና የሰው አልባ አውሮፕላን የመሳስሉት ዘርፎች ላይ እንደሚሰራ ይታወቃል።
ይህንንም ግዙፍ የስራ ዘርፍ ሃሳብ ጠቅልሎ የያዘ ወካይ ምልክት ነው።
በአጠቃላይ የሚወነጨፉት መስመሮች፦ እድገትን፣ በጋራ (በህብረት ማደግን) ወይም መስራትን፣ ኢላማን፣
ተደራሽነትን፣ አለማቀፋዊነትን፣ ራእይን፣ ቀዳሚነትን፣ ተፋስን፣ በቴክኖሎጅ የታገዘ ጉዞን፣ ምድርን እና ሰማዩን ማካለልን፣
ምርምርን፣ ምጡቅነትን፣ ምርታማነትን፣ ፈጣን መሆንን፣ አየር ሃይልን፣ ዩሮ ስፔስን፣ አርቆ አሳቢነትን፣ እቅምን . . .
ያሳያል።
በመጨረሻም በ 450 (አርባ አምስት ዲግሪ አንግል) የሚወነጨፉ መስመሮች በ Diagonal line አቀራረብ
የተቀመጡ ሲሆኑ ትርጓሜውም፡- ኢላማን (ግብ መምታትን)፣ አቅጣጫን፣ በጋራ መስራትን (Teamwork)፣
ተደራሽነትን፣ ለውጥን፣ ምጡቅነትን፣ ምርምርን፣ ፈጣን የአስራር መንገድን (ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠትን)፣ የተቋሙን
ራዕይ እና ተልዕኮን፣ እንቅስቃሴን (Movement)፣ ግንኙነትን፣ አለማቀፋዊነትን፣ ጥረትን (effort)፣ ልምድ ልውውጥን፣
ከፍታን፣ ለለውጥ መጓዝን፣ ቁርጠኝነትን፣ ሚዛናዊነትና ፍትሃዊነትን፣ እኩልነትን፣ ህይወትን እና ስኬታማነትን ጠቅልሎ
የያዘ ምልክት ነው፡፡
የቀለማት ትርጓሜ
ሰማያዊ
ሰማያዊ የመጀመሪያ ደረጃ ቀለም ሲሆን ሌሎች ቀለማቶች ተቀይጠው የማይገኝ (unique) ቀለም ነው። ሰማያዊ ቀለም፦
እርጋታን፣ ትኩረት መስጠትን፣ ተደራሽነትን፣ ምሉዕነትን፣ ህዋን፣ ተደራሽነትን፣ ምጡቅነትን፣ ልዩ (unique)፣
አለማቀፋዊነትን፣ ጥልቀትን ፣ ቻይነትን ፣ ቴክኖሎጂን፣ ጥበብን (wisdom)፣ ምጥቀትን፣ የምናባዊነትን፣ ተአማኒነት፣
ልበሙሉነትን የሚወክል ቀለም ነው። በተጨማሪም ዩሮ ስፔስን፣ ኤር ፎርስን፣ ቴክኖሎጅን፣ ኢንጂነሪንግን፣ ኢንዱስትሪን
ይወክላል።
የበሰለ አረንጓዴ
ልምላሜ፣ military፣ የምድር ሃይልን፣ ወታደራዊ አልባሳትን፣ ብስለትን (maturity)፣ መድረስን፣ ተፈጥሮን፣
ሚዛናዊነትን፣ ሰላማዊነትን፣ ምጡቅ፣ መልካም እድልን፣ ጤንነትን፣ ህይወትን፣ ለውጥን . . . ያሳያል።

ነጭ
ሰላምን፣ ነፃነትን፣ ግልፅነትን፣ እንከን የለሽነትን፣ እረፍትን፣ ንፅህናን፣ መንገድን፣ ቅንነትን እና መልካም ነገሮችን ጠቅልሎ
የያዘ ትርጉመ ብዙ ቀለም ነው

በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ በመከላከያ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሸላዝድ ሆስፒታል በመገኘት ለኢትዮጵያ ክብርና ሉአላዊነት አቻ የማይገኝለት ዋጋ የከፈሉ የኢትዮጵያዊያን...
21/11/2021

በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ በመከላከያ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሸላዝድ ሆስፒታል በመገኘት ለኢትዮጵያ ክብርና ሉአላዊነት አቻ የማይገኝለት ዋጋ የከፈሉ የኢትዮጵያዊያን የቁርጥ ቀን ደራሽ ልጆች የመከላከያ ሰራዊት አባላት 9.999.173.66/ዘጠኝ ሚሊየን ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ መቶ ሰባ ሶስት ብር ከ 66 ሳነቲም/ ግምት ያለው 13,806 /አስራ ሶስት ሺህ ስምንት መቶ ስድስት/ ብርድልብስና እና 5000 / አምስት ሺህ/አንሶላ ድጋፍ አደረገ፡፡
ድጋፉን ያስረከቡት የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሃብት አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ ኮ/ል ተመስገን አስማማው ሀገራችን አሁን ያለችበት ወቅት ከውጭና ከሀገር ውስጥ ጫና የበዛባት ጊዜ በመሆኑ ይህንን ለመቋቋም የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ለህልውናው ዘመቻ የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ እንደሚንገኝና ድጋፉም ቀጣይነት ያለው መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የመከላከያ ጤና ዋና መምሪያ የመድሃኒት መገልገያ ህክምና መሳሪያ አቅርቦት መምሪያ ሃላፊ ብ/ጀ የሺመቤት አያለው ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው፡፡ አሸባሪው የህውሀት ቡድን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት ሌሎችም ለመከላከያ ሰራዊት የሚያደርጉትን ሁለተናዊ ድጋፊ አጠናክረው መቀጠል ይገባቸዋል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ሰንደቅ አላማ የብሄራዊ አንድነት መገለጫ የአንድ ሀገር ዜጎች ሀገራዊ ፍቅርና ብሄራዊ ስሜትን የሚገልፁበት ታሪካዊ ትስስርና ስነ ልቦናዊ አንድነትን የሚንፀባረቁበት የሀገራዊ አንድነትና ህብረት...
11/10/2021

ሰንደቅ አላማ የብሄራዊ አንድነት መገለጫ የአንድ ሀገር ዜጎች ሀገራዊ ፍቅርና ብሄራዊ ስሜትን የሚገልፁበት ታሪካዊ ትስስርና ስነ ልቦናዊ አንድነትን የሚንፀባረቁበት የሀገራዊ አንድነትና ህብረት አድማ ነው::በመሆኑም "በአዲስ ምእራፍ በተሟላ ሉአላዊነት ለሰንደቅ አላማችን ከፍታ!"በሚል መሪ ቃል ለ14ኛ ጊዜ በመላው ኢትዮጲያ ተከብሮ ውሏል::

ጥቅምት በገባ በመጀመሪያው ሳምንት ሰኞ የሚከበረው የሰንደቅ አላማ ቀን ጥቅምት 1,2014አ/ም ለ14 ጊዜ "በአዲስ ምእራፍ በተሟላ ሉአላዊነት ለሰንደቅ አላማ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በመከላከ...
11/10/2021

ጥቅምት በገባ በመጀመሪያው ሳምንት ሰኞ የሚከበረው የሰንደቅ አላማ ቀን ጥቅምት 1,2014አ/ም ለ14 ጊዜ "በአዲስ ምእራፍ በተሟላ ሉአላዊነት ለሰንደቅ አላማ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዳስትሪ ኮርፖሬሽን ተከበረ:: የዘንድሮ የሰንደቅ አላማ ቀን በአል ሚከበረው በአንድ በኩል 6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ ተካሂዶ በምርጫው ውጤት መሰረት አዲስ ፓርላማ እና የመንግስት ምስረታ በተካሄደበት ማግስት እና በኢትዮጲያ እውነተኛ ዲሞክራሲ ለመገንባት ብልፅግናን ለማምጣት አዲስ ምእራፍ በጀመርንበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል በሌላ በኩል የውስጥና የውጭ ጠላቶች ብሄራዊ አንድነታችንን እና ሉአላዊነታችን እየተፈታተኑ ባሉበት ወቅት የሰንደቅ አላማ በአሉን ማክበር ተናበንና ተደራጅተን በተባበረ ክንድ የተጋረጠብንን የህልውና አደጋ ለመመከትና ለመቀልበስ ለብሄራዊ አንድነታችንነ ሉአላዊነታችን ያለንን ቁርጠኝነት በባንዲራችን ፊት ዳግም ቃላችንን የምናድስበት እለት ነው::የኢንዱስትሪው ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል አህመድ ሀምዛ እና ሰራተኞች በተገኙበት ቃለ መሀላ በመፈፀም እና የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር በመዘመር ተጠናቋል::

አዲስ አበባ መስከረም6 2014 የኢኖቬሽን ና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በተጠሪ ተቋሙ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዮት ስር የነበረውን ህንፃ ለመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፓሬሽን ማስረከቡ...
16/09/2021

አዲስ አበባ መስከረም6 2014 የኢኖቬሽን ና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በተጠሪ ተቋሙ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዮት ስር የነበረውን ህንፃ ለመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፓሬሽን ማስረከቡን አስታወቀ:: የኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር አህመዲን መሀመድ የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፓሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል አህመድ ሀምዛ ;የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዮት ዋና ዳይሬክተር ሙሉቀን ቀሬ እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፓሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሳንዶካን ደበበ በርክክቡ ወቅት በዘርፋ በጋራ ለመስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች መክረዋል:: እንደ መከላከያ ኢንጅነሪንግ ኮርፓሬሽን ያሉ ተቋማት ለቴክኖሎጂ እድገት አስተዋፅኦ ስላላቸው በዘርፋ ሀገራዊ ለውጥ ለማምጣት በጋራና ትብብር ለመስራት ወሳኝ መሆኑን ዶ/ር አህመዲን ተናግረዋል የሀገሪቱ የሳይንስ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፓሊሲ ከግብ ለማድረስና ሀገራዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በዘርፋ የሚሰሩ ተቋማት ችግር መቅረፍ እንደሚገባ የተናገሩት ሚኒስቴር ዴኤታው;የአዲሱ ህንፃ ርክክብም የዚህ አንድ አካል ነው ብለዋል::የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፓሬሽን ለዋና መስሪያ ቤት የሚሆን የቢሮ ህንፃ ስላልነበረው ስራዎችን በሙሉ አቅም ለመስራት ሲቸገር ቆይቷል:: አዲሱ ህንፃ የተሟላ መሰረተ ልማት የተዘረጋለት በመሆኑ ለተቋሙ ተልእኮ አስተዋፅኦ ያደርጋል ተብሎ ይገመታል::

ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት,የፌደራልና የክልል የፀጥታ አካላት በሙሉ የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በያላቹበት እንኳን ለአዲሱ አመት 2014 አደረሳቹ::
11/09/2021

ለጀግናው መከላከያ ሰራዊት,የፌደራልና የክልል የፀጥታ አካላት በሙሉ የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን በያላቹበት እንኳን ለአዲሱ አመት 2014 አደረሳቹ::

የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጀ አህመድ ሀምዛ ለአዲሱ አመት 2014 ያስተላለፋት መልእክት                   አዲሱ አመት አሁን ሀገራችን ያጋጠሙ...
11/09/2021

የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጀ አህመድ ሀምዛ ለአዲሱ አመት 2014 ያስተላለፋት መልእክት
አዲሱ አመት አሁን ሀገራችን ያጋጠሙንን ፈተናዎች ሁሉ በድል ተጠናቀው ፊታችንን ወደ ልማት የምናዞርበት እንዲሁም የሀገራችን ዜጎች
የአካባቢያቸውን ሰላም በመጠበቅ እና ሁሉም በተሰማራበት የስራ መስክ ጠንክሮ በመስራት የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ጠይቀዋል::
በመቀጠልም የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ከተቋቋመ አንድ አመት ቢሆነውም በርካታ ስኬቶችን አስመዝግቧል::
ለዚህም ስኬት የመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፓሬሽን ሰራተኞችንና ለኢንዱስትሪው ያልተቋረጠ ድጋፍ ላደረጉ የቦርድ አመራሮች እንዲሁም ከፍተኛ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል በመጨረሻም መጪው አዲስ አመት 2014 የደስታ,የፍቅር,የመተሳሰብ እንዲሆን ተመኝተዋል::

በመከላከያ ኢንጂሪንግ  ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ስታፍ ሰራተኞች ደማችን ለመከላከያ ሰራዊታችን በሚል መሪ ቃል ደም ሊገሳ አደረጉደም የለገሱት አባላት እንደተናገሩት ከሰራዊቱ ጋር ሄደን ባንዋጋም...
06/09/2021

በመከላከያ ኢንጂሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ስታፍ ሰራተኞች ደማችን ለመከላከያ ሰራዊታችን በሚል መሪ ቃል ደም ሊገሳ አደረጉ
ደም የለገሱት አባላት እንደተናገሩት ከሰራዊቱ ጋር ሄደን ባንዋጋም ደም በመለገስ የበኩላችንን መዋጣት አለብን ሌላው በዛሬ ቀን ደም መለገሳችን ደግሞ ልዩ ያደርገዋል በሀገራችን ጳጉሜ አንድ የኢትዮጵያዊነት ቀን የሚታሰብብት በመሆኑ ብለዋል፡፡ የደም ልገሳው ፕሮግራም በኮርፖሬሽኑ ስር በሚገኙ ኢንዱስትሪዎችም የሚቀጥል ይሆናል፡፡

Address

Addis Ababa

Telephone

+251975156500

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FDRE Defense Engineering Industry Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category