03/06/2026
አካዳሚው በሁሉም ስፖርት አይነቶች በሀገሪቱ ስፖርት ላይ ተፅዕኖ መፍጠር የቻሉ በርካታ ተተኪ ስፖርተኞችን እያፈራ ነው፦
አቶ አምበሳው እንየው የአካዳሚው ዋና ዳይሬክተር
ግንቦት 26/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማጣርያ የሁለተኛ ዙር የመልስ ጨዋታውን ከቡሩንዲ ጋር አድርጎ በድምር ውጤት 4ለ2 በማሸነፍ ከዛምቢያ ጋር ለመጨረሻ የደርሶመልስ ጨዋታ የሚያደርግ ሲሆን ከብሄራዊ ቡድኑ አባላት መካከል ከአካዳሚው ሁለቱ ካምፓሶች 10 ተጨዋችችና አንድ የአካል ብቃት አሰልጣኝ የሚገኙበት ሲሆን በድል ለተመለሱት የቡድኑ አባላት አካዳሚው ዛሬ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም በቅጥር ግቢው ደማቅ የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የዕውቅና ፕሮግራም አከናውኗል።
ብሄራዊ ቡድኑ በማጣሪያ አራት ጨዋታዎችን አድርጎ 12 ጎሎችን ያስቆጠረ ሲሆን ከተቆጠሩት ጎሎች ውስጥ 10 ጎሎችን የአካዳሚው ሰልጣኞች አስቆጥረዋል።
በመድረኩ የአካዳሚው ዋና ዳይሬክተር አቶ አምበሳው እንየው ባስተላለፉት መልዕክት አካዳሚው በሁሉም ስፖርት አይነቶች በሀገሪቱ ስፖርት ላይ ተፅዕኖ መፍጠር የቻሉ በርካታ ተተኪ ስፖርተኞችን እያፈራ መሆኑን በመግለፅ በዚህ ብሄራዊ ቡድን ከአካዳሚው ሁለቱም ካምፓሶች ተመርጣችው እየተጫወታችሁ ያላችሁ ሰልጣኞች ሀገርን በትልቅ ደረጃ ሊያስጠራ የሚችል ታሪክ ለመስራት በመመረጣችሁ በጣም እድለኞች ናችሁ። በቀጣይም የሚቀራችሁን የደርሶመል ጨዋታ በማሸነፍ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያን ለአለም ዋንጫ እንደምታሳልፉ አካዳሚው ሙሉ እምነት አለው ብለዋል አያይዘውም ሰልጣኞቹን ከመላው ሀገሪቱ መልምላችሁ እና አሰልጥናችሁ ለዚህ ያበቃችሁ አሰልጣኞችና መላው ሰራተኞች ፍሬያችሁን ስላያችሁ ልትኮሩ እና ልትመሰገኑ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ አሰልጣኞች እስካሁን በተገኘው ውጤት የተሰማቸውን ደስታ እና መልካም ምኞታቸውን የተናገሩ ሲሆን ሰልጣኞቹም በበኩላቸው ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል እና ዕውቅና ፕርግራም አካዳሚውን በማመስገን በቀጣይ ጠንክረን በመስራት ሀገርን እና አካዳሚውን የሚያኮራ ስራ እንሰራለን ብለዋል።
በመጨረሻም አካዳሚው በብሄራዊ ቡድኑ ለተሳተፉ 10 ሰልጣኞችና አንድ የአካል ብቃት አሰልጣኝ ለእያንዳዳቸው ግምታዊ ዋጋው 25000(ሃያ አምስት ሺ ብር) የሚያወጣ የስፖርት ትጥቅ ሽልማት አበርክቶላቸዋል።
በፕሮግራሙ የአካዳሚው ከፍተኛ አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣የማኔጅመንት አባላት፣ ሰልጣኞችና ሰራተኞች ታድመዋል።
ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”