Ministry of Urban and Infrastructure/Ethiopia

Ministry of Urban  and Infrastructure/Ethiopia This is the official Facebook
page of FDRE, Ministry of Urban and Infrastructure This is the official Facebook page of Ministry of Urban and Infrastructure

እመርታችን ይቀጥላል!ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ትቆማለች!የተሻለ ነገን ዛሬ እንገነባለን!የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር
06/09/2026

እመርታችን ይቀጥላል!
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ትቆማለች!
የተሻለ ነገን ዛሬ እንገነባለን!

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር

እመርታችን ይቀጥላል!ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ትቆማለች!የተሻለ ነገን ዛሬ እንገነባለን!የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር
06/09/2026

እመርታችን ይቀጥላል!
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ትቆማለች!
የተሻለ ነገን ዛሬ እንገነባለን!

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር

06/09/2026
የፕሬስ መግለጫእመርታ ለዘላቂ ከፍታ!እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል...
06/09/2026

የፕሬስ መግለጫ

እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!

እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል፤ በዚያ አግባብ የሚመጣ መሻሻል ከታለመዉ ግብ ለመድረስ የትውልዶችን ጥረት የሚጠይቅ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን በቁጭት ለዘመናት ከቆየንበት ኋላ ቀርነት እና ድህነት በአዝጋሚ ጉዞ ለመላቀቅ ስለማይቻል እመርታዊ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርገን ሠርተን ስኬቶችን እያስመዘገብን ነው፡፡ ያለፉት ጥቂት ዓመታት ጥረቶቻችን ውጤቶች የሚያሳዩትም ይህንኑ ነው፡፡

የኢትዮጵያን ጀርባ ያጎበጡ የውጭ ዕዳዎችን ጫና በመቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅም በማሻሻል፣ የማዕድን ሀብቶች አጠቃቀምን በማላቅ እመርታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡ የመንግሥት አጠቃላይ የማድረግ ዐቅም በእጅጉ ተለውጧል፡፡ ይህንን እመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ የተቻለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በማድረግ፤ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል፤ የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በማሳደግ፤ የቢዝነስ ሥርዐቱን ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ዐቅም ከዜጋ ተኮር እና ብሔራዊ ጥቅም አንጻር በመግራት የመደመር መንግሥት ባደረገዉ ሰፊ ጥረት ነው፡፡

ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ የኃላፊነት ስሜት በሕጋዊ አግባብ መጠቀም ጀምራለች፤ ታዳሽ ኃይልን በማምረት ከራስ አልፎ ለቀጠናዉ የኃይል ምንጭ ኾናለች፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመተግበር ኹለንተናዊ ዕድገቶችን እያስመዘገበች መጥታለች፤ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በዓለም ገበያ ተወዳድራ የመሸጥ ዐቅም ፈጥራለች፡፡ የመንግሥት የልማት ዕቅድ ከቁጥ ቁጥ ወጥቶ ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ግብ አስቀምጦ እየተተገበረ ነው፡፡ በ2018 ዓ/ም በሁሉም መስክ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ለውጥ የመሸጋገር ሀገራዊ ራዕይን ማሳካት ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያን በ2023 ዓ.ም አፍሪካዊት የብለጽግና ተምሳሌት የማድረግ ግብ ተቀምጦ ርብርብ እየተደረገ የስኬቱ ዋዜማ እየተቃረበ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር መንግሥት በተነደፉ የፖሊሲ ሐሳቦች ኹለንተናዊ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዞን ጀምራለች፡፡ በገቢ አሰባሰብ ላይ የታየዉ እመርታ አንዱ አብነት ነው፡፡ የግብር እና ታክስ መሠረትን በማስፋት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፤ የግብር ከፋዩን የመንግሥት አገልግሎት እርካታ በመሶብ አንድ ማእከል እና በዲጂታል አገልግሎቶች ከፍ በማድረግ የላቀ አፈጻጸም ማሳየት ተችሏል፡፡ በዚህም የበጀት ጉድለትን በእጅጉ ማጥበብ ተችሏል፡፡

ባለፉት ጥቂት ዓመታት የመንግሥት ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ዐቅም በእጅጉ አድጓል፡፡ ፕሮጀክቶች መቼ እንደሚጀመሩ እና በምን ያህል በጀት እንደሚፈጸሙ ብቻ ሳይኾን መቼ ተጠናቅቀው በትክክል አገልግሎት እንደሚሰጡ ጭምር በከፍተኛ የራስ መተማመን የመሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ መናገር የሚቻልበት ቁመና ላይ ተደርሷል፡፡

እመርታዊ ስኬቶችን ዕውቅና ለመስጠት፣ በቀጣዮቹም ዓመታት የበለጠ እመርታዊ ስኬቶችን ለማስመዝገብ መዘጋጀት አስፈላጊ በመኾኑ ዛሬ ጳጒሜን 01 ቀንን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መሪ መልእክት እያከበርን ነው፡፡

እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

ጳጒሜን 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት"የእመርታ ቀንአባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነት...
06/09/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

"የእመርታ ቀን

አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!"

በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችል ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፣ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖ...
03/09/2026

በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችል ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፣ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ዛሬ መፈረሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት እንዳስታወቁት፣ ይህ አዲስ የሚቋቋመው ኩባንያ በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመ ሲሆን፣ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ደግሞ ለተቋሙ እስከ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ የፋይናንስ አስተዋፅኦ ያደርግበታል።

ይህ ተቋም ወደ ሥራ ሲገባ በባንክ ዘርፉ ውስጥ የሚታየውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን ችግር የሚቀርፍ ከመሆኑም በላይ፣ በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስ አቅርቦትን እንደሚያስገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አብራርተዋል።

በተጨማሪም ይህ አጋርነት መንግሥት በተመጣጣኝ ዋጋ የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ ያስቀመጠውን ግብ ለማሳካት፣ እንዲሁም በሀገራችን የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ይበልጥ ለማስፋት የሚያስችል ወሳኝ እርምጃ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ የመገንባት ጥረቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አረጋግጠዋል።

እየተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው ።ነሃሴ 27፣ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ እየተጠናቀቀ በሚገኘዉ 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ...
02/09/2026

እየተጠናቀቀ ያለው ዓመት ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶች የተመዘገቡበት ነው ።

ነሃሴ 27፣ 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

እየተጠናቀቀ በሚገኘዉ 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ እንደምትገኝ የሚያመላክቱ ስኬቶችን እንዳስመዘገበች የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ አገልግሎቱ የዘንድሮ የጳጒሜን ቀናት የሚከበሩበትን ዓውድ፣ የቀናቱን ስያሜ እና መሪ መልእክት ይፋ ያደረገበትን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

መግለጫዉን የሰጡት የአገልግሎቱ ሚኒስትር ድኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ “ጳጒሜን የኢትዮጵያ ማንሰራራት ወር ብሎ ለማክበር የሚያስችሉ ስኬቶች እየተጠናቀቀ ባለው ዓመት መመዝገባቸውን ገልጸዋል ፡፡

ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ቴክኖሎጂ ነክ ዓመታዊ ስኬቶችን በመግለጫቸዉ ያነሡት ሚኒስትር ድኤታዉ የጳጒሜን ቀናት በልዩ ልዩ ስያሜዎች እና ኹነቶች ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ አመላክተዋል፡፡ አካታች፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የተሳተፉበት ነፃ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተካሄደበት፣ ኅብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን በፅኑ መሠረት ላይ የሚያስቀምጥ አካታች እና የነበሩ ልዩነቶችን በመፍታት የጋራ ትልሞች ላይ እንዲተኮር የሚያስችል ሀገራዊ ምክክር በስኬት የተጠናቀቀበት፣ የውስጥ አንድነቷ የተጠናከረ እና የዲፕሎማሲ ዐቅሟ ያደገች ኢትዮጵያ የታየችበት ዓመት እንደነበር አቶ ከበደ በመግለጫቸዉ አመላክተዋል፡፡

ከኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አንጻር የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ለመፍጠር በወቅታዊ ዓለማቀፋዊ ቀውሶች ጭምር ታልፎ ስኬት የተመዘገበበት፣ የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር የተቻለበት፣ የዕዳ ጫና በከፍተኛ ደረጃ የቀነሰበት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅም ከ1.5 ትሪሊዮን ብር የተሻገረበት፣ የኢንዱስትሪ ምርታማነት እና የውጭ ምንዛሪ ግኝት ታሪካዊ ዕድገት ያስመዘገበበት፣ የወጪ ንግድ ገቢ ከ10.2 ቢሊዮን ዶላር የተሻገረበት፣ በአንድ ዓለማቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም ብቻ ከ13.2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ የኢንቨስትመንት የመግባቢያ ሰነድ የተፈረመበት እና በአብዛኛዉ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወደ ማውጣት ደረጃ የተሸጋገሩበት፣ የግብርና ምርት እና ምርታማነት በጋ ከክረምት በግብዓት አቅርቦት ታግዞ በከፍተኛ ደረጃ የጨመረበት ስኬታማ ዓመት ነበር፡፡

የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ያስቻሉ ከ100 በላይ የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎቶች የተስፋፉበት፣ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደትን በፅኑ መሠረት የሚያስቀምጥ እና ማኅበራዊ መስተጋብርን የሚያጎለብት ስኬታማ ምክክር የተደረገበት፣ የሕዝቡን የማኅበራዊ መሻቶች ለማሳካት ሰፋፊ የበጎ አድራጎት እና የመሠረተ ልማት ማስፋፋት ሥራዎች የተከወኑበት በውጤቱም ኢትዮጵያን ከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበት ዕድገት ማሸጋገር የተቻለበት ዓመት እንደነበር ክቡር አቶ ከበደ በመግለጫቸዉ አመላክተዋል፡፡

በታዳሽ ኃይል አቅርቦት፣ ግዙፍ መሠረታዊ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት እና ዐዳዲስ መሠረተ ልማቶችን ወደ ግንባታ በማስገባት የተመዘገቡ ተጨባጭ ውጤቶችንም ዳስሰዋል፡፡ የዐፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ እና የቢሾፍቱ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መጀመር ከሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል በክቡር ሚኒስትር ድኤታዉ በአብነት ተነሥተዋል፡፡ እነዚህን ስኬቶች፣ ከተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች እና በዕቅድ ከተያዙ ሀገራዊ ትልሞች ጋር በማስተሳሰር ኢትዮጵያ በማንሰራራት ላይ መኾኗንም አመላክተዋል፡፡
የጳጒሜን ቀናት “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል የጋራ መሪ መልእክት ይከበራሉ፡፡
ጳጉሜን 1 - የእመርታ ቀን፣
ጳጉሜን 2 - የማንሰራራት ቀን፣
ጳጉሜን 3 - የጽናት ቀን፣
ጳጉሜን 4- የኅብር ቀን እና
ጳጉሜን 5 - የነገ ቀን በሚሉ ስያሜዎች እንደ ቅደም ተከተላቸዉ በልዩ ልዩ ኹነቶች እንደሚከበሩ ያስታወቁት ሚኒስትር ድኤታዉ ለዚህም ቅድመ ዝግጅቶች እየተጠናቀቁ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል፡፡

ዜጎች በዐዲስ ዓመት ለግል ስኬቶቻቸዉ እንደሚያቅዱት ኹሉ ለኹለንተናዊ ሀገራዊ ብልጽግናም የሚጫወቱትን ሚና ታሳቢ እንዲያደርጉ፣ የመንግሥትን ፖሊሲ እና ስትራቴጂ እንዲሁም ዕቅድ ተገንዝበዉ ተሳትፏቸዉን እንዲያሳድጉ ለማነሣሣት ቀናቱ እንደሚከበሩም ገልጸዋል፡፡ የጳጒሜን ቀናቱን ስያሜ መሠረት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄዎች፣ የበጎ አድራጎት እና ማዕድ ማጋራት ተግባራት፣ ነፃ ጤና ምርመራ፣ የደም ልገሳ፣ የፓናል ውይይት እና መሰል መርሐ ግብሮች እንደሚኖሩም አስታውቀዋል፡፡

የፒያሳዎቹ ወግ፡ ከዘመናዊነት ማዕበል እስከ የኢኮኖሚው ሞተር«ፒያሳ» የሚለው ቃል በኢትዮጵያ የከተማ ሥነ ሕንጻ እና ማኅበራዊ ታሪክ ውስጥ ከቀላል የስፍራ መጠሪያነት እጅግ የራቀ ትርጉም አለ...
02/09/2026

የፒያሳዎቹ ወግ፡ ከዘመናዊነት ማዕበል እስከ የኢኮኖሚው ሞተር

«ፒያሳ» የሚለው ቃል በኢትዮጵያ የከተማ ሥነ ሕንጻ እና ማኅበራዊ ታሪክ ውስጥ ከቀላል የስፍራ መጠሪያነት እጅግ የራቀ ትርጉም አለው።

ፒያሳዎች የከተሞች የልብ ትርታ፣ የባህል መስተጋብር፣ የንግድ ማዕከል እና የዘመን መሻገሪያ ሕያው ድልድዮች ናቸው።

ታዋቂው አሜሪካዊ የታሪክና የከተማ ባህል ተቺ ሉዊስ ሙምፎርድ ከተማን ሲገልጻት፤ ከተማ በተፈጥሮ ውስጥ እንዳለ ዋሻ ወይም የጉንዳን ክምር ያለ እውነታ ብቻ ሳትሆን፤ በተመሳሳይ ጊዜ የሰው ልጅ የንቃተ-ህሊና የጥበብ ሥራ ጭምር መሆኗን ያነሳል።

አእምሮ በከተማ ውስጥ ቅርፅ ይይዛል፤ በምላሹም የከተማ ቅርጾች የአንድን ማኅበረሰብ አእምሮ ይቀርጻሉ። ሙምፎርድ እንደሚሞግተው ከተሞች የሰውን ልጅ ሥልጣኔና ማኅበራዊ ትስስር የሚመግቡ ሕያው የኪነ-ጥበብ መድረኮች ናቸው።

ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ ከተሞች በከፍተኛ ፍጥነት እየተተገበረ ባለው ሀገራዊ የኮሪደር ልማት እና የከተማ ዝመና ፕሮጀክት ምክንያት የሀገሪቱ አንጋፋ የሆኑት የአዲስ አበባ እና የሀዋሳ ፒያሳ ሰፈሮች የትናንት የጥበብና የማኅበራዊ ትስስር ትዝታቸውን ከዛሬው ዘመናዊ መልክ፣ ምቹ የኑሮ ዘይቤ እና ግዙፍ የኢኮኖሚ አቅም ጋር እያዋሃዱ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እየጻፉ ይገኛሉ።

የአዲስ አበባ ፒያሳ፡ ከትዝታ ማዕከልነት ወደ ግዙፍ የኢኮኖሚና የግብይት እምብርት..

የአዲስ አበባ ፒያሳ የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ መናገሻ ናት። በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ተቆርቁራ፣ በጣሊያን ወረራ ወቅት የተለየ የስነ-ሕንጻ ገጽታን የተላበሰችው ይህች ሰፈር፤ በሲኒማ ቤቶች፣ በጥንታውያን የወርቅ ቤቶች እና በስፖርት ካፌዎች የምትታወቅ የከተማዋ «ነፍስ» ናት።

የትናንቷ ፒያሳ የፍቅርና የውበት ማዕከል፣ ግብይት የሚደራባትና በሁሉ ተወዳጅ ሰፈር ነበረች። አሁን ግን የኮሪደር ልማቱን ተከትላ ፒያሳ ፊቷን ሙሉ በሙሉ ወደላቀ የከተሜነት ደረጃ ተቀይራለች።

ዛሬ ላይ ፒያሳ የመንገድ ማሳለጫ ብቻ ሳትሆን፣ ግዙፍ የኢኮኖሚና የሥራ ዕድል ፈጠራ ሞተር ሆናለች።

በግርማ ሞገስ የቆመው የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ አዲሱ የዓድዋ ገበያ ማዕከል እና ዘመናዊው የትራንስፖርት ተርሚናል አካባቢውን ወደ ከፍተኛ የንግድና የኢንቨስትመንት ማዕከልነት አሸጋግረውታል።

እነዚህ ዘመናዊ የግብይት ማዕከላት በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠራቸውም ባሻገር፣ ሸማቹ ማኅበረሰብ በአንድ ማዕከል የተሟላ አገልግሎት እንዲያገኝ አስችለዋል።

ቀድሞ የነበረውን መጨናነቅ በማስቀረት፤ ሰፋፊና ደረጃቸውን የጠበቁ የእግር ጉዞ መንገዶች፣ ደኅንነታቸው የተረጋገጠ የብስክሌት መስመሮች፣ እንዲሁም ነዋሪው አየር የሚቀበልባቸው አረንጓዴ ፓርኮች የፒያሳን የድሮ ድባብ ወደ ዘመናዊ የቅንጦት እና የዕረፍት መዳረሻነት ቀይረውታል።

የአካባቢው ነዋሪዎችም የድሮዋን ፒያሳ ትዝታ እያደሱ፣ ዛሬ ላይ የሚታየው ንጽህና፣ ውበትና ሥርዓት ያለው የንግድ እንቅስቃሴ ለትውልድ የምትመች ዘመናዊ ከተማን ማስረከቡን ይመሰክራሉ።

የሀዋሳ ፒያሳ፡ የጥበበኞች ማረፊያ እና የስማርት ሲቲ ጉዞ

ከአዲስ አበባ ወደ ደቡብ ስናመራ የምናገኛት የሀዋሳ ፒያሳ ደግሞ የራሷ የሆነ የተለየ የታሪክ ውበትና አዲስ የዝመና ጉዞ አላት።

በ1950ዎቹ የተመሠረተችው ሀዋሳ፣ ከሐይቁ በሚነፍሰው ቀዝቃዛ አየር፣ በብስክሌት ተጠቃሚዎቿ፣ በሰላማዊ ማኅበራዊ ኑሮዋ እና በቡና ባህሏ ትታወቃለች። ይህች ከተማ በታዋቂ ሀገር በቀል ከዋክብት እይታ ስትገለጽ ይበልጥ ደማቅ ትሆናለች።

ለምሳሌ ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም የከተማዋን እድገት በምድራዊት ገነት መስለው፣ "ሀዋሳ ለእኔ ጥሩ አትክልተኛ እንዳገኘው አይነት የአትክልት ሥፍራ ናት፤ ኃላፊነት የወሰደ፤ በተገቢው መልኩ ውሃ የሚያጠጣ እና የሚኮተኩት አካል ያላት ምርጥ ከተማ"ሲሉ አሞግሰዋታል።

የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ በበኩላቸው "የትም ብትሆን መንፈስህን ታድሳለህ... የተሸላሚነት ሥራዎቼ ንድፈ ሃሳብ የተገኙት በዚህች ከተማ ለማረፍ ስመጣ ነው" በማለት የሀዋሳን የፈጠራ ማነቃቂያነት መስክረዋል።

ዛሬ ላይ ይህችው የሀዋሳ ፒያሳ፣ በከተማዋ እየተተገበረ ባለው የኮሪደር እና የመሠረተ ልማት ግንባታ አማካኝነት ወደ ስማርት ሲቲ እየተለወጠች ትገኛለች።

የድሮዎቹ ዝቅተኛ ሕንጻዎች ቦታቸውን ለባለብዙ ፎቅ ሆቴሎች፣ ለዓለም አቀፍ ደረጃ ላላቸው የገበያ አዳራሾች እና ለዘመናዊ የንግድ ኮምፕሌክሶች ለቀዋል።

ይህ የንግድ መሠረተ ልማት መስፋፋት ሀዋሳን የሲዳማ ክልል ዋነኛ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ማዕከል ከማድረጉም በላይ፤ የአካባቢውን ኢኮኖሚ በማነቃቃት ለበርካቶች የሥራ ዕድል ፈጥሯል።

የጎዳናዎቹ መብራት፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ልማት ነዋሪውም ሆነ ጎብኚው ያለምንም ስጋት ሌሊትና ቀን እንዲንቀሳቀስና እንዲገበያይ ምቹ ሁኔታን ፈጥረዋል።

ከአዲስ አበባ እና ከሀዋሳ የፒያሳ ዝመናዎች ጀርባ አንድ ትልቅ ሀገራዊ የከተማ ፕላን ፍልስፍና አለ። ይኸውም «የመደመር መንግሥት» በተሰኘው መጽሐፍ ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው፣ መገንባት የምንፈልጋቸው የአዲሱ ዘመን ከተሞች አካታችነትን ማዕዘን ድንጋይ ያደረጉ መሆን አለባቸው።

በነባር ከተሞች እድሳትም ሆነ አዳዲሶችን ከመገንባት አኳያ ለአይበገሬነት ቅድሚያ መስጠት ያስፈልጋል፡፡ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ሆነው መታቀድና የከተማ ደኖችን ጨምሮ አረንጓዴ መሠረተ ልማቶችን ማካተት አለባቸው ይላል መጽሐፉ።

በመሆኑም፤ ዛሬ ላይ በሁለቱ ፒያሳዎች የምናየው የጎዳና ማስፋፋት፣ የፓርኮች ግንባታ እና የመሠረተ ልማት እድሳት እንዲሁ ለውበት ብቻ የተሠራ ሳይሆን፣ ከተሞቹ ሁኔታዎችን በቀላሉ ተላማጅ የሆነ የከተማ አወቃቀር እንዲኖራቸው ታስቦ ነው።

ይህ ተላማጅ አወቃቀር የንግድ እንቅስቃሴን በማሳለጥ፣ ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና የስነ ሕዝብ ለውጦችን በቀላሉ በማስተናገድ ከተሞች ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ የኢኮኖሚ ዋልታ ሆነው እንዲያድጉ ያስችላል።

አዲስ አበባ እና ሀዋሳ ዛሬ ላይ የሚያወጉን እውነት ቢኖር፤ የትናንቱ ጠባብ መንገድ እና ያረጁ ቤቶች ለአረንጓዴ አካባቢዎች፣ ለሰው ልጅ ምቹ ለሆኑ መንገዶች፣ ለዘመናዊ የግብይት ማዕከላት እና ለአየር ንብረት የማይበገሩ መሠረተ-ልማቶች ቦታቸውን መልቀቃቸው የማይቀሬ የዕድገት እና የስልጣኔ ጉዞ መሆኑን ነው።

የኢትዮጵያ ፒያሳዎች ትናንትም የፍቅር፣ የኪነ-ጥበብና የታሪክ መድረክ ነበሩ፤ ዛሬም የኢኮኖሚ ሞተር በመሆን፣ አካታችነትንና አይበገሬነትን መሠረት አድርገው በዘመናዊነት አሸብርቀው የነገዋን ውብ ኢትዮጵያ የሚከትቡ የሥልጣኔ አውራ ጎዳናዎች ሆነው ቀጥለዋል።

Address

Sudan Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ministry of Urban and Infrastructure/Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ministry of Urban and Infrastructure/Ethiopia:

Shortcuts

Share