02/09/2026
የቀበና ኮሪደር ልማት ለስፖርተኞች እና ለወጣቶች አዲስ የሰብአት ስፍራ መሆኑ የካራቴ የስፖርት ቤተሰቦች ገለጹ
ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ/ም ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ
በአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር የተገነባው የቀበና ወንዝ ዳርቻ ኮሪደር ልማት በስፖርት ቤተሰቦች፣ በአሰልጣኞች እና በወጣቶች ዘንድ ተመራጭ የሰብአት ስፍራ ነው ሲ,ሉ የካራቴ ስፖርት ቤተሰቦች ገለጹ
ይህ የተገለጸው የአዲስ አበባ ከተማ ካራቴ ፌዴሬሽን የተውጣጡ የስፖርት ቤተሰቦች፣ አሰልጣኞች እና ታዳጊ ስፖርተኞች በቀበና ወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በተከናወነው ልዩ የስፖርታዊ እግር ጉዞ ፕሮግራም ላይ ነው።
ፕሮጀክቱ ያካተታቸው ማራኪ የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ፣ ለስነ-ልቦና እረፍትና ለወጣቶች ሁለንተናዊ በጎ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኝ የካራቴ ስፖርተኞች ገልጸዋል፡፡
"የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ ውበት መስጠቱ ብቻ ሳይሆን፣ ስፖርተኞችና ታዳጊዎች ከአዳራሽ ውጭ ንጹህ አየር እየተነፈሱ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችንና የተለያዩ አርቶችን ለማሳየት እና ለማቅረብ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አክለዋል፡፡
ቀደም ሲል ተከልለውና ለአካባቢ ብክለት ተጋልጠው የነበሩት የወንዝ ዳርቻዎች በአሁኑ ወቅት ወደ ዘመናዊ የስፖርት፣ የብስክሌትና የእግር ጉዞ መስመሮች መለወጣቸው ለአካባቢው ነዋሪዎች በተለይም ለታዳጊዎችና ለወጣቶች ምቹ የሰብዕት ቦታ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል።