03/08/2026
ኢትዮጵያውያን ላሳዩት አስደናቂ ርብርብ እና ቁርጠኝነት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ምስጋናቸውን ገለፁ
******
የኢፌዴሪ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያውያን ላሳዩት የላቀ ርብርብ እና ቁርጠኝነት አድናቆትና ምስጋናቸውን ገልፀዋል።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የአንድ ጀምበር የ800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ሀገራዊ መርሐ ግብር አፈጻጸምን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በያዘችው እቅድ መሰረት በአንድ ቀን ብቻ 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ታሪካዊ ስኬት አስመዝግባለች ብለዋል።
በዚህም ሀገራችን ከራሷ አልፋ ለመላው አፍሪካ ታላቅ ምሳሌ መሆን መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብስረዋል፡፡
በዚህ ደማቅ ሀገራዊ የችግኝ ተከላ ንቅናቄ ላይ 26.2 ሚሊዮን ዜጎች በነቂስ ወጥተው እጅግ ከፍተኛ እና የነቃ ተሳትፎ ማድረጋቸውን በመግለፅ አመስግነዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን ላሳዩት ርብርብ እና ቁርጠኝነት አድናቆታቸውን የገለጹት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በዚሁ የአንድ ጀምበር ተሳትፎ 291.4 ሺህ ሄክታር መሬት የአረንጓዴ ዐሻራ መልበስ መቻሉንም በመግለጫቸው አስታውቀዋል፡፡