Addis Ababa City Administration Bureau Of Women, Children and Social Affair

Addis Ababa City Administration Bureau Of Women, Children and Social Affair This is official page of Addis Ababa City Administration Bureau of Woman,Children and Social Affairs.

06/09/2026

የአርቲስት እና የነፃነት ተጋይ እልፍነሽ ቀኖ ህልፈተ ህይወት የሰማሁት በጥልቅ ሀዘን ዉስጥ ነው ።

አርቲስት እልፍነሽ ድምፃዊት ብቻ ሳትሆን የሰበአዊ መብትና እኩልነት ታጋይ ነበረች።
ለቤተሰቦቿ ፣ለወዳጅ ዘመዶቿና ለአድናቂዎቿ መጽናናትን እመኛለሁ።
ፈጣሪ ነብሷን በአፀደ ገነት ያኑር

Lubbuun darbuu Artistii fi Qabsooftuu Bilisummaa Ilfinash Qannoo kanan dhagahe gadda guddaa keessatti.

Artist Ilfinash weellistuu qofa osoo hin taane qabsooftuu mirga namummaa fi wal-qixummaa turte.
Maatii ishee, firoottan ishee fi dinqisiifattoota isheef jajjabinan hawwa.
Waaqni Lubbuu ishee Jeennata haa jiraachisu

06/09/2026
06/09/2026

ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ እና በተለያዩ መንገዶች ከቦሌ - መገናኛ የቪአይፒ ኮሪደር ልማት አካል የሆነውና ቦሌ ብራስ አካባቢ በሚገኝ የመንገድ መሿለኪያ ውስጥ የተፈጠረውን የውሃ ማቆር ችግር አስመልክቶ የሰጣችሁትን ጥቆማ በአክብሮት ተቀብለናል።

በእርግጥም የሰጣችሁት ጥቆማ ትክክል እና ተገቢነት ያለው ከመሆኑ በተጨማሪ ለከተማችን ልማት ያላችሁን ተቆርቋሪነት እና የኔነት ስሜት ያሳየ በመሆኑ ከልብ እያመሰገንን።

ይህ ያልተጠናቀቀው የምድር ውስጥ መሿለኪያ ቦታ የውሃ ማቆር ችግር ያጋጠመው፤ ቀደም ሲል ስራውን ይዞት ከነበረው ኮንትራክተር ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ምክንያት የውል መቋረጥ በማጋጠሙ እና የግንባታ መጓተት በመከሰቱ ሲሆን ፤ ይህንን ያልተጠበቀ ችግር በመረዳት ተቋማችን አፋጣኝ መፍትሄ ለመስጠት ሲሰራ ቆይቷል።

በመሆኑም ያልተጠናቀቀውን የመሿለኪያ የምድር ውስጥ ስራ ዳግም ለማስጀመር በፍጥነት የአዲስ ኮንትራት ግዢ ጨረታ በማውጣት ሂደቱ ተጠናቋል።

በመጨረሻም ሀሳባችሁን ለሰጣችሁ እና በኔነት ስሜት ተቆርቋሪነታችሁን ለገለፃችሁ ሁሉ በድጋሚ ምስጋናችንን እያቀረብን፤ ይህንን የተጓተተ ስራ በማጠናቀቅ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤቱን መልሰን ለእናንተው የምናሳውቅ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን ።

የከተማችንን ልማት ከነዋሪዎቿ ጋር በመሆን እናፋጥናለን!

06/09/2026
የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀ...
06/09/2026

የእመርታ ቀን

አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Address

Dejach Wube
Addis Ababa
DEJACHWUBE1888TAWOR

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 08:00 - 17:00
Sunday 08:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa City Administration Bureau Of Women, Children and Social Affair posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ababa City Administration Bureau Of Women, Children and Social Affair:

Shortcuts

Share