04/09/2026
Advancing Issuers’ Understanding of Post-Registration Obligations
*************************************************************
The Ethiopian Capital Market Authority (ECMA) conducted a training session for issuers on Post-Registration Obligations, focusing on the key regulatory requirements that apply after securities registration.
The session covered ongoing information disclosure, periodic reporting, key post-registration regulatory areas, and other important compliance requirements.
The training aims to strengthen issuers’ awareness and understanding of the Public Offering and Trading of Securities Directive No. 1030/2024, while promoting greater transparency, accountability, and compliance within Ethiopia’s growing capital market.
Building knowledge and strengthening compliance are essential to developing a transparent, credible, and well-functioning capital market.
ሰነደ ሙዓለ ንዋይ አውጭዎች ከምዝገባ በኋላ ስለሚጠበቅባቸው ግዴታዎች የሚያስገነዝብ ስልጠና ተሰጠ
**********************************************************************
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ሰነደ ሙዓለ ንዋይ አውጭዎች ከምዝገባ በኋላ ስለሚጠበቅባቸው ግዴታዎች ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው ከምዝገባ በኋላ ስለሚጠበቁ መረጃን ይፋ የማድረግ የህግ ግዴታዎች ላይ በሚመለከት የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሲሆን ሰነደ ሙዓለ ንዋይን ለህዝብ የማቅረብ እና የግብይት መመሪያ ቁጥር 1030/2017 እና ከምዝገባ በኋላ ስለሚጠበቁ ጉዳዮች በተመለከተ ትኩረት አድርጓል፡
ሰነደ ሙዓለ ንዋይን ለህዝብ የማቅረብ እና የግብይት መመሪያ ቁጥር 1030/2017 አንቀጽ 135 መሠረት ለሕዝብ ሽያጭ የቀረቡ ወይም በሕዝብ የተያዙ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች አውጪ በቋሚነት መረጃን ለህዝብ ይፋ የማድረግ የህግ ግዴታ ያለበት ሲሆን እነዚህን የህግ ግዴታዎች በወቅቱና በተገቢው መልኩ መወጣት እንደሚያስፈልግም በስልጠናው ተገልጿል፡፡
ስልጠናው የሰነደ ሙዓለ ንዋይ አውጭዎች ከምዝገባ በኋላ የሚጠበቅባቸውን ሀላፊነት በተመለከተ ያላቸውን ግንዛቤ ማጠናከር ያለመ ሲሆን በኢትዮጵያ እያደገ ባለው የካፒታል ገበያ ውስጥ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ለማስፈን ያስችላል።