Addis Ababa Police

Addis Ababa Police መሪ ቃል፦ በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!!!
እሴቶቻችን፡- ሙያዊ ብቃት፣ ምሉዕነት፣ ብዝሃነትን ማክበር፣ ሰብዓዊ መብት ማክበር
Motto: Protect with courage Serve with Compassion!
(244)

Values: Professionalism, Integrity, Respect for diversity, Respect for Human rights በጀግንነት መጠበቅ፤በሰብዓዊነት ማገልገልⵑ (Protect With Courage, Serve with Compassionⵑ)
እሴቶቻችን
ብዛህነትን ማክበር (Respect for Diversity)
ሙያዊ ብቃት (Professionalism)
ምሉዕነት ( Integrity )
ሰብዓዊ መብት ማክበር (Respect for Human Rights)

በአራዳ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የጃን ሜዳ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አመራርና አባላት ታካሚዎችን ጎበኙ፡፡***አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- በአራዳ ክ/ከተማ...
26/08/2026

በአራዳ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የጃን ሜዳ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አመራርና አባላት ታካሚዎችን ጎበኙ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- በአራዳ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የጃን ሜዳ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አመራርና አባላት በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በመገኘት በሆስፒታሉ የሚገኙ ታካሚዎችን ጎበኙ።

የጃን ሜዳ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፔክተር ስጦታው ቡጤ ታካሚዎች በተጎበኙበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ፖሊስ መምሪያው እንደዚህ ያሉ ማህበራዊና ሰብዓዊ ተግባራትን በተቀናጀ መልኩ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው ፖሊስ ከተሰጠው ተልዕኮ በተጨማሪ በመሰል ማህበራዊ ጉዳዮች የሚያደርገው ተሳትፎ አንዱ ማሳያ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

የፖሊስ መምሪያው የወንጀል መከላከል ም/መምሪያ አዛዥ የሆኑት ኢንስፔክተር ተሬሳ ጋዲሳ የፖሊስ ተግባር ወንጀልን መከላከልና ህግን ማስከበር ብቻ ሳይሆን፣ ማህበራዊ ኃላፊነትንም መወጣት በመሆኑ መሰል ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል፡፡

የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የህንፃ አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ፊራፊስ አቡና በበኩላቸው ፖሊስ በሆስፒታሉ በመገኘት ያደረገው ድጋፍ የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም የህዝብ አገልግይነቱም አንዱ ማሳያ ነው ብለው ሆስፒታሉና ፖሊስ መምሪያው በጤናና በማህበራዊ ጉዳዮች በጋራ እንደሚሰሩም ተናግረዋል፡፡

የፖሊስ መምሪያው አመራርና አባላትም ለታካሚዎች ምግብና መጠጦችን በስጦታ በማበርከት ከህመማቸው እንዲፈወሱም መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡
*
ዘገባ፡- ም/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
‎*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
በጀግንነት መጠበቅ ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል!
Protect with Courage, Serve with Compassion!
🇪🇹

የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በመገኘት የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ ***አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲ...
26/08/2026

የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በመገኘት የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ አበባ)፦ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በተገኙበት ወቅት የዋና ጠቅላይ መምሪያው አዛዥ ሌ/ጀነራል አስራት ደኔሮ፣ የወንጀል መከላከል ምክትል ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ም/ኮሚሽነር ቶፊቅ መደድ፣ የወንጀል ምርመራ ምክትል ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ም/ኮሚሽነር እርዚቅ ኢሳ እንዲሁም የዋና ጠቅላይ መምሪያና የክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አዛዦች ተገኝተዋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌ/ጀነራል አስራት ደኔሮ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አመራሮችን ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት እንደገለጹት የከተማዋን ሠላምና ደህንነት ለማረጋገጥ፣ የዜጎችን የፍትህና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት በተቋሙ ውስጥ የነበሩ የአሰራር ችግሮች መጀመሪያ መፈታት እንዳለባቸው በማመን በርካታ የሪፎርም ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል።

ለረጅም ጊዜያት የሠራዊቱ ጥያቄዎች የነበሩ የመልካም አስተዳደር፣ የማዕረግና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎች መፈታታቸው አባልና አመራሩን ለስራ ያለውን ተነሳሽነት በመጨመር ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉንም አንስተዋል።

የወንጀል ምርመራ ምክትል ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ም/ኮሚሽነር እርዚቅ ኢሳ በበኩላቸው እየተደረገ ባለው የሪፎርም ተግባር በተቋሙ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን አንስተው የተከናወኑ ተግባራትንም እንዲጎበኙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል መከላከል ም/ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ረ/ኮሚሽነር ፍቅሬ ዮዕሳ በበኩላቸው አዲስ አበባ ከተማ የፌዴራል መንግስቱና የልዩ ልዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን፤ የከተማዋን ሠላምና ደህንነት እያረጋገጠ ከሚገኘው የከተማዋ ብዙ ልምድ ለመውሰድ ስንመጣም ለተደረገልን ደማቅ አቀባበል ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

የክልሉ ፖሊስ አመራሮች በዋና ጠቅላይ መምሪያው በማዕከልና በክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ተግባራትን ጉብኝት የጀመሩ ሲሆን ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት ያህል የሚቆዩም ይሆናል፡፡
*
ዘገባ፡- ም/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
‎*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
በጀግንነት መጠበቅ ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል!
Protect with Courage, Serve with Compassion!
🇪🇹

የመውሊድ በዓልን ምክንያት በማድረግ መድፍ ይተኮሳል፡፡***አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ አበባ)፦ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ስፖርትና ኪነ ጥበባት ስራ...
24/08/2026

የመውሊድ በዓልን ምክንያት በማድረግ መድፍ ይተኮሳል፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ አበባ)፦ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ስፖርትና ኪነ ጥበባት ስራዎች ማዕከል ነገ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም የሚከበረውን የመውሊድ በዓል ምክንያት በማድረግ ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት ላይ ዘጠኝ ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ ገልጿል፡፡

በመሆኑም ህብረተሰቡ ተገቢው መረጃ እንዲኖረው ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
*
ዘገባ፦ ም/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
‎*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
በጀግንነት መጠበቅ ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል!
Protect with Courage, Serve with Compassion!
🇪🇹

በከተማችን በደረሰ የመንገድ ትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ ***አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ አደጋው የደረሰው ዛሬ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠ...
24/08/2026

በከተማችን በደረሰ የመንገድ ትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ
***
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ አደጋው የደረሰው ዛሬ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 1:50 ሠዓት በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ11 ልዩ ቦታው ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤ/ክርስቲያን አካባቢ ነው፡፡

የጉዞ አቅጣጫው ከኮዬ ፈቼ ወደ ጎሮ የሆነ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3-05997 ትግ የሆነ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በተጠቀሰው አካባቢ በመንገድ ስራ ላይ የነበረ ስካቫተር ማሽን መቆፈሪያው ወድቆበት በታክሲው ውስጥ ከነበሩ ትራንስፖርት ተጠቃሚዎች መካከል 5 ወንዶችና 1 ሴት ህይወት አልፏል፡፡

ከሟቾች በተጨማሪ በታክሲ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና ክትትል በማድረግ ላይ የሚገኙ መሆኑን የገለጸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም አስታውቋል፡፡
*
ዘገባ፦ ም/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
‎*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
በጀግንነት መጠበቅ ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል!
Protect with Courage, Serve with Compassion!
🇪🇹

ተቀጥሮ ከሚሰራበት ድርጅት የተቆራረጡ ፌሮ ብረቶችን በሁለት እግሮቹ አስሮ  ይዞ ሲወጣ  የተያዘው ግለሰብ ክስ ተመሰረተበት። ***አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦...
23/08/2026

ተቀጥሮ ከሚሰራበት ድርጅት የተቆራረጡ ፌሮ ብረቶችን በሁለት እግሮቹ አስሮ ይዞ ሲወጣ የተያዘው ግለሰብ ክስ ተመሰረተበት።
***
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ወንጀሉ የተፈጸመው ሐምሌ 24/2018 ዓ/ም ከቀኑ 11:00 ሠዓት በንፍስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ1 ለቡ መብራት አካባቢ ነው።

ተከሳሽ በሪሁን ሰፈፈ በተጠቀሰው አካባቢ ከሚገኝ አንድ ሪል ስቴት ውስጥ በቀን ሰራተኛነት ተቀጥሮ ሲሰራ የነበረ ሲሆን በስራ መውጫ ሰዓት የድርጅቱ ንብረት የሆነውን ቁርጥራጭ ፌሮ ብረት በሁለት እግሩ ከቁርጭምጭሚቱ በታች ፌስታል በመጠምጠም ከእግሮቹ ጋር አስሮ እና ሱሪውን ከላይ በመልበስ ይዞ ሊወጣ ሲል በድርጅቱ ጥበቃዎች ተይዞ ክስ እንደ ተመሰረተበት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የለቡ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

ህይወታቸውን ለመቀየር ቀን ከሌሊት በታማኝነት የሚሰሩ የቀን ሰራተኞች እንዳሉ ሁሉ አንዳንዶች ደግሞ ወንጀልን ለመፈጸም አቅደው እና አስበው የሚንቀሳቀሱ አይጠፉም እና አሰሪ ድርጅቶች ሰራተኞችን ተገቢ በሆነ መንገድ መቅጠር እና ቁጥጥር ማድረግ ይኖርባቸዋል ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።
*
ዘገባ፦ ዋና ሳጅን አባበል ከበደ
‎*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
በጀግንነት መጠበቅ ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል!
Protect with Courage, Serve with Compassion!
🇪🇹

እገታ በመፈጸም ወደ ባንክ አካውንታቸው ብር እንዲገባ ያደረጉ ሦስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።***አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 16 ቀን 2018ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተጠርጣሪዎቹ ሰለሞን ቢራራ...
22/08/2026

እገታ በመፈጸም ወደ ባንክ አካውንታቸው ብር እንዲገባ ያደረጉ ሦስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
***
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 16 ቀን 2018ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተጠርጣሪዎቹ ሰለሞን ቢራራ እሱባለው አግማሴ እና ሳንቾ ጌታቸው የተባሉ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ/ም በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ሌማት ሆቴል አካባቢ ከቀኑ 9፡00 ሠዓት ነው። ግለሰቦቹ በተጠቀሰው አካባቢ ከሚገኝ የግል ተበዳይ መኖሪያ ቤት በመሄድ የአለቃችንን ልጅ ባህር ማዶ ልከህ 5 መቶ ሺ ብር ተቀብለሃል በወንጀል ትፈለጋለህ በማለት ሀሰተኛ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት እና የመከላከያ መታወቂያ በማሳየት ጦር ኃይሎች አለቃችን ጋር እንወስድሀለን በማለት በተሽከርካሪ አግተውት ጉዞ ይጀምራሉ።

ተጠርጣሪዎቹ የተወሰነ ርቀት እንደተጓዙ የተሽከርካሪያቸውን መሪ አዙረው ወደ ቢሾፍቱ በማድረግ ከፈጣን መንገዱ እንደደረሱ ከአለቃችን ጋር ካደረስንህ ከባድ ቅጣት እና ተጠያቂነት የሚጠብቅህ በመሆኑ በሞባይል ባንኪንግ ብር አስገባልን እና እንልቀቅህ ይሉታል።

የግል ተበዳይ የሰራሁት ወንጀል የለም ወደ ህግ ውሰዱኝ በማለቱ ደብድበው 6 መቶ ሺ ብር በሞባይል ባንኪንግ በማስላክ ከተሽከርካሪ አውርደው ጥለውት መሰወራቸውን በየካ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የላም በረት አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ኢዮብ ተከተል ገልፀዋል፡፡

ፖሊስ ባደረገው ክትትልም ም/መቶ አለቃ ሰለሞን ቢራራ የተባለን ተከሳሽ የቢሾፍቱ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ባደረገው ትብብር በቁጥጥር ስር በማዋል በተከናወነው ምርመራ የማስፋት ተግባር ከመከላከያ ሰራዊት የከዳ ም/መቶ አለቃ እሱባለው አግማሴ የተባለን ደግሞ ግለሰብ ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በቁጥጥር አውሎታል።

ፖሊስ የምርመራ እና የክትትል ስራውን በመቀጠልም ገንዘብ አላቸው የሚባሉ ሰዎችን መረጃ በማጣራት ለወንጀል ፈጻሚዎች ጥቆማ የሚሰጥን ተጠርጣሪ ሳንቾ ጌታቸው የተባለን ግለሰብ ላምበረት መናኸሪያ አካባቢ በቁጥጥር ስር ሊያውለው መቻሉን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል፡፡

‎ከተወሰደው ገንዘብ 135 ሺ ብር እንዲሁም በዚሁ ብር የተገዛ 70,000 ሺ ብር የሚገመት ላፕቶፕ በኤግዚቢትነት በመያዝ ቀሪውን ብር ለማስመለስ እና ያልተያዘ አንድ ተጠርጣሪን ለመያዝ ምርመራው እና የክትትል ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን አዛዡ አመላክተዋል።

ተጠርጣሪዎቹ በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች አምስት ተመሳሳይ የእገታ ወንጀሎችን መፈጸማቸውን ለመርማሪ ፖሊስ ቃላቸውን የሰጡ ሲሆን በዚህም ጉዳይ ከሌሎች ክፍለ ከተሞች ጋር ጭምር በመነጋገር በጥልቀት እየተሰራበት መሆኑን አዛዡ ጠቁመዋል።

‎ህብረተሰቡ የጸጥታ አካል ነን ወንጀል ስለፈጸማችሁ በህግ ትፈለጋላችሁ፣ ወደ ህግ ቦታ ነው የምንወስዳችሁ በሚሉ ቃላት በመጠቀም አታለው ወንጀል የሚፈጽሙ አካላት መኖራቸውን አውቆ እንደዚህ አይነት አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በፍጥነት በአቅራቢያው ላለ የጸጥታ ተቋም ማሳወቅ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።
*
ዘገባ፡- ም/ሳጅን መልካሙ ዜና
‎*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
በጀግንነት መጠበቅ ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል!
Protect with Courage, Serve with Compassion!
🇪🇹

ሳትታገት ታግቻለሁ በማለት ከቤተሰቦቿ ገንዘብ የጠየቀችው ግለሰብ ከነአባሪዋ በቁጥጥር ስር ዋለች፡፡*** አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15 ቀን 2018ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመ...
21/08/2026

ሳትታገት ታግቻለሁ በማለት ከቤተሰቦቿ ገንዘብ የጠየቀችው ግለሰብ ከነአባሪዋ በቁጥጥር ስር ዋለች፡፡
***
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15 ቀን 2018ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሁለት ልዩ ቦታው አያት የጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ሀምሌ 25 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 4፡00 ሠዓት ሲሆን ነው።

ራሄል መለሰ የተባለች ግለሰብ ከቤት እንደወጣች ባለ መመለሷ ቤተሰብ ተጨንቆ አቅራቢያቸው ላለ የወረዳ ፖሊስ መምሪያ አመልክተዋል፡፡

ፖሊስም የደረሰውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ የክትትልና ኦፕሬሽን ቡድኑና የምርመራ ክፍሉ በመቀናጀት ግለሰቧ የት ሄደች ምን ሆና ይሆን? የሚለውን በማጣራት ላይ እንዳለ ለአባቷ ስልክ ተደውሎ ራሄል እነሱ ጋር እንደሆነችና እንዳገታት እሷን ለማስለቀቅ 850ሺ ብር እንዲልኩ ካልሆነ ልጃቸውን በህይወት እንደማያገኟ ይነገራቸዋል።

ፖሊስም ባደረገው የቀን ከሌሊት ጥረት የታገተችውን ግለሰብ በባህርዳር ከተማ ልዩ ቦታው ስማዳ እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ሆቴል ውስጥ እንዳለች በመታወቁ ግለሰቧን እና አጋች የተባለውን ሰለሞን ቁምላቸውን በቁጥጥር ስር በማዋል የምርመራ ስራውን መጀመሩን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።

በተያዙት ግለሰቦች ላይ በተደረገ ምርመራም የማስፋት ተግባር ተጠርጣሪዎቹ ከዚህ ቀደም የፍቅር ግንኙነት የነበራቸው ሲሆን ከሀገር ለመውጣት አስበው ከቤተሰቦቿ ገንዘብ ለመቀበል ይህንን እቅድ እንዳወጡም ፖሊስ አረጋግጧል፡፡

በተጠርጣሪዎቹ ላይ የምርመራ ስራውን መቀጠሉን የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ሲባል በመሰል የወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚገቡ ግለሰቦች እየታዩ በመምጣታቸው ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የአዲስ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል ።
*
ዘገባው:- ኢንስፔክተር እመቤት ሃብታሙ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
በጀግንነት መጠበቅ ፤ በሰብዓዊነት ማገልገል!
Protect with Courage, Serve with Compassion!
🇪🇹

ተቀጥራ ከምትስራበት መኖሪያ ቤት ከአምስት መቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት የወርቅ ጌጣጌጦችን እና ላፕቶፕ የሰረቀች ተከሳሽ በእስራት ተቀጣች። ***አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15 ቀን 2018ዓ/ም (...
21/08/2026

ተቀጥራ ከምትስራበት መኖሪያ ቤት ከአምስት መቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት የወርቅ ጌጣጌጦችን እና ላፕቶፕ የሰረቀች ተከሳሽ በእስራት ተቀጣች።
***
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 15 ቀን 2018ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተከሳሽ ቦንቱ ሀብታሙ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመችው በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ሸጎሌ መንደር ሰባት ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

ተከሳሽ ተቀጥራ ከምትስራበት መኖሪያ ቤት ውስጥ የአሰሪዋን አለመኖር እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ተቆልፎ የነበረን የመኝታ ቤቱ በር ቁልፍ ሰብራ በመግባት ቁም ሳጥን ውስጥ ተቀምጦ የነበረ አጠቃላይ ግምቱ 535ሺህ ብር የሚገመት የጆሮ ጌጥ 6፣ የአንገት ሐብል 2፣ የጣት ቀለበት 3፣ የጆሮ 1 ጌጣ ጌጦችን እና አንድ ላፕቶፕ ሰርቃ ተሰውራለች፡፡

የግል ተበዳይ ንብረታቸው መሰረቁን እንዳወቁ ጉዳዩን በጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ለፓስተር ፖሊስ መምሪያ አሳውቀዋል።

ፖሊስ የቀረበውን መረጃ መነሻ በማድረግ ባደረገው ብርቱ ክትትል ተከሳሽን ከተደበቀችበት ሰበታ አካባቢ ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር በማዋል እና ምርመራውን በማጠናቀቅ በአቃቤ ህግ በኩል ክስ እንዲመሰረትባት ማድረጉን ገልጿል።

የተከሳሽ ቦንቱ ሀብታሙን ጉዳይ ሲመለከት የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት መናገሻ ምድብ ወንጀል ችሎት ተከሳሿን ያስተምራል ሌሎችን ያስጠነቅቃል በማለት በ5 ዓመት ከ5 ወር እስራት እንድትቀጣ ወስኖባታል።

ግለሰቦች ወንጀል ፈፅመው ለጊዜው የተሰወሩ ቢመስላቸውም ከህግ ተጠያቂነት ማምለጥ እንደማይቻል የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ህብረተሰቡ ንብረቱን ሲያስቀምጥ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም መልዕክቱን አስተላልፏል።
*
ዘገባ፡- ም/ሳጅን ሳምሶን ሠለሞን
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/

በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ ሲጋራዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡***አዲስ አበባ፤ነሐሴ 15 ቀን 2018ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ተገቢውን የጉምሩክ ሂደት ሳያልፉ በህገ ወጥ መ...
21/08/2026

በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ ሲጋራዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 15 ቀን 2018ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ተገቢውን የጉምሩክ ሂደት ሳያልፉ በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ ሲጋራዎችና የሞባይል ስልክ ኬብሎች ከነ ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር የዋሉት በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው ዓለም ባንክ ‹‹ ብሩሩ ›› ወንዝ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው ፡፡

አብዱሐኪም ኑረዲን የተባለው ተጠርጣሪ ተከራይቶ በሚኖርበት ግቢ ውስጥ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ-3A-27624 አ/አ በሆነ ተሽከርካሪ አከማችቶት የነበረውን ከ66 ካርቶን በላይ የተለያዩ ሲጋራዎች፣ ከ149 ፓኬት በላይ የተለያየ መዋስል እንዲሁም 3 ማደበሪያ የሞባይል ኬብል እና የመሳሰሉት ዕቃዎችን በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የዓለም ባንክ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ባካሄደው የኦፕሬሽን ተግባር ከነ ተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን ፖሊስ ዋና መምሪያው አስታውቋል።

በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሃገር ውስጥ የሚገቡ እቃዎች በሃገር ምጣኔ ሀብትና በህጋዊ ነጋዴዎች ላይ የሚያስከትለው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ በአቋራጭ ለመበልጸግ በማሰብ በመሰል ህገ ወጥ ድርጊት ውስጥ የሚገቡ ግለሰቦችን ህብረተሰቡ መረጃ መስጠት እንዳለበት ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ትብብሩንም አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አቅርቧል።
*
ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዘላለም አበበ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና  መምሪያ በክፍለ ከተማው ካለው ተጨባጭ የፀጥታ ጉዳይ ጋር በተገናኘ በአካባቢው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አደረገ፡፡***አዲስ አበባ፤ነሐሴ 1...
20/08/2026

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ በክፍለ ከተማው ካለው ተጨባጭ የፀጥታ ጉዳይ ጋር በተገናኘ በአካባቢው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አደረገ፡፡
***
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 14 ቀን 2018ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ለፀጥታ ችግር በሆኑ ጉዳዮች እና በቀጣይ መከናወን ባለባቸው የህግ ማስከበር ተግባራት በተመለከተ በክፍለ ከተማው ካሉ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተደርጓል።

በውይይት መድረኩ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ም/ኮሚሽነር ሽመልስ ሽፈራው እና የዋና መምሪያው የወንጀል ምርመራ ምክትል ዋና መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ተክሌ አንጋሳ ለውይይቱ ተሳታፊዎች የ2018 በጀት አመት አፈፃፀም ሪፖርት በማቅረብ በቀጣይ በ2019 ዓ/ም በጀት ዓመት ትኩረት ተሰጥቶባቸው ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ዙሪያ እቅዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

ም/ኮሚሽነር ሽመልስ ሽፈራው የፀጥታ ስራ ለአንድ ወገን ብቻ የሚተው አለመሆኑን እና ህብረተሰቡ ለአካባቢው ፖሊስ መሆኑን አበክረው በመግለፅ ወንጀል ፈፃሚዎች በፈፀሙት ወንጀል በህግ ፊት ቀርበው እንዲጠየቁ ማድረግ የሚቻለው ወንጀል ሲፈፀም ያየ የምስክርነት ቃሉን በፍርድ ቤት ቀርቦ እውነታውን በመመስከር፣ ህጋዊነትን በተከተለ መልኩ ቤቱን በማከራየትና የተከራዩን እንቅስቃሴ በመከታተል መረጃ በመስጠት፣ አካባቢውን ከፖሊስ ጋር በጥምረት በመጠበቅ ፀጥታው ዘላቂ እንዲሆን ማድረግ እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡

የውይይት ተሳታፊዎችም ፖሊስ የሰራውን ስራ ይፋ አድርጎ ህዝብ እንዲገመግመው ማድረጉ ያልተለመደ ተግባር መሆኑን በመግለፅ በቀጣይ በወንጀል መከላከሉ ዘርፍና በፖሊስ አባላት ተጠቃሚነት ዙሪያ በሚያስፈልገው ሁሉ ከዚህ በፊት ሲሰራበት በነበረው ተነሳሽነት ትኩረት ሰጥተው እንደሚከውኑ ተናግረዋል።

በተጨማሪም በክፍለ ከተማው ያለውን የህዝብ አኗኗርና የቦታ አቀማመጥ ሁኔታን ታሳቢ ያደረገ እንዲሁም ከዚህ ቀደም ይፈፀሙ የነበሩ ቀላልና ከባድ ወንጀሎች ተጨባጭነት ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በ2019 ዓ/ም በጀት ዓመት ወንጀልን ለመጨቆን በሚያመች መልኩ ቅድመ ትግበራ እቅድ በማዘጋጀት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ በክፍለ ከተማው ካሉ 9ኙ ፖሊስ መምሪያዎች ጋር የስራ ስምምነት ሰነድ ፊርማ ስነ-ስርዓትም አድርገዋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የህብረተሰቡን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ከየትኛውም ጊዜ በተለየ የተጣለበትን ኃላፊነት በተገቢው ለመወጣት ትኩረት ሰጥቶ ህብረተሰቡን በማሳተፍ መዲናዋ ከወንጀል የፀዳች ሠላምና ደህንነቷ የተጠበቀባት እንድትሆን አበክሮ እየሰራ ይገኛል።

ህብረተሰቡም ለአካባቢው ዘብ በመቆም ሰላምና ፀጥታውን ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት መረጃን በመስጠት ሊሰራ እንደሚገባ መልዕክት ተላልፏል።
*
ዘገባ:- ዋና ሣጅን አዳነ ደስታ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቲክቶክ ፦https://www.tiktok.com/?
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/

Address

Arada Sub City , Addis Ababa Police
Addis Ababa
5647

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa Police posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ababa Police:

Shortcuts

Share