Ministry of Water and Energy - Ethiopia

Ministry of Water and Energy - Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ministry of Water and Energy - Ethiopia, Government Organization, Haile G/Selassie Road, Addis Ababa.
(1)

The Ministry of Water, Irrigation and Energy of Ethiopia is a federal organization established to undertake the management of Water and Energy resources of Ethiopia. This involves development, planning and management of water and energy resources, development of polices, strategies and programs, develop and implement water and energy sector laws and regulations, conduct study and research activiti

es, provide technical support to regional water and energy bureaus and offices and sign international agreements. The powers and duties given to the former Ministry of Water Resources and the Ministry of Mines and Energy, with respect to energy, by the provisions of other laws, currently in force, and with respect to rural electrification, to the Ministry of Agriculture and Rural Development and the Ethiopian Rural Energy Development and Promotion Center, under Proclamation No.317/2003 are hereby given to the Ministry of Water, Irrigation and Energy.

ከ 77 ሚሊዮን ብር በላይ የማማከር፣ ጥናትና ዲዛይን እና ግንባታ ውል ስምምነት ተፈረመነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በማዕከላዊ...
02/09/2026

ከ 77 ሚሊዮን ብር በላይ የማማከር፣ ጥናትና ዲዛይን እና ግንባታ ውል ስምምነት ተፈረመ

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ 77 ሚሊዮን ብር በላይ የማማከር፣ ጥናትና ዲዛይን እና ግንባታ ውል ስምምነት ተፈረመ።

የውል ስምምነቱን የፈረሙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ አካባቢዎቹ ውሃ አጠር በመሆናቸው በውሉ መሰረት የማማከርና የግንባታ ቁጥጥር ስራው ቢቻል ከተያዘለት ጊዜ ቀደም ብለው ሰርተው እንዲያስረክቡ አሳስበው፤ ለህብረተሰቡ ዘላቂ ጥቅም በሚያስገኝ አግባብ እንዲተገበርም አደራ ብለዋል።

ክቡር አምባሳደር አክለውም ተቋሙ የፕሮጀክቶቹን አፈፃፀም በመከታተል አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋልም ብለዋል።

የ LETINSA Share Company ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ማሞ እና የ DH Consult PLC ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አስቴር ተሰማ በበኩላቸው የፕሮጀክቱን አስቸኳይነት ተረድተን ከተያዘው ጊዜ ቀድመን በጥራት ሰርተን ለማስረከብ ቃል እንገባለን ብለዋል።

በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል የሆነውና በአለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የሚተገበረው ፕሮጀክት የ88 መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ጥናትና ዲዛይን የአማካሪ ቅጥር እየተከናወነ ሲሆን ከነዚህ መካከል የ72ቱ ፕሮጀክቶች አማካሪ ቅጥር የተፈፀመ በመሆኑ፤ በዛሬው ዕለት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል 4 ፕሮጀክቶች 2ቱ በሱርማ እና 2ቱ በሸኮ ወረዳ በ45,260,435.00 ወጪ ከ DH Consult PLC ጋር ውል የተፈረመ ሲሆን፤ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 3 ፕሮጀክቶች 2ቱ በጠምባሮ እና 1ዱ በሙሁር አክሊል ወረዳ በ31,750,137.69 ወጪ ከ LETINSA Share Company ጋር በ12 ወራት የሚጠናቀቅ ውል ተፈርሟል።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/

የሦስተኛው ምዕራፍ OWNP-CWA III የዝግጅት ምእራፍ ላይ ውይይት ተካሄደ።ነሐሴ 27/2018ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) አዲስ አበባ  OWNP-CWA III በኢትዮጵያ በሙሉ ዘላቂ እና ፍትሃዊ የውሃ...
02/09/2026

የሦስተኛው ምዕራፍ OWNP-CWA III የዝግጅት ምእራፍ ላይ ውይይት ተካሄደ።

ነሐሴ 27/2018ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) አዲስ አበባ OWNP-CWA III በኢትዮጵያ በሙሉ ዘላቂ እና ፍትሃዊ የውሃ፣ የንፅህና እና የንፅህና መጠበቂያ (WaSH) አገልግሎቶችን ተዳራሽነ በሚያረጋግጠው ፌዝ 3 ዋሽ ፕሮግራም የዝግጅት ላይ ውይይት ተካሄደ።

መርሀግብሩ ላይ የተገኙት የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ዶክተር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ባደረጉት ንግግር የፕሮግራሙን ዋና ዓላማ አጠቃላይ ንድፍ የበለጠ ለማሻሻል እና ለማጠናከር መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በፕሮግራሙ ወሰንና ሽፋን፣ የውጤት መስኮች፣ የፋይናንስ ክፍያ አመልካቾች ፣የክትትልና ግምገማ ስርዓቶች እንዲሁም አፈፃፀም ላይ የጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ ያለመ መሆኑንም ጠቅሰዋል ።

ሚኒስትር ዲኤታው በማከል ባለፋት ቀናት ላይ የመንግሥት እና የልማት አጋሮች ቡድኖች ከፌዴራል የዋሽ ሴክተር ጋር በመሆን ስኬቶችን የመገምገም እና የስትራቴጂክ አቅጣጫዎችን የመለየት ስራ ማከናወናቸውን ገልጸዋል ።

በውይይቱ ላይም የቴክኒክ፣ የሕዝብ ወጪ፣ (የፋይናንስ አስተዳደር) እንዲሁም የአካባቢ እና ማህበራዊ ስርዓቶች ምዘና ግኝቶችና የውሳኔ ሃሳቦች ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸው በመጥቀስ OWNP-CWA III በኢትዮጵያ በሙሉ ዘላቂ እና ፍትሃዊ የውሃ፣ የንፅህና እና የንፅህና መጠበቂያ (WaSH) አገልግሎቶችን ተዳራሽነት ለማፋጠን ታስቦ የተዘጋጀ ነውም ብለዋል።

በመጨረሻም ክቡር አምባሳደር አስፋው የዚህ ፕሮግራም ስኬት በጋራ ቁርጠኝነትና ባለቤትነት ላይ የተመሰረተ መሆኑን በመጠቆም ሁሉም ተሳታፊዎች በሚያደርጉት ንቁ ተሳትፎ ፕሮግራሙ በተያዘለት ጊዜ ወደ ትግበራ እንዲገባ ጥሪ አቅርበዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የቀጣዩን የOWNP-III ፕሮግራም ዲዛይን ለማጠናከር፣ ከተሳታፊዎች ግብዓት ለማሰባሰብ እና በተካሄዱ የቴክኒክ፣ የህዝብ ወጪ፣ የፋይናንሻል ሥርዓት፣ የአካባቢና ማህበራዊ ሥርዓት ግምገማዎች የተገኙ ግኝቶችን ወደ ፕሮግራሙ ዲዛይን ማካተት በሚያስችሉ ጉዳዮች በተለያዩ አካላት ሰነዶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በመጨረሻም የውይይቱ ውጤቶችና ከተሳታፊዎች የተሰበሰቡ ግብዓቶች ቀጣዩን የOWNP-III ፕሮግራም ለማጠናቀቅ እንደ ጠቃሚ ግብዓት እንደሚያገለግሉ የተገለፀ ሲሆን የፕሮግራም ዝግጅቱን ለማስቀጠል ቀጣይ እርምጃዎችም ተመላክተዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የፌደራል ሚኒስቴር መስሪያቤት፣ የክልል ውሃ፣ ጤና፣ ፋይናንስ እና ትምህርት ቢሮዎች፣ የልማት አጋሮች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/

የቤዚን ፕላን ክለሳ ሂደት የዴስክ ስተዲ ስራ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግምገማ ተጀመረነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | ሀዋሳየቤዚን ፕላን ክለሳ ሂደት አካል የሆነው የዴስክ ስተዲ (Desk Study) ስ...
01/09/2026

የቤዚን ፕላን ክለሳ ሂደት የዴስክ ስተዲ ስራ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግምገማ ተጀመረ

ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም | ሀዋሳ

የቤዚን ፕላን ክለሳ ሂደት አካል የሆነው የዴስክ ስተዲ (Desk Study) ስራ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግምገማ በሀዋሳ ሮሪ ሆቴል መካሄድ ጀመረ።

የግምገማ መድረኩ ዋና ዓላማ በዴስክ ስተዲ ሂደት የተከናወኑ ስራዎችን፣ የተገኙ ግኝቶችንና የታዩ ክፍተቶችን በጋራ በመገምገም ለቀጣይ የቤዚን ፕላን ክለሳ ስራ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው።

በመድረኩ ላይ የስ/ሸ/ሀ/ቤ/አስ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ወንድሙ ታዲዮስ እንደገለጹት፣ የቤዚን ፕላን ለመከለስ የዴስክ ስተዲ ስራው ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፣ የተለያዩ ሙያዎችንና የትምህርት ደረጃዎችን ያካተቱ ባለሙያዎች በጋራ በመስራታቸው ልዩ ልዩ ልምድና እውቀት ለመለዋወጥ እንዳስቻለ ገልጸዋል።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ብሔራዊ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር አስተባባሪ እና የብራይት ፕሮጀክት የቤዚን ፕላን አስተባባሪ ዶ/ር ብዙነህ አሰፋው በበኩላቸው፣ የቤዚን ፕላን ክለሳ ስራው ከኦዲት በተገኘ ግብዓት መጀመሩ ለስራው መሳለጥና ውጤታማነት አጋዥ መሆኑን ገልጸዋል።

በክለሳ ሂደቱም ሁሉም የትኩረት መስኮች በጥልቀት እንዲታዩ፣ ክፍተቶች እንዲለዩና ገንቢ ግብዓቶች ተሰብስበው ወደ ቀጣይ ስራ እንዲገቡ የሚያስችል ሂደት እንደሚከናወን አስረድተዋል።

በዕለቱም የጽ/ቤቱ የቤዚን ፕላን ዴስክ ኃላፊ አቶ አበበ አሰሌ በአርባምንጭ ቆይታ የተከናወኑ ስራዎችን በማጠቃለል ለመድረኩ አቅርበዋል።

በመቀጠልም እያንዳንዱ የትኩረት መስክ በቆይታው ያከናወናቸውን ስራዎች በHarmonization Table (የተገኙ ግኝቶችን የማጣጣሚያ ሰንጠረዥ)፣ Gap Matrix (ክፍተቶችን የሚያሳይ ሰንጠረዥ)፣ Review Matrix (የግምገማ ሰንጠረዥ) እና Action Plan for Next Duties (የቀጣይ ስራ ዕቅድ) በመጠቀም ለግምገማ እያቀረበ ይገኛል።

በግምገማው መድረክ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የቤዚን ፕላን ዴስክ ኃላፊና ሌሎች ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ ከውሃና መሬት ልማት ማዕከል ባለሙያዎች፣ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመራማሪዎች እንዲሁም ከደቡብ ኢትዮጵያ፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ከኦሮሚያና ከሲዳማ ክልሎች የውሃ፣ የግብርና፣ የመስኖና የአካባቢ ጥበቃ ቢሮዎች ተወካዮች ተሳትፈዋል። የቤዚን ጽ/ቤቱ ኃላፊዎችና ባለሙያዎችም በመድረኩ ተገኝተዋል።

የግምገማ መድረኩ የተዘጋጀው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ የውሃና መሬት ሀብት ማዕከል እና የብራይት ፕሮጀክት ባላቸው ትስስርና በተደረገ የበጀት ድጋፍ ሲሆን፣ መድረኩ ለቀጣይ ሁለት ቀናት ይቆያል።

የዴስክ ስተዲ ስራው የመጀመሪያ ምዕራፍ ግምገማ በተሳታፊ አካላት የሚቀርቡ ግብዓቶችን በማካተት ለቀጣዩ የቤዚን ፕላን ክለሳ ስራ ጠንካራ መሠረት እንደሚፈጥር ይጠበቃል።

የባዘርኔት 2ኛው ብሔራዊ ስትሪንግ ኮሚቴ የ2018 በጀት ዓመት ሪፖርትና የ2019 በጀት ዕቅድ ላይ መከረ።አዲስ አበባ:-ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚተገ...
31/08/2026

የባዘርኔት 2ኛው ብሔራዊ ስትሪንግ ኮሚቴ የ2018 በጀት ዓመት ሪፖርትና የ2019 በጀት ዕቅድ ላይ መከረ።

አዲስ አበባ:-ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚተገበረው የቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ (BaSRINET) ፕሮጀክት 2ኛው ብሔራዊ ስትሪንግ ኮሚቴ የ2018 በጀት ዓመት ሪፖርትና የ2019 በጀት ዕቅድ ላይ መከረ።

ውይይቱን ያስጀመሩት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ እና የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ፕሮጀክቱ ውጤታማ እንዲሆን ከቢሮ አደረጃጀት ጀምሮ እስከ ባለሙያ ምደባ ተደርጎ በበጀት አመቱ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ እንደነበረ አስታውሰዋል።

ክቡር አቶ ሞቱማ አያይዘውም በሁለቱ ቤዚኖች ላይ በቂ ባለሙያ የተመደበ ሲሆን በቀጣይ ከዚህ የበለጠ አፈፃፀም እንዲኖር ሁሉም የሚመለከታቸው ባለድርሻዎች ለፕሮጀክቱ ተግባራዊነት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ አሳስበዋል።

የጣሊያን መንግስት ተወካይ Mr. Luca Carpintieri በበኩላቸው በቀረው ሪፖርት የፕሮጀክቱን አፈፃፀም አድንቀው፤ በቀጣይ ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር ከዚህ የበለጠ መስራት እንደሚቻል ማሳያ ነው ብለዋል።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ የቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ (BaSRINET) ፕሮጀክት የ2018 በጀት ዓመት ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዕቅድን እንዲሁም የፕሮጀክት አፈፃፀም መመሪያ ምንነትን በአማካሪው አድማሱ ቴሶ (ዶ/ር) ለብሔራዊ ስትሪንግ ኮሚቴ አቅርበው በሰፊው ውይይት ተደርጎበታል።

የባዘርኔት ፕሮጀክት የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር በቤዚኖች ዕውን እንዲሆን ከሚያግዙ ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን፤ በአዋሽ እና በዋቢሸበሌ ቤዚን የሚገኙ አርብቶና ከፊል አርብቶ አደሮችን የመቋቋም አቅማቸውን በማጎልበት በውሃ ላይ የተመሰረተ ዘላቂ የኑሮ አማራጮችን መፍጠር ያለመው ነው።

በጣሊያን መንግስት የሚደገፈውና በሁለቱ ቤዚኖች ላይ የሚተገበረው ፕሮጀክት የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር (IWRM) ለማሳለጥ የመረጃ ተደራሽነትን ማሻሻል፣ የውሃ ተደራሽነትን ማሳደግ፣ የተራቆቱ አካባቢዎችን እንዲያገግሙ ማድረግ፣ የተቋማትን አቅም ማሳደግ እና የኢነርጂ ተደራሽነትን ማስፋት ላይ ያለመ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የፕሮጀክት አስተዳደር እና ቅንጅት፣ የውሃ ተፋሰስ መረጃ አያያዝ፣ አስተማማኝ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የውሃ አቅርቦትና ተደራሽነትን ማሻሻል፣ የተፋሰስ እና የመከላከያ ቀጠና (Buffer Zone) አስተዳደርን ማሻሻል እና ቴክኒካዊና ተቋማዊ የቁጥጥር አቅምን ማጠናከር ላይ ውጤታማ ስራ መሰራቱን በሪፓርቱ ተመላክቷል።

በመድረኩ ከግብርና፣ ከገንዘብ እና ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር እና ከአለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ (IFAD) የተውጣጡት ብሔራዊ ስትሪንግ ኮሚቴዎች የተሳተፉ ሲሆን የ2019 በጀት አመት የተግባራት ዕቅድን፣ የፕሮጀክት አፈፃፀም መመሪያን /PIM/ እና ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ በጀትን አፅድቀዋል።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/

ውጤታማ የኢነርጂ ልማት ለግብርናና ለኢንዱስትሪ ማንሰራራት ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም. (ዉ.ኢ.ሚ) የመደመር መንግሥት በኢነርጂ ልማት ባከናወናቸው በርካታ ተግባራት አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል።...
30/08/2026

ውጤታማ የኢነርጂ ልማት ለግብርናና ለኢንዱስትሪ ማንሰራራት

ነሐሴ 24/2018 ዓ.ም. (ዉ.ኢ.ሚ)

የመደመር መንግሥት በኢነርጂ ልማት ባከናወናቸው በርካታ ተግባራት አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል። የኢነርጂ አማራጭ ምንጮችን በአግባቡ በመለየት እና በጠንካራ የፕሮጀክት አፈጻጸም በዘርፉ የላቀ ስኬት መጥቷል።

የኢነርጂ አማራጭን በማስፋት ከውሃ በተጨማሪ የንፋስ፣ የፀሐይ እና የእንፋሎት ኢነርጂን በማልማት የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት ተሰርቷል።

የኃይል ተደራሽነት መስፋፋቱ የተለያዩ ዘርፎች ዕድገት እንዲያስመዘግቡ ወሳኝ ሚና አለው። በተለይም የግብርናና የኢንዱስትሪ ዘርፎች ከፍተኛ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በማድረግ ለአገራዊ ብልጽግና እውን መሆን የድርሻውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ሥራዎች አጠቃላይ የኃይል ተደራሽነት 63 በመቶ ደርሷል። ይህም ከግሪድና ከኦፍ-ግሪድ የኃይል አቅርቦቶች የተገኘ ውጤት ሲሆን፤ ከተሞችን እና ገጠር አካባቢዎችን በኃይል አገልግሎት ለማስተሳሰር የተደረገውን ጥረት ያሳያል።

የኢነርጂ ልማት የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ከማሳደግ ባለፈ፣ በአገሪቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ደማቅ አሻራውን እያሳረፈ ነው። ኃይል ለግብርናና ለኢንዱስትሪ ዘርፎች የምርት መሠረታዊ ግብዓት በመሆኑ የእነዚህን ዘርፎች ምርታማነት ለማሳደግ ወሳኝ ሚና አለው።

የኃይል አቅርቦት መስፋፋቱ የመስኖ ልማትን ለማስፋፋት፣ የግብርና ማሽነሪዎችን በስፋት ለመጠቀም፣ የውሃ ማንሳትና ማከፋፈል ሥራዎችን ለማቀላጠፍ እንዲሁም የምርትና የማቀነባበር አቅምን ለማሳደግ እያገዘ ይገኛል። በዚህም የግብርና ምርትን ከማሳ እስከ ገበያ የሚያስተሳስር የምርት ሰንሰለት ለማጠናከር አዳዲስ ዕድሎች ተፈጥረዋል።

በኢንዱስትሪውም የተረጋጋና ተደራሽ የኃይል አቅርቦት የፋብሪካዎችን፣ የማምረቻ ተቋማትንና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የምርት አቅም ለማሳደግ ወሳኝ ግብዓት ሆኗል። የኃይል አቅርቦቱ መሻሻል የማምረቻ ሂደቶችን ለማሳለጥ፣ የምርት ወጪን ለመቀነስ፣ የምርት መጠንና ጥራትን ለማሳደግ እንዲሁም የኢንዱስትሪ ዘርፉን ተወዳዳሪ ለማድረግ ያግዛል።

የግሪድና ኦፍ-ግሪድ የኃይል መፍትሔዎችን በጋራ መጠቀምም ከብሔራዊ ግሪድ ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን በኃይል አገልግሎት ለማካተት የሚያስችል አማራጭ ፈጥሯል። ይህም በገጠር የሚገኙ አነስተኛ ንግዶችንና የማምረቻ ተቋማትን ለማስፋፋት፣ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና የአካባቢ ኢኮኖሚን ለማነቃቃት ዕድል ፈጥሯል።

የኃይል ተደራሽነት መስፋፋቱ በትምህርት፣ በጤና፣ በቴክኖሎጂና በዲጂታል አገልግሎቶች የሚታየውን ለውጥ ለማፋጠን አስተዋጽኦ እያደረገ ነው። ኃይል ከቤት ብርሃን በላይ የምርት፣ የኢንተርፕራይዝ፣ የኢንዱስትሪና የዲጂታል ኢኮኖሚ መሠረት በመሆኑ የኢነርጂ ልማት የአገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን የማይተካ ሚና አለው።

በመሆኑም የኢነርጂ ልማትን ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከከተማ ልማትና ከሌሎች ዘርፎች ጋር በማስተሳሰር መሥራት የኢትዮጵያን የምርት አቅም ለማሳደግና የኢኮኖሚ ሽግግሩን ለማፋጠን ቁልፍ ነው።

በአጠቃላይ የኃይል ተደራሽነት የኤሌክትሪክ ብርሃን ተደራሽ ከማድረግ ባሻገር የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርታማነት ዕድገት መሰረት ሆኗል።

በተጨማሪም የሥራ ዕድልን ለመፍጠር እና የአገሪቱን ኢኮኖሚ ወደ ተሻለ የልማት ደረጃ ለማሸጋገር የኢነርጂ ዘርፉ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።

ይህንን ድርሻውን ይበልጥ ለማጠናከር እና አገራዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ የኢነርጂ ልማቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት የአፈጻጸም ማንዋል አተገባበር ውይይት ተደረገበትአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም. (ው.ኢ.ሚ) — በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተተገበረ የሚገ...
29/08/2026

የቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት የአፈጻጸም ማንዋል አተገባበር ውይይት ተደረገበት

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም. (ው.ኢ.ሚ) — በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተተገበረ የሚገኘው የባዘርኔት ፕሮጀክት የአፈጻጸም ማንዋል (BaSRINET Project implementation manual) አተገባበርን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ።

ውይይቱ የፕሮጀክቱን አፈጻጸም በተቀናጀ፣ በተደራጀና በውጤታማ መንገድ ለመምራት የተዘጋጀው የአፈጻጸም ማንዋል በተግባር እንዴት ሊተገበር እንደሚችል ለመወያየትና የባለድርሻ አካላትን ግብዓት ለማሰባሰብ ያለመ ነው።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሞላ ረዳ፣ የአፈጻጸም ማንዋሉ ፕሮጀክቱን በቀጣይ የትግበራ ሂደት በተደራጀና በተቀናጀ መንገድ ለመምራት ጠቃሚ የአፈጻጸም መሣሪያ መሆኑን ገልጸዋል።

ማንዋሉ የፕሮጀክቱን ዓላማዎችና የአፈጻጸም አቅጣጫዎች በግልጽ ለመለየት ከማገዙም በላይ በፕሮጀክቱ የሚሳተፉ አካላት የየራሳቸውን ሚናና ኃላፊነት በተገቢው መንገድ እንዲወጡ የሚያስችል የጋራ የትግበራ ሰነድ መሆኑን ተጠቁሟል።

የልማት አማካሪው ዶክተር አድማሱ ቴሶ የማንዋሉን ዝርዝር ይዘት በማቅረብ፣ ማንዋሉ የፕሮጀክቱን ትግበራ ሊያግዝ በሚችል መልኩ በተለያዩ ይዘቶችና ምዕራፎች መደራጀቱን አብራርተዋል።

በማንዋሉ የዝግጅት ዘዴ፣ ዓላማና ጥቅም፣ ተቋማዊ የአመራር ሥርዓት፣ የዕቅድ አፈጻጸም ይዘቶች፣ የፕሮጀክቱ አስተዳደር ይዘቶች፣ የአፈጻጸም ክትትልና ግምገማ ሥርዓት እንዲሁም የትግበራ ስልቶች ተካተዋል።

በውይይቱ ወቅትም ማንዋሉ በትግበራ ሂደት ቀላል፣ ግልጽና ተግባራዊ እንዲሆን የሚያስችሉ ማሻሻያ ሐሳቦችና አስተያየቶች ከተሳታፊዎች ቀርበው ምክረ ሀሳቦች ተሰንዝረዋል።

በመድረኩ የተነሱት ሐሳቦችና አስተያየቶች የፕሮጀክቱን የአፈጻጸም ማንዋል በቀጣይ የትግበራ ሂደት የበለጠ ተግባራዊ፣ ግልጽና ውጤታማ ለማድረግ ጠቃሚ ግብዓት እንደሚሆኑ ተገልጿል።

የአፈጻጸም ማንዋሉ ስትራቴጂካዊ የትግበራ ሰነድ በመሆኑ፣ የፕሮጀክቱን ዓላማዎች ለማሳካት የሥራ ሂደቶችን በግልጽ አቅጣጫ ለመምራት፣ ተግባራትን በቅንጅት ለማከናወንና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ለማጠናከር ቁልፍ ሚና እንደሚኖረው ተመልክቷል።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/

የባዝርኔት ፕሮጀክት የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ አቀረበ፡፡በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሥር የሚተገበረው የባዘርኔት (BASRINEt) ፕሮጀክት የ2018 ዓ....
28/08/2026

የባዝርኔት ፕሮጀክት የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ አቀረበ፡፡

በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሥር የሚተገበረው የባዘርኔት (BASRINEt) ፕሮጀክት የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ለብሔራዊ ቴክኒካል ኮሚቴ አቀረበ።

ነሐሴ22/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ)
ፕሮግራሙን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተቀናጀ ውሀ ሃብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ መርተውታል።

የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ክንውኖች፣ አፈጻጸሞች እና ያጋጠሙ ችግሮችን በዝርዝር የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሞላ ረዳ አቅርበዋል።

አቶ ሞላ ፕሮጀክቱ በዋናነት አምስት ኮምፖነንቶች እንዳሉት በመግለጽ ባለፈው በጀት አመት በዋናነት የውሃ ሀብት እና መሰረተ ልማት ልማት በሦስት የፕሮጀክት ትግበራ ቦታዎች ላይ የውሃ አማራጮች መለያ እና ካርታ የማዘጋጀት ሥራ ተጠናቋል፣የ16 ኪሎ ሜትር የታችኛው አዋሽ ወንዝ የጎርፍ መከላከል እና የቦይ ማቋቋሚያ ጥናት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ለ3 አነስተኛ መስኖ እና 4 የውሃ አቅርቦት ስራዎች ጥናት መጀመሩን፣13 የውሃ ጥራት እና ደለል መከታተያ የላቦራቶሪ ዕቃዎች ተገዝተው ወደ ሀገር ውስጥ በመግባት ላይ መሆናቸውን፣በአዋሽ እና በዋቢ-ሸበሌ ተፋሰሶች 10 የቴሌሜትሪ ቅድመ-ተከላ ቦታዎች የተረጋገጡ ሲሆን፣ ለ6 የሙከራ እና 5 የመከታተያ የከርሰ-ድርጅት ጉድጓዶች የግዥ ሂደት በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

የተፋሰስ እንክብካቤ እና የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ላይም የተፋሰስ እና ወሰን ክልል እንክብካቤ ማዕቀፍ እንዲሁም የመሬት አጠቃቀም ምዘና 100%የተጠናቀቀ መሆኑን በመግለጽ የአቅም ግንባታ እና ማህበረሰብ ሰፊ እንቅስቃሴ መደረጉንም በሪፖርታቸው ገልጸዋል፡፡

በሪፖርቱ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና የተወሰዱ መፍትሄዎች የቀረቡና በኮሚቴዉ ተሳታፊዎች ዉይይት ከተደረገበት በኋላ የ2019 ዓ.ም የፕሮጀክቱ ዓመታዊ የሥራና የበጀት እቅድም በአስተባባሪው ቀርቧል፡፡

በሪፖሪቱ ዋና ዋና ተግባራት እና የአመቱ በጀት በኮምፖነንት ቀርቦ በዚህ መሰረት የበጀት አመቱ አጠቃላይ በጀት በጣም ከፍተኛ መሆኑ የተመላከተ ሲሆን፤ይህንን ለማሳካት አስፈላጊዉን ስልት በማዉጣት ለማከናወን እንደታለመ እና ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላትና ፈጻሚዎች ተገቢ ድጋፍ ከተደረገ ማከናወን አንደሚቻል ተጠቅሷል።

በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች አቶ ሞላ ረዳ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

አቶ ደበበ ደፈርሶ በተሳታፊዎች በቀረቡት ጉዳዮች ላይ መሻሻል የሚገባቸዉ ነጥቦች እንዲሻሸሉ አቅጣጫ በመስጠት ስብሰባዉ አጠቃለዋል።

በፕሮግራሙ ከውሃና ኢነርጂ ፣ከግብርና እና ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ የጣሊያን የልማት ትብብር ኤጀንሲ AICS እናሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከCIFF ጋር በንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን  ዘርፍ የሚደረገውን  ትብብር አጠናከረ።አዲስ አበባ፣ነሐሴ 21/ 2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒ...
27/08/2026

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከCIFF ጋር በንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ የሚደረገውን ትብብር አጠናከረ።

አዲስ አበባ፣ነሐሴ 21/ 2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ)

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ፣ መቀመጫውን በእንግሊዝ ያደረገው የChildren’s Investment Fund Foundation (CIFF) መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ sir Chris Horn እና የልዑካን ቡድናቸውን በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል ተቀብለው በሁለትዮሽ ትብብር ጉዳዮች ላይ በስፋት ተወያይተዋል።

ሚኒስቴሩ በአዋጅ የተሰጠውን ሥልጣንና ተግባር በተሟላ ሁኔታ ለመፈጸም ከሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት፣ ከሁለትዮሽና ከአጋር ድርጅቶች እንዲሁም ከበጎ አድራጎትና ፋውንዴሽን ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝም ተገልጿል።

ከሚኒስቴሩ ጋር በተለይም በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን (WASH) ዘርፍ በትብብር እየሰሩ ካሉ አጋር ተቋማት መካከል CIFF አንዱ ሲሆን፣ ፋውንዴሽኑ በኢትዮጵያ የWASH ፕሮግራሞችን ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት የሚገኘውን ድጋፍ እያጠናከረ እንደሚገኝ በመድረኩ ተጠቅሷል ።

በውይይቱ ወቅት በሚኒስቴሩ በኩል በንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አቅርቦት ዘርፍ ለረጅም ጊዜ የቆዩ መሠረታዊ ተግዳሮቶችን፣ አሁን እየተከናወኑ ያሉ ዋና ዋና የመንግሥት ፕሮግራሞችን እና በቀጣይ በጋራ ሊሰራባቸው የሚገቡ የትብብር መስኮች ተብራርተዋል።

በተለይም ኢትዮጵያ የሁሉንም ዜጎች የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፍላጎትን ለማሟላት የምታደርገውን ጥረት ለማፋጠን በአጋር ተቋማት ሊደረግ የሚችለውን ድጋፍ በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

የCIFF መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ sir Chris Horn
በበኩላቸው በኢትዮጵያ በንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችንና የታዩ እድገቶችን አድንቀዋል። በተጨማሪም CIFF በመንግሥት ቅድሚያ የሚሰጣቸው አጀንዳዎችን በመከተል ዘርፉን ለመደገፍና ከሚኒስቴሩ ጋር ያለውን ትብብር ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

CIFF ባለፉት ዓመታት ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር በመስራት የኢትዮጵያን የWASH ፕሮግራሞች ለማጠናከር የሚደረገውን ጥረት ሲደግፍ የቆየ ሲሆን በዕለቱ በተካሄደው ውይይትም ይህንን ትብብር በቀጣይ ለማጠናከር በሚቻልባቸው የጋራ የሥራ መስኮች ላይም ተጨማሪ ሀሳብ ተለዋውጧል።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/

ስፔሻላይዝድ ላብራቶሪው የአገሪቱን የውሃ ሃብት ጥራትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊነሐሴ 21/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ...
27/08/2026

ስፔሻላይዝድ ላብራቶሪው የአገሪቱን የውሃ ሃብት ጥራትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የአገሪቱን የውሃ ሃብት ጥራትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የውሃ ጥራት ላብራቶሪ የምረቃ ስነስርዓት ላይ የአገሪቱን የውሃ ሃብት ጥራትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ ነው ተባለ።

የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በነባሩ ግቢ ውስጥ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ ህንፃዎችንና ዘመናዊ የላብራቶሪ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በይፋ ስራ አስጀመረ።

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ለአገልግሎት የበቃው ዘርፈብዙ ህንፃ እና ስፔሻላይዝድ ላብራቶሪ ተቋሙ የተጣለበትን ኃላፊነትና ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ የሚያስችል በመሆኑ የጥናት፣ የምርምር እና የልማት ስራዎችንም ያዘምናል ብለዋል።

ስፔሻላይዝድ ላብራቶሪው የአገሪቱን የውሃ ሃብት ጥራትንና ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው እንደሀገር ከዘመናዊ ግብርና ወደ ኢንደስትራላይዜሽን ለመሸጋገርም ከፍተኛ እገዛ አለው ነው ያሉት።

ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም እንደሀገር የውሃ መጠንና ጥራት ምን ይመስላል የሚለውንም ለመለየት በላብራቶሪ የተደገፈ መሆን ስላለበት ዛሬ እውን ሆኖወደ ስራ እንዲገባ የላቀ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላትም በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ታመነ ኃይሉ በበኩላቸው ተቋሙ ለረጅም አመታት በጥናት፣ በምርምርና በስልጠና ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰው፤ በይፋ አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው ስፔሻላይዝድ ላብራቶሪ ተቋሙ ኃላፊነቱን የበለጠ እንዲወጣም ያግዛል ብለዋል።

ዶ/ር ታመነ አያይዘውም የውሃ ጥራትና ምርምር ላይ በላብራቶሪ አገልግሎት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግርና በተሻለ አቅምና ጥራት ተልዕኳችንን ለመወጣት የሚያስችል አዲስ ምዕራፍ ከመሆኑም በላይ ተቋሙ ለውሃው ዘርፍ ብቁ፣ ተግባራዊ ክህሎት ያለውና ችግር ፈቺ የሆነ የሰው ሀብት ልማት ለማፍራትም ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል ነው ያሉት።

በመድረኩ የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አህመድ እና የቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ግቢው የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ ማድረጊያ፣ ለልምድ ልውውጥ የሚመቹ ቦታዎች፣ ሶስት በአንድ የስፓርት ማዘውተሪያ ሜዳ፣ የመዝናኛና ሌሎች የመሰረተ ልማት ማሻሻያ ቦታዎችን ያካትታል።

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/

የአፍሪካ የኢኮሃይድሮሎጂ ቀጠናዊ ማዕከል (ARCE) በዩኔስኮ ተገመገመ ።በኢትዮጵያ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ የኢኮሃይድሮሎጂ ቀጠናዊ ማዕከል (ARCE) በዩኔስኮ ግምገማ ተካሄደ።ነሐ...
26/08/2026

የአፍሪካ የኢኮሃይድሮሎጂ ቀጠናዊ ማዕከል (ARCE) በዩኔስኮ ተገመገመ ።

በኢትዮጵያ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ የኢኮሃይድሮሎጂ ቀጠናዊ ማዕከል (ARCE) በዩኔስኮ ግምገማ ተካሄደ።

ነሐሴ 20/2018ዓም (ው.ኢ.ሚ)
በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ሃብት ዘርፍ ሚ/ር ዲኤታ ተወካይ እና በሚኒስትር ዲኤታ ማእረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ እንደገለጹት፤ማዕከሉ በኢትዮጵያ መንግስት እና በዩኔስኮ መካከል በተደረገ ስምምነት ከተቋቋመ ወዲህ በምርምር፣ በአቅም ግንባታ፣ በዕውቀት ሽግግር እና በቴክኒክ ትብብር ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸዋል።

ክቡር አቶ ሞቱማ በማከል ማዕከሉ ለተፋሰስ ጥበቃ፣ ለስነ-ምህዳር ማገገም፣ ለውሃ ጥራት መሻሻል፣ ለብዝሃ-ሕይወት ጥበቃና ለአየር ንብረት መቋቋም እና ዘላቂ ኑሮ እንደ ተግባራዊ ላቦራቶሪ የሚያገለግሉ 11 የኢኮሃይድሮሎጂ ማሳያ ጣቢያዎችን ገንብቶ ወደ ሥራ ማስገባንም አውስተዋል።

በኢትዮጵያ መንግስት እና በዩኔስኮ ስምምነት መሰረት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ በራስ ገዝ የፌደራል ተቋምነት የተቋቋመው ማዕከሉ፤ በሳይንሳዊ ዕውቀት ላይ የተመሰረቱ መፍትሔዎችን ወደ ተግባር በመቀየር ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛልም ብለዋል።

ማዕከሉ የዩኔስኮ የዓለም አቀፍ ሃይድሮሎጂ ፕሮግራም አካል በመሆን በአፍሪካ ደረጃ የሚከሰቱ የውሃ ክፍተቶችን ለመቅረፍና ለስነ-ምህዳር እንክብካቤ የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር ቀጠናዊ ማዕከል ሆኖ እንደሚቀጥልም ክቡር አቶ ሞቱማ ገልጸዋል።

በመጨረሻም ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ለማዕከሉ መታደስና መጠናከር ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግና ከተገምጋሚው ቡድን የሚወጡ አስተያየቶችና ምክረ-ሃሳቦች ተቋሙን የበለጠ ውጤታማ እንደሚያደርጉት ጠቅሰዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ ባለፉት ስድት ዓመት የተሰሩ እና ውጤት ያስመዘገቡ ስራዎችን አቶ ዮሀንስ ዘሩሁን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

ከዩኒስኮ የመጡ ተወካዮችም በቀረበላቸው ገለጻ በመነሳት ማእከሉ ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሀሳብ አስተያየታቸውን ሰጥተዋ፡፡

በመርሀ ግብሩ ላይ የውሃና ኢነርጂ ከፍተኛ
አመራች የዘርፉ ባለሙያዎች፣የዩኒስኮ ተወካዮችና ዩኒቨርስቲዎች ተሳትፈዋል፡፡

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ
https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p/
ቴሌግራም
http://t.me/mowieethiopia
ዌብሳይት
http://mowe.gov.et
X/ትዊተር
https://x.com/mowe_ethiopia
ዩቱዩብ
https://youtube.com/-e8842?s
ቲክቶክ
tiktok.com/

Address

Haile G/Selassie Road
Addis Ababa
5744AND5673

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30

Telephone

+251116611111

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ministry of Water and Energy - Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ministry of Water and Energy - Ethiopia:

Shortcuts

Share