Arada subcity worada 8 communication

Arada subcity worada 8 communication ኢትዮጵያዊነት we serve the government of Ethiopia PR for the purpose of Addise Abeba press secretary

 "የማንሰራራት ቀን "ን አስመልክቶ የወርቃማ ሰኞ የፓናል ውይይት ተካሄደበአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር የጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን አስመልክቶ የወርቃማ ሰኞ የፓናል ውይይት ተካሄ...
07/09/2026



"የማንሰራራት ቀን "ን አስመልክቶ የወርቃማ ሰኞ የፓናል ውይይት ተካሄደ

በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር የጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን አስመልክቶ የወርቃማ ሰኞ የፓናል ውይይት ተካሄደ።

የውይይቱ ዋና ዓላማ የማንሰራራት ቀን የሚያስተላልፈውን መልዕክት በማጉላት፣ በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ለውጦችንና ስኬቶችን በመገምገም ቀጣይ ስራዎችን በተቀናጀ መልኩ ለማከናወን አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው።

በፓናል ውይይቱ የማንሰራራት ትርጉምና ጠቀሜታ፣ ከተሞችን በተሻለ ደረጃ ለመገንባት የሚደረጉ ጥረቶች፣ የመንግስት ሰራተኛው የጋራ ኃላፊነት እንዲሁም የተጀመሩ መልካም ተግባራትን ወደ ዘላቂ ልማት ለማሸጋገር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ሀሳብ ተለዋውጧል።

ተሳታፊዎችም ያለፈውን ልምድ በመገምገም የተሻለ ነገን ለመገንባት ከግለሰብ እስከ ተቋምና ማህበረሰብ ድረስ የሚጠበቀውን ሚና በተግባር መወጣት እንደሚገባ ተገልጿል።

በወረዳ ደረጃ የተጀመሩ መልካም ስራዎችን በማስቀጠል የነዋሪዎችን ኑሮና የአካባቢውን ገጽታ ለማሻሻል በትብብር መስራት እንደሚገባም ተጠቁሟል።

በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ  ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ነው።አራዳ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ምጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን ምክንያት ...
07/09/2026

በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ነው።

አራዳ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም

ጳጉሜ 2 የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ የአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ያሉትን የኤሌክትሪክ መኪኖች በመጠቀም ለነዋሪው ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን የአስተዳደሩ ሀላፊዎች በቦታው በመገኘት ለትራንስፖርት ተጠቃሚዎች የእንኳን አደረሳችሁ ፖስት ካርድ ሰጥተዋል።

ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በሚሰጥበት ቦታ የአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ምክትል ስራ አስፈጻሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብዲ ሙሉነህ፣ የአራዳ ክ/ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ደሳለኝ አገኘሁ፣ የአራዳ ክ/ከተማ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ደቻሳ ጆቴ፣ የክ/ከተማው የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ እንድሪስ አስናቀ እንዲሁም የክ/ከተማና የወረዳ አመራሮችና የስራ ሀላፊዎች በትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ ቦታዎች ላይ በመገኘት የእንኳን አደረሳችሁ ፖስት ካርድ የመስጠትና የማስተባበር ስራ በመስራት ላይ ይገኛሉ።

የከተማ አውቶቢስን ጨምሮ ሁሉም የመንግስት የህዝብ ትራንስፖርት መስጫ ተሽከርካሪዎች በዛሬው እለት ለነዋሪው ማህበረሰብ ነጻ የትራንስፖርት እየሰጡ መሆኑ ታውቋል።

 በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር የፅዳት  ዘመቻ ተካሄደጳጉሜ 2 “የማንሰራራት ቀን”ን በማስመልከት በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።በዘመቻው የአካባቢ...
07/09/2026



በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ

ጳጉሜ 2 “የማንሰራራት ቀን”ን በማስመልከት በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።

በዘመቻው የአካባቢ ፅዳትን ለማስጠበቅና ንፁህና ምቹ የከተማ አካባቢን ለመፍጠር የሚያግዙ የፅዳት ሥራዎች በጋራ ተከናውነዋል።

በተጨማሪም በፅዳት አጠባበቅ ሞዴል ለሆኑ ብሎኮች የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዶ፣ በአካባቢ ፅዳትና ውበት ላይ የላቀ ተሳትፎ ላደረጉ አካላት እውቅና ተሰጥቷል።

የማንሰራራት ቀን በመተባበር፣ በኃላፊነትና በተግባር የተሻለች ከተማን ለመገንባት የሚያነሳሳ ቀን ነው።

የማንሰራራት ቀንን ምክኒያት በማድረግ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ነው።የአዲስ አመት መቀበያ  የሆነችው ጳጉሜን ቀናት በተለያየ ስያሜዎች እየተከበሩ ሲሆን የዛሬው ጳጉሜን 2 ደግሞ...
07/09/2026

የማንሰራራት ቀንን ምክኒያት በማድረግ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት እየተሰጠ ነው።

የአዲስ አመት መቀበያ የሆነችው ጳጉሜን ቀናት በተለያየ ስያሜዎች እየተከበሩ ሲሆን የዛሬው ጳጉሜን 2 ደግሞ በማንሰራራት ተሰይሟል።

የአዲስ አበባ የማንሰራራት ማሳያ የሆነው የትራንስፖርት ዘርፍም ለከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ቀኑን እያከበረ ነው።

ለግማሽ ቀን በሚቆየው ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የከተማ አውቶብስና የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ለደንበኞቻቸው መልካም የአዲስ አመት በመመኘት ጭምር እየተሳተፉ ነው።

በቦሌ ሚሊኒየም አካባቢ የተሰጠውን ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በነጻ ትራንስፖርቱ 1.1 ሚሊየን የመዲናዋ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል።

የአዲስ አበባ የማንሰራራት ማሳያ ከሆኑ ልማቶች መካከልም የትራንስፖርት ዘርፉ ዋነኛው ነው ያሉት አቶ ዳኛቸው የአዲስ አበባን ዝማኔ የሚመጥኑ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማስፋፋት ዘርፉን ማንሰራራት ተችሏል ብለዋል።

ምቹ መሰረተ ልማቶችን ማስፋፋትና የዘመነ አገልግሎትም በዘርፉ መሻሻል ማሳየቱ ነው ምክትል ቢሮ ኃላፊው የገለጹት።

"የማንሠራራት ቀን ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ! ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስ...
07/09/2026

"የማንሠራራት ቀን

ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!

ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።"

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


"የእመርታ ቀን " #ከጥገኝነት አዙሪት ፣ ወደ አምራችነት ልዕልና! #አዲስ አበባየሀገራዊ እመርታችን ህያው ማሳያ! #በትጋት ሰርተን ፣በላባችን አምርተን፣ ከተረጂነት ቀንበር ነፃ ወጥተናል!
06/09/2026

"የእመርታ ቀን "
#ከጥገኝነት አዙሪት ፣ ወደ አምራችነት ልዕልና!
#አዲስ አበባየሀገራዊ እመርታችን ህያው ማሳያ!
#በትጋት ሰርተን ፣በላባችን አምርተን፣ ከተረጂነት ቀንበር ነፃ ወጥተናል!

የጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን” በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በድምቀት ተካሄደየጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን” በአራዳ ክፍለ ከተማ በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ተካሄደ።በዕለቱ የከተማን ጽዳትና ...
06/09/2026

የጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን”

በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በድምቀት ተካሄደ

የጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን” በአራዳ ክፍለ ከተማ በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ተካሄደ።

በዕለቱ የከተማን ጽዳትና ውበት ለማስጠበቅ የጽዳት ዘመቻ ተካሂዷል። በዘመቻው የአካባቢ ንጽህናን በማስጠበቅ ንጹህና ምቹ የከተማ አካባቢ ለመፍጠር የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት ተከናውነዋል።

በተጨማሪም የሌማት ትሩፋት ስራዎች የተከናወኑበትን ሁኔታ ለመመልከት ጉብኝት ተካሂዷል። ጉብኝቱም የተለያዩ የምርትና የሌማት ትሩፋት ስራዎችን በመመልከት ተሞክሮ ለመቅሰም ያስቻለ ነበር።

የባዛር ጉብኝትም በዕለቱ ከተካሄዱት መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በባዛሩ የቀረቡ ምርቶችን በመመልከትና የአምራቾችን ተግባራት በመጎብኘት የምርት አቅምን ማሳደግና የአካባቢ ምርቶችን ማስተዋወቅ ያለውን ሚና ለማጠናከር ተሰርቷል።

በአጠቃላይ የጳጉሜ 1 “የእመርታ ቀን” መርሃ ግብር አራዳ ክፍለ ከተማን ንጹህ፣ ምርታማና በዘላቂ ልማት የተሻለች ከተማ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶችን በማጠናከር በድምቀት ተካሄደ።

በአራዳ ክፍለ ከተማ በኮንስትራክሽን ዘርፍ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸው ተገለፀ።አራዳ ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም በአራዳ ክፍለ ከተማ በኮንስትራክሽን ዘርፍ በርካታ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን...
06/09/2026

በአራዳ ክፍለ ከተማ በኮንስትራክሽን ዘርፍ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸው ተገለፀ።

አራዳ ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም

በአራዳ ክፍለ ከተማ በኮንስትራክሽን ዘርፍ በርካታ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ጽ/ቤት ገለፀ።

በበጀት ዓመቱ በዘርፉ በተከናወኑ ስራዎች የከተማውን ገፅታ በዘመናዊ መልኩ መቀየር የተቻለ ሲሆን የ7/24 የስራ ባህልን በማዳበር የግንባታ ፈጣን አፈፃፀም ማምጣት ተችሏል።

በዘርፉ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩ፣ የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት መረጋገጡ፣ የመንግስትና የግል ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ በዘመናዊ አሰራር መታገዙ የዘርፉ እመርታዎች ናቸው።

የሀገር ውስጥ የስራ ተቋራጮች፣ አማካሪዎች፣ ባለሙያዎች፣ ጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅቶችን አቅም በዘላቂነት ለመገንባት የተሰሩ ስራዎች ተጠናክረው የቀጠሉ ሲሆን ባለሙያዎች ወጭ ቆጣቢና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በግንባታ ሂደቶች ውስጥ የመጠቀም አቅም በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።

እነዚህ አመርቂ ውጤቶች ከአራዳ ክፍለ ከተማ ታሪካዊ ቁመና እና አሁን አዲስ አበባ ከምታከናውነው አጠቃላይ የኮሪደር ልማት ማዕቀፍ ጋር ተጣጥመው መተግበራቸው ለዘርፉ የላቀ ስኬት መሠረት ሆኗል።

የኮሪደር ልማቱ አካባቢዎችን ለኑሮ ምቹ፣ ንጹህና ማራኪ በማድረግ የከተማዋን ነዋሪዎችና የቱሪስቶች እንቅስቃሴ ምቹ እንዲሆን አድርጎታል።
የክፍለ ከተማው አስተዳደር የኮንስትራክሽንና የኮሪደር ልማት ስራዎችን በማቀናጀት አራዳን የዕድገትና የብልጽግና ምዕራፍ ማሳያ ለማድረግ በቀጣይም የተጠናከሩ ስራዎች እንደሚሰሩ ጽ/ቤታ ገልጿል።

06/09/2026
የ"ጎቤ" እና "ሺኖዬ" ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነውከክረምት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገርን የሚያበስረው “የጎቤ” እና “ሺኖዬ”ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡...
06/09/2026

የ"ጎቤ" እና "ሺኖዬ" ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው

ከክረምት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገርን የሚያበስረው “የጎቤ” እና “ሺኖዬ”ፌስቲቫል በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡፡

በኦሮሞ ባህል ዘንድ የክረምቱን መውጣትና የጸደይ መዳረሻን ለማብሰር ከሚከናወኑ ባህላዊ ሥርዓቶች መካከል “የጎቤ” እና “ሺኖዬ” ጨዋታ ተጠቃሽ ነው።
AMN

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arada subcity worada 8 communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Arada subcity worada 8 communication:

Shortcuts

Share