Addis Ababa Police

Addis Ababa Police መሪ ቃል፦ በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!!!
እሴቶቻችን፡- ሙያዊ ብቃት፣ ምሉዕነት፣ ብዝሃነትን ማክበር፣ ሰብዓዊ መብት ማክበር
Motto: Protect with courage Serve with Compassion!

Values: Professionalism, Integrity, Respect for diversity, Respect for Human rights በጀግንነት መጠበቅ፤በሰብዓዊነት ማገልገልⵑ (Protect With Courage, Serve with Compassionⵑ)
እሴቶቻችን
ብዛህነትን ማክበር (Respect for Diversity)
ሙያዊ ብቃት (Professionalism)
ምሉዕነት ( Integrity )
ሰብዓዊ መብት ማክበር (Respect for Human Rights)

የሰው ሕይወት ያጠፋን  የፖሊስ አባልን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ/ም (አ...
08/05/2026

የሰው ሕይወት ያጠፋን የፖሊስ አባልን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ሚያዚያ 29 ቀን 2018 ዓ/ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ከቀኑ 10፡40 ላይ አቶ ተገኝ ባልቻን በክላሽን ኮፕ ጠመንጃ የገደለውን ረዳት ሳጅን ማቴዎስ ተመቸውን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አስታወቀ፡፡

ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ከዚህ ቀደም በሟች እና በፖሊስ አባሉ መካከል ጠብ ተፈጥሮ አቶ ተገኝ በፖሊስ ላይ ባደረሰው ጉዳት ታስሮ በዋስ መለቀቁን አስታውሷል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በእለቱ ሟች በሌላ ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ ተይዘው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ከሄዱ በኋላ ከመኪና ወርዶ ወደ ውስጥ እንዲገባ ሲጠየቅ አልገባም በሚል ግብ ግብ በመፍጠራቸው በአካባቢው ግርግር አጋጥሞ እንደነበር ፖሊስ ገልጿል፡፡

ምንም እንኳ ግለሰቡ ከፖሊስ አባላት ጋር ግርግር መፍጠራቸው ተገቢ ባይሆነም የፖሊስ አባሉ የፈፀመው ድርጊት ፍፁም ተቀባይነት የሌለው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት መሆኑን እና ፖሊስ ከቆመለት ዓላማ በተቃራኒ የተፈፀመ በመሆኑ ተቋሙን የማይወክል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ በግለሰቦች ላይ የሚፈፀምን መሰል ድርጊቶች የማይታግስ መሆኑን እና የግድያውን የምርመራ ውጤት በቅርቡ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

በተፈጠረው ድርጊት የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የተሰማውን ሀዘን በመግለፅ ለሟች ቤተሰቦቸ፣ ዘመድ አዝማዶች፣ ጓደኞች መፅናናትን ተመኝቷል፡፡
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”

በድርድር 15ሺህ ብር መደለያ የተቀበለች የነዳጅ ማደያ ሠራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለች፡፡***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ራህማ ሰዒድ ድርጊቱን የፈጸመችው ሚያ...
07/05/2026

በድርድር 15ሺህ ብር መደለያ የተቀበለች የነዳጅ ማደያ ሠራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለች፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ራህማ ሰዒድ ድርጊቱን የፈጸመችው ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ/ም በንፍስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዩ ቦታው ጀሞ አንድ አካባቢ ከሚገኝ የነዳጅ ማደያ ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት ላይ ነው።

የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3-A07522 ኢ.ቲ የሆነ የጭነት መኪና አሽከርካሪ ጃፋር ደቻሳ የተባለ ነዳጅ ለመቅዳት በሄደበት አጋጣሚ ግለሠቧ 20ሺ ብር መደለያ እንዲሰጣት ትጠይቃለች።

አሽከርካሪው ጉዳዩን ለመኪናው ባለቤት በማሳወቅ በድርድር 15ሺ ብር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በግለሰቧ የግል አካውንት ገቢ ያደርጋል። የገንዘቡ ዝውውር መደረጉን የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ በማረጋገጡ ግለሰቧን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

በአሁኑ ወቅት ከነዳጅ ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ ህገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል ጥምር የጸጥታ አካላት አስፈላጊውን ክትትልና ቁጥጥር እያደረጉ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። ተገልጋዩን በማጉላላትና ያልተገባ ጥቅምን ለማግኘት የሚደረጉ ህገ ወጥ ተግባራትን በጋራ መከላከል እንደሚገባ ፖሊስ ገልጿል።

ህብረተሰቡ ጥቆማ የመስጠት ልምዱን አጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባ በመሆኑ መረጃ ለመስጠትም ሆነ የፖሊስን አገልግሎት ለማግኘት በነጻ የስልክ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም እንዲሁም በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (Citizen Engagement Application) መጠቀም እንደሚቻል ተገልጿል።
*
ዘገባ፦ ዋና ሳጅን አባብል ከበደ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”

ለኮሪደር ልማት የተዘጋጀን ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ የዋጋ ግምት ያለውን የኤሌክትሪክ ኬብል የሰረቁ ግለሰቦች በህብረተሰቡ ጥቆማ እጅ ከፍንጅ ተያዙ፡፡***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28 ቀን 201...
06/05/2026

ለኮሪደር ልማት የተዘጋጀን ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ የዋጋ ግምት ያለውን የኤሌክትሪክ ኬብል የሰረቁ ግለሰቦች በህብረተሰቡ ጥቆማ እጅ ከፍንጅ ተያዙ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ሦስቱ ግለሰቦች ወንጀሉን የፈፀሙት ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ስፖርት ፌደሬሽን አካዳሚ ፊት ለፊት ከጠዋቱ 4 ላይ ነው።

አስመራ ነገራ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 47749 ኢት የሆነ ክሬን ተሽከርካሪ ሹፌር፣ ኤልያስ በርሄ የሹፌሩ ረዳት እና ወርቁ ኖራህ ተባባሪ በመሆን 9 ጥቅል እና አንድ ገመድ የሌለው የኬብል መጠቅለያ አጠቃላይ የዋጋ ግምቱ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣና ለኮሪደር ልማት ሊዘረጋ የነበረ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመድ ሲጭኑ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል፡፡

የኤሌክትሪክ ገመዶች አስጭናችሁ አምጡ ተብለን ነው በማለት ንብረቱን ሲጭኑ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ ሦስቱ ወንጀል ፈፃሚዎች ከነተሽከርካሪው እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን በቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የአደይ አበባ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ላይ በተደረገ ተጨማሪ ምርመራ የአዲስ አበባ ከተማ ኮሪደር ልማት ሰራተኞች አለመሆናቸው ተረጋግጧል።

ወንጀል ፈፃሚዎቹ እጅ ከፍንጅ እንዲያዙ የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ መሆኑን ፖሊስ ገልፆ የወንጀል ፈፃሚዎች መያዝ ህብረተሰቡ ከፖሊስ ጋር ያለው ቁርኝት ይበልጥ እየጠነከረ መምጣቱን ጥሩ ማሳያ እንደሆነ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል፡፡ የህብረተሰቡ ተሳትፎ ትልቅ ምስጋና የሚቸረውና ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባ መሆኑን ዋና ጠቅላይ መምሪያው አስታውቋል፡፡
*
ዘገባ፦ ዋና ሳጅን ደጀኔ ኡልፋታ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”

የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ለከፍተኛ አመራሮች ዝውውርና ምደባ ሰጠ።***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ...
05/05/2026

የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ለከፍተኛ አመራሮች ዝውውርና ምደባ ሰጠ።
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የከተማዋን ሠላምና ደህንነት የተሳለጠ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሠጣጥን ተደራሽ ለማድረግ ለከፍተኛ አመራሮች ዝውውርና ምደባ ሠጥቷል። በዚህም መሠረት፦

1). ም/ኮሚሽነር አህመዲን ጀማል ---የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
2). ም/ኮሚሽነር ዮሃንስ ጭልጆ --- በዋና መምሪያ ማዕረግ የዋና ጠቅላይ መምሪያው አማካሪ
3). ም/ኮሚሽነር ሽመልስ ሽፈራው --- የለሚኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
4). ም/ኮሚሽነር ገናናው ጥበቡ --- የጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
5). ም/ኮሚሽነር ሰዒድ አህመድ ---- የሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ኋላፊ
6). ረ/ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋ --- የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
7). ረ/ ኮሚሽነር መኮነን አሻግሬ ---- የየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
8). ረ/ኮሚሽነር ሞቱማ ሲማ --- የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
9). ረ/ኮሚሽነር ግርማ ተሰማ ---- የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
10). ረ/ኮሚሽነር አይናለም በየነ --- የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
11). ረ/ኮሚሽነር መስፍን ሰብስቤ --- የሰው ኃብት ልማት ዋና መምሪያ ኃላፊ
12). ኮማንደር ያሲን ሁሴን ---- የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
13). ኮማንደር ዘውዴ በላይ ---- የቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
14). ኮማንደር አራጌ እሸቴ ---- የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዥ
15). ኮማንደር በኃይሉ ደጀኔ ---- በዋና መምሪያ ማዕረግ የጠቅላይ መምሪያው የሰው ኃብት ልማት አማካሪ
16). ኮማንደር አብይ መብራቱ --- የፎረንሲክ መረጃ ማሰባሰብ ዋና መምሪያ ኃላፊ
17). ኮማንደር ባህሩ ወ/ዩሐንስ --- የዋና ጠቅላይ መምሪያ ልዩ ፅ/ቤት ኃላፊ በመሆን ከሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ የተመደቡ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እያስታወቀ አመራሮቹ ህዝብና መንግስት የጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጡም ዋና ጠቅላይ መምሪያው አሳስቧል።
*
ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”

በውጪ ሀገር ዜጋ ላይ የስርቆት ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በፖሊስ ክትትል ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ዋሉ።‎***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ አብዲ ሀሰን እ...
03/05/2026

በውጪ ሀገር ዜጋ ላይ የስርቆት ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች በፖሊስ ክትትል ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ዋሉ።
‎***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ አብዲ ሀሰን እና ቃልዓብ ወርቁ የተባሉት ተጠርጣሪዎች ሚያዚያ 23 ቀን 2018 ዓ/ም በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ኢሰመኮ አካባቢ ነው የስርቆት ወንጀሉን የፈጸሙት።

ኢብራሂም ሀሰን የተባሉ የዩናይትድ አረብ ኢምሬት ዜግነት ያላቸው የግል ተበዳይ በአካባቢው ካለ ሱፐር ማርኬት ዕቃ ገዝተው ወደ አረፉበት ሐያት ሪጀንሲ ሆቴል እያመሩ ሳለ ተጠርጣሪዎቹ በግራና በቀኝ ሆነው በማዋከብ አንደኛው ተጠርጣሪ ሄድ ፎን ግዛን ሲል ሁለተኛው ተጠርጣሪ ከግል ተበዳይ ኪስ ውስጥ በመግባት ግምቱ 2 መቶ ሺ ብር የሚያወጣ አይፎን15 ፕሮማክስ ሞባይል ስልክ በማውጣት ከአካባቢው መሰወራቸውን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የባምቢስ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።

‎ፖሊስ የደረሰውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ ፈጣን የሆነ የምርመራ እና የክትትል ስራ በመስራት ሁለቱንም ተጠርጣሪዎች በሰዓታት ልዩነት ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ሊያውላቸው መቻሉን አስታውቋል።

‎ራስን ባልተገባ መንገድ ለማበልጸግ መሠል የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚገቡ አካላት ከፖሊስ አይን እና ከህግ ተጠያቂነት እንደማያመልጡ አውቀው ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።
*
ዘገባ፦ ም/ሳጅን መልካሙ ዜና
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”

የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ።***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ ...
02/05/2026

የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ።
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ አድራጎት የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ዱባይ፣ ኒውዮርክ፣ ቤይጂንግ እና ናይሮቢ ሲካሄድ ቆይቶ ነገ ዕሁድ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ/ም በአዲስ አበባ ይከናወናል።

ሩጫው ከመስቀል አደባባይ መነሻውን አድርጎ በለገሀር መብራት፣ በብሔራዊ ቴአትር መብራት አድርጎ የቀድሞው EBC መብራት ላይ ዞሮ በሠንጋ ተራ መብራት፣ በሜክሲኮ አደባባይ፣ በቡናና ሻይ ለገሀር በማድረግ ፍጻሜው መስቀል አደባባይ ይሆናል። ይህ የጎዳና ላይ ሩጫ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅም የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ።

በዚህም መሠረት፦
👉 ከቅዱስ ዑራኤል ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ ወይም መቅረዝ ሆስፒታል ላይ)
👉 ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
👉 ከጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ጥላሁን አደባባይ ላይ )
👉ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ለገሀር መብራት ላይ)
👉 ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድየም (ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ላይ)
👉 ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ሀራምቤ መብራት ላይ)
👉ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተ መንግስት መስቀለኛ ላይ) ከንጋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የሩጫ ፕሮግራሙ እስኪጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ዝግ ይሆናሉ።

በተጨማሪ ለዚሁ ፕሮግራም ሲባል ከዛሬ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስመሮቹ ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በጥብቅ እያሳሰበ ህብረተሰቡ ማንኛውም ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በነጻ የስልክ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም በ011-1-26-43-59፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (Citizen Engagement Application) EFPApp በመጠቀም ጥቆማ መስጠት እንደሚገባም ጥሪውን አቅርቧል።
*
ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”

ለጌርጌሴኖን የአእምሮ ሕሙማን መርጃና ማገገሚያ ማዕከል ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ልዩ ልዩ የፅዳት ዕቃዎች ድጋፍ ተደረገ።***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ...
02/05/2026

ለጌርጌሴኖን የአእምሮ ሕሙማን መርጃና ማገገሚያ ማዕከል ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ልዩ ልዩ የፅዳት ዕቃዎች ድጋፍ ተደረገ።
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ጌርጌሴኖን የአእምሮ ሕሙማን መርጃ እና ማገገሚያ ማዕከል በአእምሮና በተለያዩ ህመሞች ተይዘው በየጎዳናውና በየአምልኮ ስፍራዎች ወድቀው የሚገኙ ወገኖቻችንን ለመርዳት የተቋቋመ ሀገር በቀል የበጎ አድራጎት ማዕከል ሲሆን የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያም በስሩ ካሉ ፖሊስ ጣቢያዎች ከአባላትና አመራሮች ያሰባሰበውን የፅዳት ዕቃዎች ድጋፍ አበርክቷል።

የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ረ/ኮሚሽነር አይናለም በየነ ፖሊስ ከህዝብ ወጥቶ ህዝብን የሚያገለግል፣ ወንጀልን ከመከላከል ባሻገር በርካታ የበጎ አድራጎት ስራዎች የሚሰራ መሆኑን ተናግረው የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያም በስሩ ከሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች አመራርና አባላት ጋር በመሆን በጌርጌሴኖን የአእምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት ከግማሽ ሚልዮን ብር በላይ የሚያወጡ ልዩ ልዩ የፅዳት መጠበቅያ ቁሳቁሶች እንዳበረከቱ ገልፀዋል።

የጌርጌሴኖን የአእምሮ ሕሙማን መርጃ እና ማገገሚያ ማዕከል መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ መለሰ አየለ በበኩላቸው የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ለማዕከሉ ላደረገው ድጋፍ ምስጋና በማቅረብ ፖሊስ ከመደበኛ ስራው ባሻገር በበጎ ተግባር በመሳተፍ ካለው ቀንሶ ለማዕከሉ የፅዳት ማስጠበቅያ ድጋፍ መስጠቱ ለሌሎችም በአርአያነት የሚጠቀስ ተግባር በመሆኑ ሁሉም ከዚህ ተሞክሮ በመውሰድ ድጋፍ እንዲያደርግልን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

አመራርና አባላቱ ባከናወኑት ተግባር ትልቅ የህሊና እርካታ እንደተሰማቸው በመግለፅ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህላችንን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።
*
ዘገባ፦ ም/ሳጅን ፍሬወይኒ ገ/ጻዲቅ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!"

ለወንጀል መንስኤ የሚሆኑ ህገ ወጥ ተግባራትን አስቀድሞ በመከላከልና በማስወገድ የተጠያቂነት አሰራርን ማስፈን እንደሚገባ ተገለፀ፡፡***  አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ...
01/05/2026

ለወንጀል መንስኤ የሚሆኑ ህገ ወጥ ተግባራትን አስቀድሞ በመከላከልና በማስወገድ የተጠያቂነት አሰራርን ማስፈን እንደሚገባ ተገለፀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ መከላከል ም/ጠቅላይ መምሪያ ከተማዋን ከማንኛውንም የወንጀል ስጋት የፀዳች እንድትሆን በቅድመ ወንጀል መከላከልና በወንጀል መከላከል ተግባራቱ በርካታ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል፡፡

ከማዕከል እስከ ፖሊስ ጣቢያዎች በተዘረጋው የማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎት አደረጃጀትን ከሚመሩ በየደረጃው ከሚገኙ አመራርና አባላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡

ውይይቱን የመሩት የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት መምሪያ ኃላፊ ረ/ኮሚሽነር አለማየሁ አያልቄ እነዚህ ውጤቶች የተመዘገቡትም ህብረተሰቡ ወንጀልን አስቀድሞ በመከላከል ሂደት ተሳታፊ እንዲሆን በማድረግና ተፈፅሞ ሲገኝም መረጃን ከመስጠት ጀምሮ በፍርድ ቤት ምስክር እስከመሆን በሚደርስ የህብረተሰቡ ተሳትፎ መሆኑን በመግለፅ ለህብረተሰቡም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

ህብረተሰቡ የወንጀል መከላከል ስራዎቻችንን እንዲያግዝ በላቀ ደረጃ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን ከመስራት ባሻገር በየቀጠናው አካባቢውን እንዲጠብቅና ወንጀል ሲፈፀምም እጅ ከፍንጅ የመያዝ ተግባራቱን እንዲያጠናክር መደረግ እንዳለበትም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

የወንጀል መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በጥናት በመለየት አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ የተናገሩት የውይይቱ ታዳሚዎች በበኩላቸው ህብረተሰቡ ወንጀልን ከመከላከል ባሻገር የፀጥታ ስራው የእኔ ነው በሚል መንፈስ የማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎት ማዕከላት ግንባታዎች ላይ እያደረገ ያለው ከፍተኛ አስተዋፅኦ በገንዘብ የሚተመን ባለመሆኑ ሊመሰገን ይገባልም ብለዋል፡፡
*
ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!"

ከ6 ዓመት በላይ ሲሰራበት የነበረውን እና ለስራ የተሰጠውን ተሽከርካሪ የሸጠው ሾፌር በእስራት ተቀጣ፤ የተሽከርካሪው ሠሌዳና ቀለም ተቀይሮ ተገኝቷል፡፡***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 23 ቀን 20...
01/05/2026

ከ6 ዓመት በላይ ሲሰራበት የነበረውን እና ለስራ የተሰጠውን ተሽከርካሪ የሸጠው ሾፌር በእስራት ተቀጣ፤ የተሽከርካሪው ሠሌዳና ቀለም ተቀይሮ ተገኝቷል፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የሠሌዳ ጥቁር ኮድ 1-37226 አ/አ ሚኒባስ አሽከርካሪ የሆነው አሽናፊ ታደሰ ለስራ የተሰጠውን ተሽከርካሪ ይዞ መጥፋቱ ያሳሰባቸው የመኪናዋ ባለንብረት ወ/ሮ አስራት በየነ ጉዳዩን ለፖሊስ ያሳውቃሉ፡፡

ፖሊስ የደረሰውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ ባሰባሰበው መረጃ ሾፌሩ መኪናውን በ280ሺ ብር ሸጦ ከሀገር ለመውጣት ጥረት ሲያደርግ ጅግጅጋ ከተማ ላይ በቁጥጥር አውሎታል፡፡

በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካራማራ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ንብረቱን ለማስመለስ ባደረገው ጥረት መኪናውን የገዛውን ያብስራ አበራን በቁጥጥር ማዋሉን አስታውቋል፡፡

መኪናውን የገዛው ግለሰብ ከዚህ በፊት ሰማያዊ በነጭ የነበረውን የተሽከርካሪውን ቀለም ሙሉ በሙሉ ነጭ በማስቀባት እንዲሁም ኮድ 1-37226 አ/አ የነበረውን ሰሌዳ ወደ ኮድ 3-ኦሮ 93124 በመቀየር የኋላ ወንበር ሙሉ በሙሉ በመፍታትና የመኪናውን ዕቃ መጫኛ በመንቀል ተሽከርካሪው ሌላ ይዘት እንዲኖረው በማድረግ ሻሽመኔ ከተማ ዲዳ ቦቄ በሚባል መንደር በአንድ መኖሪያ ግቢ ውስጥ መኪናውን ደብቆ ተገኝቷል፡፡

ግለሰቡ ከዚህ ቀደም ሲጠቀምበት የነበረ በአሁኑ ወቅት ግልጋሎት የማይሰጥ መኪናን ሰሌዳ በመለጠፍ ሲንቀሳቀስ እንደነበር ታውቋል፡፡

ፖሊስ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ የምርመራ መዝገቡ ለአቃቤ ህግ በመላክ ዋናው ወንጀል ፈፃሚ በሆነው አሽናፊ ታደሰ ክስ እንደ እንዲመሰረት አድርጓል፡፡

የአሽናፊ ታደሰን ጉዳይ የተመለከተው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቦሌ ምድብ ፈጣን ችሎት ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት ግለሰቡ በ4 ዓመት ከ11 ወር እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡ ተሽከርካሪውን የገዛው ያብስራ አበራ የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበት በማረፊያ ቤት የሚገኝ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

መኪናዋን የሸጠው ግለሰብ ለ6 ዓመት በረዳት እና ለአንድ ዓመት በሾፌርነት በሸጣት መኪና ላይ ሲሰራ እንደነበር ታውቋል፡፡

የተሰረቀ ንብረት የሚገዙ ግለሰቦች ለወንጀል መስፋፋት መንስኤ መሆኑን የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የተሰረቀ ንብረት በሚያሻሽጡ እና በሚገዙ ወንጀል ፈፃሚዎች ላይ የጀመረውን ቁጥጥር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!"

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የፖሊስ ቻሌንጅና የማዕረግ ሽግግር ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮችን አስመረቀ፡፡ ***አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 22 ቀን 2018 ዓ/ም (አ...
30/04/2026

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የፖሊስ ቻሌንጅና የማዕረግ ሽግግር ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮችን አስመረቀ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 22 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በቅርቡ ተመድበው የመጡት ስትራቴጂክ አመራሮች ባስጀመሩት ሁለገብ ተቋማዊ የሪፎርም ስራ የከተማውን ሠላምና ፀጥታን ይበልጥ አስተማማኝ ለማድረግ በየዕርከኑ ለሚገኙት የፖሊስ አመራርና አባላት የተለያዩ ሙያዊ ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡

ጠቅላይ መምሪያው በተለያየ የእርከን ደረጃ ለሚገኙና የማዕረግ ማግኛ ጊዜያቸው ለደረሰ መካከለኛና ከፍተኛ አመራሮች ቢሾፍቱ በሚገኘው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ አየር ኃይል የቻሌንጅ ስልጠና ሲሰጥ ቆይቶ ዛሬ ሚያዝያ 22 ቀን 2018 ዓ/ም አስመርቋል፡፡

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌተናል ጀነራል አስራት ደኔሮ፣ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ መከላከል ም/ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ም/ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድ፣ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ምክትል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ም/ኮሚሽነር እርዚቅ ኢሳ፣ የአየር ወለድ ኮማንዶ ምክትል አዛዥ ሻለቃ ደጀኔ ረጋሳን ጨምሮ የተለያዩ ከፍተኛ የፖሊስ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በምስረታቸው ረጅም ዕድሜ ካስቆጠሩ መንግስታዊ ተቋማት አንዱ መሆኑን የገለፁት የጠቅላይ መምሪያ አዛዡ ሌ/ጀነራል አስራት ደኔሮ ፖሊስነት ሀገርንና ህዝብን በታማኝነት በማገልገል በሚገኝ ርካታ ውስጥ ያለ ሙያ እንደመሆኑ መጠን ተመራቂ አመራሮች በስልጠና ቆይታቸው የቀሰሙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር የተጣለባቸውን ህዝባዊ ኃላፊነት በብቃት እንዲወጡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ ዋና መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ተከታይ ያዜ ባቀረቡት የስልጠና አፈፃፀም ሪፖርት ተመራቂዎች የፖሊስ ቻሌንጅና የማዕረግ ሽግግር ስልጠናን በከፍተኛ የአዕምሮ ዝግጁነትና የመንፈስ ፅናት በብቃት ማጠናቀቃቸውን ገልፀዋል።

ተመራቂዎች በስልጠና ወቅት ያሳዩት መልካም ስነ ምግባርና ፖሊሳዊ ብቃት የተላበሰ እንቅስቃሴያቸው ከፍተኛ መሆኑን በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ ወታደራዊ ስልት ክፍል ኃላፊ ሻለቃ ጉዑሽ ግደይ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ስትራቴጂክ አመራሮች እየተከናወኑ ያሉ በርካታ ሰው ተኮር ስራዎች ውጤታማና የሚያስመሰግኑ መሆናቸውን የተናገሩት ተመራቂዎች በስልጠና ያገኙትን እውቀት ካላቸው ልምድ ጋር በማጣመር ፖሊሳዊ አገልግሎትን ከማሳደግ አንፃር መንግስትና ህዝብ የጣለባቸውን ኃላፊነታቸውን በብቃት ለመወጣት ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
*
ዘገባ፡- ዋና ሳጅን ጤናው ፈጠነ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!"

አንድ የተሰረቀን ሞባይል ስልክ መነሻ በማድረግ በተደረገ ክትትል በተለያዩ ጊዜያት ከተለያዩ ግለሰቦች የተሰረቁ 7 ስልኮች ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡***አዲስ አበባ፤ ሚያ...
29/04/2026

አንድ የተሰረቀን ሞባይል ስልክ መነሻ በማድረግ በተደረገ ክትትል በተለያዩ ጊዜያት ከተለያዩ ግለሰቦች የተሰረቁ 7 ስልኮች ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 21 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የግል ተበዳይ አቶ ይስሀቅ ጥበቡ ይባላሉ፤ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2፡30 ሠዓት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው ደራርቱ ህንፃ አካባቢ ማንነቱ ያልታወቀ ተጠርጣሪ ከተሽከርካሪያቸው ውስጥ S 24 ሳምሰንግ ሞባይል ሰርቆ ያመልጣል።

የግል ተበዳይ የተፈፀመባቸውን የወንጀል ድርጊት ለቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያመለክታሉ፤ ፖሊስ የቀረበለትን አቤቱታ መነሻ በማድረግና ቴክኖሎጂን በመጠቀም ተገቢውን የወንጀል ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

ከክትትል ቡድኑ የተገኘ መረጃን መነሻ በማድረግም የተሰረቀው ስልክ ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ/ም በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ሲዳሞ ተራ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከተቀባዩ ዳውድ ኮላ ከተባለ ግለሰብ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎታል፡፡

ፖሊስ የመጀመሪያውን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር በማዋል ባደረገው ምርመራ የማስፋት ተግባርም አብዱ ወኪል ገዙ ከተባለ ግለሰብ የተሰረቀውን ስልክ እንደተገዛ በመድረሱ በተጠቀሰው ግለሰብ ላይም ተገቢውን የመያዝ ስራ ተሰርቷል፡፡

ተጠርጣሪው አብዱ ወኪል ገዙ በተያዘበት ወቅት በተደረገበት የአካል ፍተሻም ከተለያዩ ግለሰቦች የተሰረቁ 5 አይፎን፣ 1 ቴክኖ፣ 1አልትራ 23 በጥቅሉ 7 የሞባይል ስልኮች በእጁ ላይ የተገኙ በመሆኑ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተጨማሪ ምርመራ የማስፋት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ከቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ ያመለክታል ።
የተሰረቁ ንብረቶችን ከወንጀል ፈጻሚዎች የሚቀበሉ አካላት ከድርጊታቸው መቆጠብ እንዳለባቸው ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መሰል የስርቆት ወንጀል የተፈፀመባቸው ግለሰቦች በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመቅረብ ስልኮቻቸውን መምረጥ እንደሚችሉም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
*
ዘገባ፡- ዋና ሳጅን ደጀኔ ኡልፋታ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል

Address

Arada Sub City , Addis Ababa Police
Addis Ababa
5647

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa Police posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ababa Police:

Share