Ethiopian Sports Academy

Ethiopian Sports Academy Empowering skilled young athletes with scientific training to achieve excellence and victory in national and international sports.

Operating under the Ministry of Culture & Sport-Ethiopia, we strive to nurture talent, and build a legacy of champions.

አካዳሚው  የአንደኛ ዙር ምልመላውን ገመገመነሀሴ 28/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ለ2019 ዓ.ም የስልጠና ዘመን ለአዲስ አበባ እና አሰላ (ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማ...
03/09/2026

አካዳሚው የአንደኛ ዙር ምልመላውን ገመገመ

ነሀሴ 28/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ለ2019 ዓ.ም የስልጠና ዘመን ለአዲስ አበባ እና አሰላ (ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል) ካምፓሶች በ10 ስፖርት አይነቶች የፀጥታ ችግር ከሌለባቸው ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በአጠቃላይ በሁለቱም ካምፓሶቹ 158 ወንድ እና 200 ሴት በድምሩ 358 ተተኪ ስፖርተኞችን አስገብቶ ለተከታታይ አራት አመታት ለማሰልጠን በመላው ሀገሪቱ 19 የጉዞ መስመሮችን እና በ65 የምልመላ ጣቢያዎችን በማዘጋጀት በሁለት ዙር ከነሀሴ 4-25 /2018 ዓ.ም ሲያካሂድ የቆየውን የመጀመሪያ ዙር የእጩ ተተኪ ስፖርተኞች ምልመላን ዛሬ ነሀሴ 28/2018 ዓ.ም በአካዳሚው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ገምግሟል።

በግምገማ መድረኩ በተዘጋጀዉ ፍኖተ ካርታ መሰረት ሁሉም የመልማይ ኮሚቴ የቡድን ሰብሳቢዎች (ፀኃፊዎች) እንደየስፖርት አይነቱ በተዘጋጀው የመመልመያ መስፈርት መሰረት በምልመላው የሰሩትን ስራ እና ያጋጠሟቸውን ችግሮች እንዲሁም ለቀጣይ ይጠቅማሉ ያሏቸውን ምክረ_ሀሳቦችን አጠር ያለ ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

ከሪፖርቱ እና በውይይቶች በተገኘው መረጃ በየምልመላ ጣቢያው ከፍተኛ የእጩ ሰልጣኞች መኖር፣ የቡድን አባላት ስራዎችን በቅንጅት መስራታቸው ፣ የእድሜ ተገቢነት ችግር ከፍ እና ዝቅ ብሎ መኖሩ፣ ደረጃውን የጠበቀ የማዘውተሪያ ስፍራ ችግር፣ በአንዳንድ ስፖርት አይነቶች የሴት እጩ ተመልማዮች ቁጥር አናሳ መሆኑ፣ የፓራለምፒክ ተመልማዮች አናሳ መሆን፣ የአየር ንብረት ችግር (ዝናብማ) መሆን፣ ለምልመላ የሚያገለግሉ የቁሳቁስ እጥረት መኖሩ፣ በአንዳንድ ክልሎች የአካዳሚው የምልመላ መረጃ ደርሷቸው ወደ ዞኖች እና ወረዳዎች አለማውረድ በዋናነት በጥንካሬ እና በተግዳሮት ተገልጿል።

በመጨረሻም የአካዳሚው የአስተዳደርና ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ፍቃዱ መኩሪያ እና የአካዳሚው አሰላ ካምፓስ ካምፓስ ዋና ዲን አቶ መሀመድ ጃርሶ የግምገማ መድረኩን ሲያጠቃልሉ ባስተላለፉት መልዕክት እና በሰጡት የስራ አቅጣጫ በምልመላው የተሳተፉትን አጠቃላይ አባላት ለስራው መሳካት ላበረከቱት አስተዋፅኦ ካመሰገኑ በኃላ የዘንድሮው ምልመላ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተደራሽነቱ ሁሉንም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮችን በማማከል ከወትሮው የተሻለ የምልመላ አደረጃጀት እና ስምሪት ተሰጥቶ ሰራው በአግባቡ መሰራቱን እና ለተነሱ ጥያቄዎች ቴክኒካዊ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።

አያይዘውም አካዳሚው በቀጣይ በጊዚያዊነት በያዘው ፕሮግራም ከመስከረም 05-12/2019 ዓ.ም ለሁለተኛ ዙር (የማጠቃለያ) ምልመላ የሚጠሩ እጩ ሰልጣኞችን በቴክኒክ ኮሚቴው ተለይተው በአስቸኳይ ጥሪ እንዲደረግላቸው አቅጣጫ በማስቀመጥ የግምገማ መድረኩ ተጠናቋል።

ማሳሰቢያ
አካዳሚው ለሁለተኛ (ለማጠቃለያ) ምልመላ የምትጠሩ እጩ ስፖርተኞችን በተንቀሳቃሽ ስልካችሁ የሚያሳውቅ ስለሆነ ስልካችሁን ክፍት እንድታደርጉ እያሳሰበ በተጨማሪም ለክልል እና ከተማ አስተዳደሮች ስፖርት ቢሮዎች አካዳሚው በህጋዊ ደብዳቤ የምናሳውቅ መሆኑን እየገለፅን በተጨማሪም በማህበራዊ ድህረ_ገፃችንም ከምልመላው ጋር የተያያዙ ተከታታይነት ያላቸው መረጃዎችን የምንሰጥ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።

ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

አካዳሚው ከስራ አስፈፃሚዎች ጋር የ2019 በጀት አመት እቅድን የስራ ውል ስምምነት በማድረግ ስራን ቆጥሮ አስረከበነሀሴ 26/2018 ዓ.ም የአካዳሚው ከፍተኛ አመራር ለሁሉም ስራ አስፈፃሚዎች...
01/09/2026

አካዳሚው ከስራ አስፈፃሚዎች ጋር የ2019 በጀት አመት እቅድን የስራ ውል ስምምነት በማድረግ ስራን ቆጥሮ አስረከበ

ነሀሴ 26/2018 ዓ.ም

የአካዳሚው ከፍተኛ አመራር ለሁሉም ስራ አስፈፃሚዎች የ2019 በጀት አመት እቅድን የስራ ውል ስምምነት በመፈራረም ስራ ቆጥረው አስረከቡ።

በመድረኩ የበጀት አመቱን የስራ ውሉን ፈርመው ቆጥረው ያስረከቡት የአካዳሚው የአስተዳደር እና ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ፍቃዱ መኩሪያ ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት ለአካዳሚው ተልዕኮ ሰጥቶ አቋቁሟል። ለዚህም አካዳሚው ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠር እንደየተልዕኮው ባህሪ የስራ ክፍሎች ተፈጥረው የአመራር እና የሰራተኛ ምደባ በማድረግ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።በዚሁ መሰረት ተልዕኮ ለመወጣት እና ግብን ለማሳካት ስራዎችን ለመደገፍ እና ለመከታተል የስራ ውል ስምምነቱ አስፈላጊነቱ እሙን ነው ብለዋል።

አመራሩ አያይዘውም የስራ ውሉን መነሻ በማድረግ ለስራ አስፈፃሚዎች አጥብቀው ባስተላለፉት መልዕክት ከሁሉም የስራ ክፍሎች ተውጣጥቶ ተቋማዊ እቅድ ታቅዷል።ግብን ለማሳካት የከፍተኛ አመራርና የስራ አስፈፃሚዎች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ለእናንተ የተሰጠውን የስራ ውል ለባለሙያዎች በማውረድ የአካዳሚውን ውጤታማነት ለማስቀጠል በኃላፊነት እና ተጠያቂነትን በሚያመጣ መልኩ ስራዎችን በፍጥነት፣ በጥራት እና በጊዜ በህግ አግባብ በቅንጅት እና በርብርብ ቀልጣፍ አገልግሎቶችን ተደራሽ ማድረግ የግድ መሆኑን በማሳሰብ ለዚህም አካዳሚው አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

ስራ አስፈፃሚዎችም በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት እቅድ ላይ ከተግባባን ስራዎችን በቅንጅት እንሰራለን ካሉ በኃላ ነገር ግን የአመራር ተዋረድ መጠበቅ እንዳለበት፣ የአሰራር ስርአት ሊጠበቅ እንደሚገባ ፣ በአንዳንድ ሰራተኞች ላይ የአመለካከት ለውጥ ማምጣጥ እንደሚያስፈልግ እና እንደአስፈላጊነቱም ርምጃ በመውሰድ አሰራር እና ህግ ተከብሮ ስራዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት ገልፀዋል።

አካዳሚው የ2019 በጀት አመት እቅድን ከአጠቃላይ ሰራተኞቹ እና ከማኔጅመን አባላቱ ጋር መገምገሙ ይታወሳል።

ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

31/08/2026
ሁለተኛ ቀኑን የያዘው     #የእግርኳስ የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ እንደቀጠለ ሲሆን ነገ ፍፃሜውን ያገኛልነሀሴ 24/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በሁለቱም ፆታ እየተካሄደ የሚገኘው የእግርኳስ ምል...
30/08/2026

ሁለተኛ ቀኑን የያዘው #የእግርኳስ የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ እንደቀጠለ ሲሆን ነገ ፍፃሜውን ያገኛል

ነሀሴ 24/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

በሁለቱም ፆታ እየተካሄደ የሚገኘው የእግርኳስ ምልመላ በዛሬው ውሎው አሰልጣኞች የእጩ ሰልጣኞችን የቴክኒክ፣ የታክቲክ እና የብቃት አመላካች ልኬቶችን ሲያደርጉ የዋሉ ሲሆን ነገ ፍፃሜውን ያደርጋል።

ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

30/08/2026
በርካታ ታዳጊዎች የተገኙበት    #የእግርኳስ የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ በሁለቱም ፆታ እየተካሄደ ሲሆን በዛሬው ውሎው አሰልጣኞች የእጩ ሰልጣኞችን የቴክኒክ፣ የታክቲክ እና የብቃት አመላካች ምል...
29/08/2026

በርካታ ታዳጊዎች የተገኙበት #የእግርኳስ የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ በሁለቱም ፆታ እየተካሄደ ሲሆን በዛሬው ውሎው አሰልጣኞች የእጩ ሰልጣኞችን የቴክኒክ፣ የታክቲክ እና የብቃት አመላካች ምልከታዎችን ሲያደርጉ የዋሉ ሲሆን ነገም ይቀጥላል።

ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው  #የጎንደር እና አካባቢው ምልመላ በስኬት ተጠናቋልነሀሴ 23/2018 ዓ.ም የአካዳሚው   መልማዮች ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት   ዞኖች ከተውጣጡ ታ...
29/08/2026

ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው #የጎንደር እና አካባቢው ምልመላ በስኬት ተጠናቋል

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ም

የአካዳሚው መልማዮች ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ዞኖች ከተውጣጡ ታዳጊዎች መካከል #ጎንደር ከተማ ላይ #በእግርኳስ፣ #በአትሌቲክስ፣ #በቅርጫትኳስ እና #በቮሊቦል ስፖርት አይነቶች በሁለቱም ፆታ ሲያደርጉት የነበረውን የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ በስኬት አጠናቀዋል።

መልማይ ቡድኑ የተሳካ ምልመላ እንዲያደርግ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ በየደረጃው ያላችሁ የስፖርት አመራሮች እና ባለሙያዎች አካዳሚው ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል።

ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

  እና አካባቢው የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ በስኬት ተጠናቋልነሀሴ 23/2018 ዓ.ም የአካዳሚው   መልማዮች ለተከታታይ ሁለት ቀናት   ዞኖች ከተውጣጡ ታዳጊዎች መካከል    ከተማ ላይ  #በእግ...
29/08/2026

እና አካባቢው የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ በስኬት ተጠናቋል

ነሀሴ 23/2018 ዓ.ም

የአካዳሚው መልማዮች ለተከታታይ ሁለት ቀናት ዞኖች ከተውጣጡ ታዳጊዎች መካከል ከተማ ላይ #በእግርኳስ፣ #በብስክሌት እና #በአትሌቲክስ ስፖርት አይነቶች በሁለቱም ፆታ ሲያደርጉት የነበረውን የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ በስኬት አጠናቀዋል።

መልማይ ቡድኑ የተሳካ ምልመላ እንዲያደርግ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ አመራሮችና ስፖርት ባለሙያዎች አካዳሚው ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል።

ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

29/08/2026

ለመመልመል የተገኙ ታዳጊዎች፤

Address

Bole
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Sports Academy posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Sports Academy:

Shortcuts

Share