Gullele woreda 3 Communication

Gullele woreda 3 Communication ይህ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የፌስ ቡክ ገፅ ነው
ፔጃችንን ፎሎው በማድረግ አዳዲስና ትኩስ መረጃዎችን ያግኙ!! ፔጃችንን ላይክ በማድረግ በወረዳችን የሚከናወኑትን አበይት ጉዳዮች መረጃ ያግኙ

በመላው ኢትዮጵያ በክርስትና ጥላ ውስጥ በሚገኙ  ቤተ-እምነቶች ያሉ ክርስቲያኖች የትንሳኤን በዓል በተስፋ፣ በመስዋዕትነት እና በአዲስ መነሳት መንፈስ በአንድነት ያከብራሉ። ከሳምንታት የፆም፣...
12/04/2026

በመላው ኢትዮጵያ በክርስትና ጥላ ውስጥ በሚገኙ ቤተ-እምነቶች ያሉ ክርስቲያኖች የትንሳኤን በዓል በተስፋ፣ በመስዋዕትነት እና በአዲስ መነሳት መንፈስ በአንድነት ያከብራሉ። ከሳምንታት የፆም፣ ጥሞና እና ራስን የመመልከት ጊዜ በኋላ ፋሲካ በእውነተኛ አምልኮ፣ መንፈስን አድሶ፣ ቤቶችንም በደስታ ይሞላል። በዘመድ አዝማድ መጠያየቅ እና ማዕድ መካፈልም ፍቅርን ያዳብራል።

‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ዓመታዊውን የፋሲካ መዐድ ማጋራት ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር በአንድነት ፓርክ በጋራ መታደማቸው ለእውነተኛው የአንድነት መንፈስ ጉልህ ማሳያ ነው።

‎በዓለ ትንሳኤው በመላው ኢትዮጵያ የእምነት፣ ቤተሰባዊነት እና የመታደስ መንፈስ የሚታይበት ጊዜ ነው። ሁላችንም በዚህ የትንሳኤ መንፈስ ዛሬም፣ ነገም፣ ሰርክ ቤታችንን፣ ልባችንንም ለተቸገሩ ወገኖች እንክፈት! መልካም በዓል።

የትንሳኤ በዓልን ስናከብር እርስ በራስ በመረዳዳት እና አቅመ ደካሞችን በመደገፍ ሊሆን እንደሚገባ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር ተናገሩ! የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማ...
12/04/2026

የትንሳኤ በዓልን ስናከብር እርስ በራስ በመረዳዳት እና አቅመ ደካሞችን በመደገፍ ሊሆን እንደሚገባ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር ተናገሩ!

የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአብርሆት ቤተ መጻህፍት አቅመ ደካማ አረጋውያንን ጾም የማስፈሰክ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ማዕድ ያጋሩት የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና የአብርሆት ቤተ መጻህፍት ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር የጾሙን ወቅት በጸሎት ያሳለፉ አረጋውያን በትንሳኤ እለት በትውፊቱ መሰረት በሌሊት የማስፈሰክ መርሃ ግብር በአብርሆት ቤተ መጻህፍት ባለፉት አመታት ሲካሄደ መቆየቱን አስታውሰው ይህን መሰሉ በዓልን አብሮ የማክበር መርሃ ግብር ሊስፋፋ እና ሊጠናከር የሚገባው ነው ብለዋል።

ህብረተሰቡ በዓልን ሲያከብር በአከባቢው ያሉ አቅመ ደካሞችንና ለተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች የተጋለጡ ወገኖችን በማሰብ እርስ በእርስ በመረዳዳት እና በመደጋገፍ ሊሆን እንደሚገባም ነው አፈ ጉባኤዋ የተናገሩት።

12/04/2026
11/04/2026
እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!የትንሣኤ በዓል በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በዓል ነው። ሞት የተሻረበትና ሕይወት ዋስትና ያገኘበት ነው። ከሞት ባሻገ...
11/04/2026

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

የትንሣኤ በዓል በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በዓል ነው። ሞት የተሻረበትና ሕይወት ዋስትና ያገኘበት ነው። ከሞት ባሻገር ሕይወት፣ ከመቃብር ባሻገር ትንሣኤ መኖሩ የታወጀበት ነው። ሞት መጨረሻ መቃብር መዳረሻ አለመሆናቸው የተረጋገጠበት ነው። በአዳም ምክንያት ወደ ምድር የወረደው ሰው፣ በክርስቶስ ምክንያት ወደላይ የወጣበት ነው።

የዘንድሮውን ትንሣኤ የምናከብረው ሀገራችን ኢትዮጵያ በሚያልፍ ፈተና ውስጥ እንዳለች እያሰብን ነው። መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን። ብርሃን እንዳናይ የሚጋርዱ፣ በጥልቁ ጨለማ ጠፍተን እንድንቀር አሥረው ለመያዝ የሚሞክሩ ወጥመዶች ብዙ ናቸው። ወደ ተስፋ ምድር እንዳንሻገር የሚጎትቱ ሰበቦች ሞልተዋል። ዳሩ ግን ከሕማማቱ ወዲያ ትንሣኤ፣ ከዕንቅፋቱ ባሻገር ስኬት እንደሚጠብቀን አምነን እንታገላለን።

በትንሣኤው ዋዜማ - ርግጠኞች፣ ተስፈኞች፣ ተስፋ ቆራጮች፣ ወሬኞች፣ ተስፋ አስቆራጮች፣ ተጠራጣሪዎች ነበሩ። ርግጠኞቹ የሕማማቱ ፈተና እንደሚያልፍ ርግጠኞች ነበሩ። የዕለተ ስቅለት መከራ፣ለዕለተ ትንሣኤ ዋዜማ ለመሆኑ ርግጠኞች ነበሩ። የድንጋዩ በር፣ የበሩ ማኅተም እና የመቃብሩ ጠባቂዎች ትንሣኤውን እንደማያስቀሩት ርግጠኞች ነበሩ። የሚናፈሰው ወሬ እና የሚሠራጨው አሉባልታ እድሜው አጭር መሆኑን ርግጠኞች ነበሩ። ርግጠኞችም ስለሆኑ መሥዋዕትነትን ለመክፈል ዝግጁዎች ነበሩ። እውነቱን ለመመስከር ቆራጦች ነበሩ። በመስቀሉ ሥር ለመገኘት ደፋሮች ነበሩ።

ተስፈኞቹ የርግጠኞቹን ያህል ሳያዩ የሚያምኑ አልነበሩም። ግን አንዳች መልካም ነገር ይጠብቁ ነበር። የተሰጠውን ትምህርት፣ የተደረገውን ተአምራት ሰምተዋል፤ አይተዋል፤ አንዳች ነገርም ጠብቀዋል። ነገር ግን ተገቢውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁዎች አልነበሩም። እውነትን ለመድፈር ቆራጦች አልነበሩም። ሐሰቱን ለመጋፈጥ ዐቅም አላገኙም። ቢያንስ ግን አንደበታቸውን ከክፉ ከልክለዋል።

ተጠራጣሪዎች አጥር ላይ የነበሩ ናቸው። በጥብርያዶስ ይበላሉ፣ በጎልጎታ ይክዳሉ። በሆሳዕና ይዘምራሉ፣ በሊቶስጥራ ይሸሻሉ፡፡ ተአምር ለማየት ይመጣሉ፣መከራ ለማየት ይሳቀቃሉ፡፡ ከደስታው አውጡልኝ፣ ከመከራው ጦመኛ ነኝ የሚሉ ናቸው።

ተስፋ ቆራጮች በሚያዩትና በሚሰሙት ቶሎ የሚወሰዱ ናቸው። በእውነትና በሐሰት፣ በፍርሃትና በጽናት መካከል ያለው ድንበር የጠፋባቸው ናቸው። ሕማማቱ ሲመጣ በቶሎ ወደ ትዝታ ገቡ። ሁሉንም ነገር የትናንት ታሪክ ብቻ አድርገው ወሰዱት። ሁሉንም ነገር “ልጡ የተራሰ፣ መቃብሩ የተማሰ” አድርገው ቆጠሩት። ከግራ ከቀኝ የሚሰሙት አሉባልታ፣ ከፊት ከኋላ የሚመጣው ጫጫታ፤ ከወዲህ ከወዲያ የሚማጣው እሳት፣ ከዚህም ከዚያም የሚያዩት መዓት አስፈራቸው። ነገን አስረሳቸው። በዚህ የተነሣ ተስፋ ቆርጠው ወደ ኋላ ተመለሱ።

ወሬኞች ድሮም ወሬ ስቧቸው የመጡ ናቸው። ምን አለ ምን ተባለ ብለው የተሰባሰቡ ናቸው። የሰሙትንም ያልሰሙትንም፤ የሚያውቁትንም የማያውቁትንም፤ እውነቱንም ሐሰቱንም እያደባለቁ ኢየሩሳሌምን በወሬ ሞሏት። ቢያንስ ከትንሣኤው 15 ዓመት በኋላ ወንጌሉን የጻፈው ማቴዎስ፣ እስከዚያ ዘመን ድረስ ወሬው ብዙ ተቀባይ እንደነበረው ገልጧል።

ተስፋ አስቆራጮች ዓላማቸው ሰውን ሁሉ ከትንሣኤ መንገድ ማራቅ ነበር። እነርሱም አይሄዱ፣ ሰውም አያስኬዱ። ከመጀመሪያው አልተቀበሉትም፤ በኋላም አልፈለጉትም። ብዙ ሰዎች እንደተከተሉት ሲያውቁ ደግሞ ቅናት አቃጠላቸው፤ ክፋት አንገበገባቸው። ክርስቶስን ከሰሱ፤ ራሳቸው ምስክር ሆኑ፤ በመጨረሻም ራሳቸው ፈረዱ። መቃብሩን ዘጉ፤ ጠባቂ አስቀመጡ

የአፍሪኤግዚም ባንክ ፕሬዝደንት የሆኑትን ዶክተር ጆርጅ ኢሎምቢን ዛሬ ተቀብያለሁ። በነበረን የጋራ ቆይታ፣ ስትራቴጂካዊ ግንኙነታችንን በምናጠናክርባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገናል።Plea...
11/04/2026

የአፍሪኤግዚም ባንክ ፕሬዝደንት የሆኑትን ዶክተር ጆርጅ ኢሎምቢን ዛሬ ተቀብያለሁ። በነበረን የጋራ ቆይታ፣ ስትራቴጂካዊ ግንኙነታችንን በምናጠናክርባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገናል።

Pleased to receive Dr. George Elombi, President of Afrexim Bank, for discussions on strengthening strategic partnerships.

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

“የሰንበት ገበያዎች በቅርበት በማግኘታችን ድካም ቀንሶልናል፤ ገንዘባችንም ጊዜአችንም ቆጥቦልናል” ነዋሪዎች! ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፣  የሰንበት ገበያዎች በተከተማዋ በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳ...
11/04/2026

“የሰንበት ገበያዎች በቅርበት በማግኘታችን ድካም ቀንሶልናል፤ ገንዘባችንም ጊዜአችንም ቆጥቦልናል”
ነዋሪዎች!

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ፣ የሰንበት ገበያዎች በተከተማዋ በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ነዋሪው ባለበት መንደሮች ሁሉ፣ በቅርበት በመኖራቸው፣ ፍጆታዎችን ለመሸመት ይባክን የነበረውን ጊዜና ጉልበት ቀንሶልናል ሲሉ ምስክርነታቸውን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

በተለይም እነዚህ ገበያዎች በአቅራቢያቸው በማግኘታቸው የተለያዩ ምርቶችን ከአንድ ቦታ ሸምቶ ለመሄድ አስችሎልናል፣ ድካም ቀንሶልናል፣ የትራንስፖርት ወጪ አስቀርቶልናል፣ ከምንም በላይ ጥራት ያለው ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንድናገኝ አስችሎናል ሲሉ ይደመጣሉ፡፡

መንግስትም ለኑሮ ውድነት መባባስ መንስኤ የሆኑትን የምርት አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ፣ የፍጆታ እና የሰብል ምርቶች በቀጥታ ከአርሶ አደሮች እና ከባለሀብቶች ጋር በማስተሳሰር ምርት በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ከተማ እንዲገባ በማድረግ ሸማቹ ማህበረሰብ ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡

በዚህ ውጤታማ ስራ ለዋጋ ንረትና ለንግድ ሚዛን መዛባት ምክንያት የሆኑ ህገ-ወጥ ነጋዴዎች እና ደላሎች ላይ ህጋዊ እርምጃዎችን በመውሰድ በገበያው ላይ ይታይ የነበረውን የዋጋ ንረት ማረጋጋት ተችሏል፡፡

11/04/2026
10/04/2026

እንደ አዲስ ልዩ ፕሮግራም

ከአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ጋር

ነገ ምሽት 3 ሰዓት ይጠብቁን!

ሽንኩርት በኪሎ ከ25 ብር ጀምሮ በላፍቶ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ማግኘት ይቻላል!የትንሣኤ በዓል ገበያን ለማረጋጋት በትላልቅ የገበያ ማዕከላት ምርት በቅናሽ እየቀረበ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተ...
10/04/2026

ሽንኩርት በኪሎ ከ25 ብር ጀምሮ በላፍቶ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ማግኘት ይቻላል!
የትንሣኤ በዓል ገበያን ለማረጋጋት በትላልቅ የገበያ ማዕከላት ምርት በቅናሽ እየቀረበ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ ገለፁ

በዚህም ሽንኩርት በኪሎ ከ25 ብር ጀምሮ እየቀረበ መሆኑን ምክትል ከንቲባው ተናግረዋል

ምክትል ከንቲባው በዛሬው እለት በላፍቶ ሁለገብ የገበያ ማዕከል በመገኘት የበዓል ገበያ እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል።

​ምክትል ከንቲባው በጉብኝታቸው ወቅት እንደገለጹት በገበያ ማዕከሉ የፍጆታ ምርቶች በበቂ ሁኔታ እንዲገቡ ቀደም ብሎ በተሰራው ዝግጅት መሠረት አበረታች ውጤት ተመዝግቧል።

በተለይም በሁሉም የከተማዋ ክፍለ ከተሞች የምርት እጥረት እንዳይከሰት ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች እንደ ሽንኩርት፣ ቲማቲም እና ድንች ያሉ ሊበላሹ የሚችሉ ምርቶች በስፋት እንዲቀርቡ መደረጉን ገልጸዋል።

​ይህም ገበያውን ለማረጋጋት ትልቅ ድርሻ እንዳለው ገልፀው በላፍቶ ገበያ ማዕከል ለምሳሌ የሽንኩርት ምርት እንደየጥራቱ ከ25 ብር ጀምሮ እስከ 50 ብር እየተሸጠ መሆኑን ጠቁመዋል።

ይህም ማዕከሉ ምርትን በጅምላ ተረክቦ ወደ ሌሎች የከተማዋ አካባቢዎች ለማሰራጨት ያለውን ዝግጁነት ያሳያል።

ወቅታዊ ሁኔታዎችን ሰበብ በማድረግ ሰው ሰራሽ የዋጋ ጭማሪ ለመፍጠር ገበያ የተረጋጋ እንዳልሆነ አሉባልታ ለመንዛት የሚሞክሩ መኖራቸውን በመግለፅ ነጋዴዎችም ሆነ ሸማች ዛሬና ነገ ወደ ላፍቶ ሁለገብ የገበያ ማዕከል መጥቶ መግዛት እንደሚችል አሳስበዋል

​አልፎ አልፎ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የአቅርቦት ችግሮችንና ህገ-ወጥ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ "አጭበርባሪዎችን" ለመለየት የከተማ አስተዳደሩ ጥብቅ ክትትል እያደረገ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በላፍቶ ሁለገብ የገበያ ማዕከል የሚገኙ ነጋዴዎች በበኩላቸው የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ምርት በስፋት እንዲገባ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

በተለይም ሰሞኑን ያለአግባብ ዋጋው ጨምሮ የነበረው የሽንኩርት ምርት በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የዋጋ ቅናሽ እንዳሳየ ተናግረዋል።

​ነጋዴዎቹ አክለውም በአሁኑ ወቅት በማዕከሉ ያለው የምርት አቅርቦት ከአዲስ አበባ ፍላጎት አልፎ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ለክልሎችም የሚተርፍ በቂ ክምችት እንዳለም አንስተዋል።

Address

Haile Melekot Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gullele woreda 3 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gullele woreda 3 Communication:

Share