05/07/2025
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃጸም የማጠቃለያ ግምገማ ማካሄድ ጀመረ
*፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
አዳማ፣ ሰኔ 28 ቀን2017 ዓ.ም (ኢ.ፌ.ፖ.ሚ)፦የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈፃጸም የማጠቃለያ ግምገማ በአዳማ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል::
የኢትዮጽያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ በግምገማው መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ሠራዊቱ ከተሰጠው ተልዕኮ ስፋት አንፃር በሁሉም መስክ ስኬታማ የሥራ አፈፃፀም የታየበት የሥራ ዘመን መሆኑን አንስተዋል።
አያይዘውም አዳዲስ አባላትን በብቃት በማሰልጠንና ነባር አመራርንና አባላትንም አቅም የበለጠ በማሳደግ የወንጀል መከላከል ስራዎች በውጤት እንዲታጀቡ የተደረገበት ዓመት መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም የሀገር ሰላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ ፀረ-ሰላም ኃይሎችን ከሌሎች የፀጥታና የደኅንነት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በተለይም በመዲናችን አዲስ አበባ በርካታ ሀገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ሁነቶች ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም እንዲከወኑ መደረጉንም ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ ተናግረዋል።
በተጨማሪም የማጠቃለያ ግምገማው በ2017 የሥራ ዘመን በተልዕኮ አፈጻጸማችን የነበሩ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል የታዩ ድክመቶችን ደግሞ በመቅረፍ ለ2018 በጀት ዓመት የምንዘጋጅበት መድረክ ነው ብለዋል።
በአዳማ የሚከናወነው ዓመታዊ የማጠቃለያ ግምገማ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከግምገማው መጠናቀቅ በኋላም በአዳማ ከተማ የአረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሀ-ግብር እንደሚከናወንም ክቡር ምክትል ኮሚሽነር ጀነራሉ ተናግረዋል።