Gullele woreda 3 Communication

Gullele woreda 3 Communication ይህ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የፌስ ቡክ ገፅ ነው
ፔጃችንን ፎሎው በማድረግ አዳዲስና ትኩስ መረጃዎችን ያግኙ!! ፔጃችንን ላይክ በማድረግ በወረዳችን የሚከናወኑትን አበይት ጉዳዮች መረጃ ያግኙ

 #ጳጉሜ 1 የእመርታ ቀን!መንግስት ባመቻቸው የሌማት ቱሩፋት መጠቀማቸውን ተጠቃሚዎች ገለጹ፡፡**************************(ጉለሌ ወረዳ 3 ኮሙኒኬሽን 01/13/2018ዓ.ም)በጉለ...
06/09/2026

#ጳጉሜ 1 የእመርታ ቀን!

መንግስት ባመቻቸው የሌማት ቱሩፋት መጠቀማቸውን ተጠቃሚዎች ገለጹ፡፡
**************************
(ጉለሌ ወረዳ 3 ኮሙኒኬሽን 01/13/2018ዓ.ም)

በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 አስተዳደር ጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን”ን ምክንያት በማድረግ የከተማ ግብርና እንቅስቃሴን የሚያፋጥኑ የዶሮ እና የኬጅ ስርጭት ተከናወነ።

በዕለቱ የመንግስትን የሌማት ቱሩፋት መርሃ ግብር ተስፋ በማድረግ ተጠቃሚ መሆን መቻላቸውን የገለጹት የወረዳው ነዋሪዎች የተደረገላቸው ድጋፍ በቤተሰብ ደረጃ አምራች ለመሆን እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።

በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሽመልስ ጎዴቦ እንደገለጹት "የእመርታ ቀን" በርካታ ለውጦች የተመዘገቡባቸውና የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች ውጤታማ መሆናቸውንና ሃገራችን ኢትዮጵያ ወደ ማንሰራራት የምታደርገውን ጉዞ የሚያሳይ እንደሆነ ተናግረው፤ በሌማት ትሩፋት የምግብ ዋስትናን በተግባር በማረጋገጥና በማስፋፋት የስራ እድል በመፍጠር የሀገርን ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ስራ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አበባው አለምነህ በበኩላቸው "የእምርታ ቀን" ሲከበር ህብረተሰባችንን ከተረጂነት አስተሳሰብ እና ተግባር በማውጣት በሁሉም መስኮች አምራች እና ራስን ወደ መቻል ማሸጋገርን አላማ ያደረገ እንደሆነ ገልፀው፤ በኢኮኖሚ ራስን ከመቻል ባለፈ በገበታ ላይ የሚቀርበውን ምግብ በራስ አቅም ማምረት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴዎችን ጨምሮ የወረዳው አመራሮች፣ እና የአካባቢው ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን፣ የሌማት ትሩፋት ስራዎች ጉብኝትም ተካሂዷል።

06/09/2026
የ"ጎቤ" እና "ሺኖዬ" ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነውከክረምት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገርን የሚያበስረው “የጎቤ” እና “ሺኖዬ”ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡...
06/09/2026

የ"ጎቤ" እና "ሺኖዬ" ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው
ከክረምት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገርን የሚያበስረው “የጎቤ” እና “ሺኖዬ”ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡፡

በኦሮሞ ባህል ዘንድ የክረምቱን መውጣትና የጸደይ መዳረሻን ለማብሰር ከሚከናወኑ ባህላዊ ሥርዓቶች መካከል “የጎቤ” እና “ሺኖዬ” ጨዋታ ተጠቃሽ ነው።
AMN

06/09/2026
ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ እና በተለያዩ መንገዶች ከቦሌ - መገናኛ የቪአይፒ ኮሪደር ልማት አካል የሆነውና ቦሌ ብራስ አካባቢ በሚገኝ የመንገድ መሿለኪያ ውስጥ የተፈጠረውን የውሃ ማቆር ችግር ...
06/09/2026

ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ እና በተለያዩ መንገዶች ከቦሌ - መገናኛ የቪአይፒ ኮሪደር ልማት አካል የሆነውና ቦሌ ብራስ አካባቢ በሚገኝ የመንገድ መሿለኪያ ውስጥ የተፈጠረውን የውሃ ማቆር ችግር አስመልክቶ የሰጣችሁትን ጥቆማ በአክብሮት ተቀብለናል።

በእርግጥም የሰጣችሁት ጥቆማ ትክክል እና ተገቢነት ያለው ከመሆኑ በተጨማሪ ለከተማችን ልማት ያላችሁን ተቆርቋሪነት እና የኔነት ስሜት ያሳየ በመሆኑ ከልብ እያመሰገንን።

ይህ ያልተጠናቀቀው የምድር ውስጥ መሿለኪያ ቦታ የውሃ ማቆር ችግር ያጋጠመው፤ ቀደም ሲል ስራውን ይዞት ከነበረው ኮንትራክተር ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ምክንያት የውል መቋረጥ በማጋጠሙ እና የግንባታ መጓተት በመከሰቱ ሲሆን ፤ ይህንን ያልተጠበቀ ችግር በመረዳት ተቋማችን አፋጣኝ መፍትሄ ለመስጠት ሲሰራ ቆይቷል።

በመሆኑም ያልተጠናቀቀውን የመሿለኪያ የምድር ውስጥ ስራ ዳግም ለማስጀመር በፍጥነት የአዲስ ኮንትራት ግዢ ጨረታ በማውጣት ሂደቱ ተጠናቋል።

በመጨረሻም ሀሳባችሁን ለሰጣችሁ እና በኔነት ስሜት ተቆርቋሪነታችሁን ለገለፃችሁ ሁሉ በድጋሚ ምስጋናችንን እያቀረብን፤ ይህንን የተጓተተ ስራ በማጠናቀቅ በአጭር ጊዜ ውስጥ ውጤቱን መልሰን ለእናንተው የምናሳውቅ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን ።

የከተማችንን ልማት ከነዋሪዎቿ ጋር በመሆን እናፋጥናለን!

06/09/2026

የፕሬስ መግለጫእመርታ ለዘላቂ ከፍታ!እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል...
06/09/2026

የፕሬስ መግለጫ
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!
እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል፤ በዚያ አግባብ የሚመጣ መሻሻል ከታለመዉ ግብ ለመድረስ የትውልዶችን ጥረት የሚጠይቅ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን በቁጭት ለዘመናት ከቆየንበት ኋላ ቀርነት እና ድህነት በአዝጋሚ ጉዞ ለመላቀቅ ስለማይቻል እመርታዊ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርገን ሠርተን ስኬቶችን እያስመዘገብን ነው፡፡ ያለፉት ጥቂት ዓመታት ጥረቶቻችን ውጤቶች የሚያሳዩትም ይህንኑ ነው፡፡
የኢትዮጵያን ጀርባ ያጎበጡ የውጭ ዕዳዎችን ጫና በመቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅም በማሻሻል፣ የማዕድን ሀብቶች አጠቃቀምን በማላቅ እመርታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡ የመንግሥት አጠቃላይ የማድረግ ዐቅም በእጅጉ ተለውጧል፡፡ ይህንን እመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ የተቻለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በማድረግ፤ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል፤ የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በማሳደግ፤ የቢዝነስ ሥርዐቱን ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ዐቅም ከዜጋ ተኮር እና ብሔራዊ ጥቅም አንጻር በመግራት የመደመር መንግሥት ባደረገዉ ሰፊ ጥረት ነው፡፡
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ የኃላፊነት ስሜት በሕጋዊ አግባብ መጠቀም ጀምራለች፤ ታዳሽ ኃይልን በማምረት ከራስ አልፎ ለቀጠናዉ የኃይል ምንጭ ኾናለች፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመተግበር ኹለንተናዊ ዕድገቶችን እያስመዘገበች መጥታለች፤ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በዓለም ገበያ ተወዳድራ የመሸጥ ዐቅም ፈጥራለች፡፡ የመንግሥት የልማት ዕቅድ ከቁጥ ቁጥ ወጥቶ ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ግብ አስቀምጦ እየተተገበረ ነው፡፡ በ2018 ዓ/ም በሁሉም መስክ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ለውጥ የመሸጋገር ሀገራዊ ራዕይን ማሳካት ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያን በ2023 ዓ.ም አፍሪካዊት የብለጽግና ተምሳሌት የማድረግ ግብ ተቀምጦ ርብርብ እየተደረገ የስኬቱ ዋዜማ እየተቃረበ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር መንግሥት በተነደፉ የፖሊሲ ሐሳቦች ኹለንተናዊ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዞን ጀምራለች፡፡ በገቢ አሰባሰብ ላይ የታየዉ እመርታ አንዱ አብነት ነው፡፡ የግብር እና ታክስ መሠረትን በማስፋት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፤ የግብር ከፋዩን የመንግሥት አገልግሎት እርካታ በመሶብ አንድ ማእከል እና በዲጂታል አገልግሎቶች ከፍ በማድረግ የላቀ አፈጻጸም ማሳየት ተችሏል፡፡ በዚህም የበጀት ጉድለትን በእጅጉ ማጥበብ ተችሏል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት የመንግሥት ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ዐቅም በእጅጉ አድጓል፡፡ ፕሮጀክቶች መቼ እንደሚጀመሩ እና በምን ያህል በጀት እንደሚፈጸሙ ብቻ ሳይኾን መቼ ተጠናቅቀው በትክክል አገልግሎት እንደሚሰጡ ጭምር በከፍተኛ የራስ መተማመን የመሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ መናገር የሚቻልበት ቁመና ላይ ተደርሷል፡፡
እመርታዊ ስኬቶችን ዕውቅና ለመስጠት፣ በቀጣዮቹም ዓመታት የበለጠ እመርታዊ ስኬቶችን ለማስመዝገብ መዘጋጀት አስፈላጊ በመኾኑ ዛሬ ጳጒሜን 01 ቀንን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መሪ መልእክት እያከበርን ነው፡፡
እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
ጳጒሜን 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ See less

Address

Haile Melekot Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gullele woreda 3 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gullele woreda 3 Communication:

Shortcuts

Share