Ethiopian Enterprise Development

Ethiopian Enterprise Development ራዕያችን ለኢንዱስትሪው ልማት አስተማማኝና ሰፊ መሰረት ያለ?

አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ========/////==========EED ግንቦት 27 ቀን 20178 ዓ.ምአንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ ‹‹እናት ዱቄት›› በሚል ስያሜ የተለያየ መጠን ያላቸውን ...
04/06/2026

አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ
========/////==========
EED ግንቦት 27 ቀን 20178 ዓ.ም

አንዋር ነስሮ የዱቄት ፋብሪካ ‹‹እናት ዱቄት›› በሚል ስያሜ የተለያየ መጠን ያላቸውን የስንዴ ዱቄት እያመረተ የሚገኝና በሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀቤላ ቲላ ወረዳ የሚገኝ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው።

ኢንተርፕራይዙ በ4 ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል በ2018 ዓ.ም በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ በተፈጠረው ንቅናቄ ስራ ጀምሯል።

የእናት ዱቄት መስራች አንዋር ነስሮ እንደሚናገረው በአካባቢው ያለውን ክፍተትና የገበያ ፍላጎት መሰረት በማድረግ ወደስራ መግባታቸውንና የተለያየ መጠን ያላቸውን የስንዴ ዱቄት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡

በአሁኑ ሰአት አጠቃላይ ሀብቱን ወደ 40 ሚልየን ብር ማሳደጉን የሚገልጸው አንዋር ለ9 ቋሚና 20 ለሚሆኑ ሰራተኞች ጊዚያዊ የስራ እድል መፍጠሩንም ይናገራል፡፡

በአካባቢው ለሚገኙ ከተሞች ምርታቸውን በስፋት እያቀረቡና በተጠቃሚዎች ዘንድ ተቀባይነታቸውንና የማምረት አቅማቸውን ለማሳደግ እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግሯል፡፡

በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት አማካኝነት ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ የወሰዷቸው ማሽኖቹ የማምረት አቅም በቀን 24 ቶን መሆኑን የሚገልጸው አንዋር የስራ ማስኬጃ እጥረትና የኤሌክትሪክ ሐይል መቆራረጥ በሚፈልጉት ደረጃ እንዳይሰሩ እንቅፋት እንደሆነባቸውና የአቅማቸውን 20 በመቶ ብቻ እየተጠቀሙ እንደሚገኝ ይገልጻል፡፡

#አድራሻ፡

ሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀቤላ ቲላ ወረዳ

☎️ስልክ፡ 0918999843





ይጎብኙ!

‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ፡- ከወዳደቁ ነገሮች ጭስ አልባ ከሰል የሚያመርት ኢንተርፕራይዝ========/////==========EED ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ምስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክ...
03/06/2026

ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ፡- ከወዳደቁ ነገሮች ጭስ አልባ ከሰል የሚያመርት ኢንተርፕራይዝ
========/////==========
EED ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ ከወዳደቁ ግብዓቶች ጭስና ሽታ አልባ ኮኮ የተሰኘ ከሰል የሚያመርት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ የሚገኝ ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ነው።

ኢንተርፕራይዙ በ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር መነሻ ካፒታል በ2018 ዓ.ም ህዳር ወር በገጠር ኢንዱስትሪያላይዜሽን ኢንሼቲቭ በተፈጠረው ንቅናቄ በ2 ጓደኛሞች የተመሠረተ አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ነው።

ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ ምክትል ስራ አስኪያጅና መስራች ወጣት አብዱልካፍ ሽኩር እንደሚናገረው ሽታና ጭስ አልባ የሆነውን ኮኮ ከሰል ለማምረት እንደ ጫት ገረባ፣ ቡና ገለባ፣ ሰጋቱራና ደቃቅ ከሰል ከመሳሰሉ በአካባቢው የሚገኙና የሚጣሉ ግብአቶችን ይጠቀማል።

ለከሰል ምርት የሚቆረጡ ዛፎችን መጠን በመቀነስ የአየር ንብረትን በጠበቀ ሁኔታ ከሰል እያመረቱ መሆኑን የሚገልጸው ም/ስራ አስኪያጁ የፈርነስ/ካራቦናይዜሽን ማሽንን በመጠቀም ካርቦን ሞኖ ኦክሳይድ የሌለው ከሰል እያመረቱና የከሰል ጭስን 95 በመቶ እየቀነሱ በመሆናቸው የህብረተሰቡን ጤናን እየጠበቁ መሆኑን ይስረዳል፡፡

ስራው ሲጀመር ዝቅ ብሎ መስራትና መቆሸሽ ይኖረዋል የሚለው አብዱልካፍ አሁን ወደከፍታ እየተሸጋገሩና በሶስት ፈረቃ እያሰሩ በመሆናቸው በአሁኑ ሰአት 2 ነጥብ 5 ሚልየን ብር ጠቅላላ ሀብት በማንቀሳቀሰ ለ25 ቋሚና 12 ጊዚያዊ/ኮሚሽን ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠራቸውን ይናገራል፡፡

ከኬራቲ ጀምሮ እስከ አዲስ አበባ ገበያ ምርቶቻቸውን በስፋት እያቀረቡ መሆኑን የሚገልጸው አብዱልካፍ ቆሻሻ ሀብት መሆኑን በመረዳት ወደሀብት እየቀየሩና ማህበረሰቡ ይህንን እንዲረዳም እየሰሩ መሆኑን ይናገራል፡፡

ምርቶቻቸው ጥራት ያለው፣ ጭስና ሽታ አልባ እንዲሁም ለረዥም ጊዜ የሚቆይ በመሆኑ ተመራጭ መሆናውንና ትላልቅ ሱፐር ማርኬቶች፣ ሆቴሎች በተለይም ኮንዶሚኒየምና አፓርታማ አካባቢ የሚገኙ የማህረሰብ ክፍሎች ምርቶችቸውን በስፋት እየተጠቀሙ መሆኑን ይገልጻል፡፡

ስሪ ኤፍ (3F) ማኑፋክቸሪንግ ከኮኮ ከሰል በተጨማሪ የተፈጥሮ ሽታ ያላቸውን አበባዎች በመጠቀም ብሑሮችና እጣኖችን እንዲሁም ደረቅ ሳሙናዎችን በማምረት ለተጠቃሚዎች በማቅረብም ላይ ይገኛል፡፡

ያለባቸውን የአቅም ውስንነት በመቅረፍም በስፋት ወደ ገበያ የመግባት እቅድ እንዳላቸው የገለጸው አብዱልካፍ ተጨማሪ ማሽኖች የሚያገኙባቸው ሆኔታዎች እንዲመቻችላቸውና ያለባቸው የኤሌክትሪክ ሐይል አቅርቦት ችግር እንዲፈታላቸውም ጥሪ አቅርቧል፡፡

#አድራሻ፡
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልባራግ ወረዳ ኬራቲ ከተማ

☎️ስልክ፡ 09 11 57 31 71/ 09 75 73 33 33





ይጎብኙ!
‌‎https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

በስደት ያጠራቀሙትን እውቀትና ገንዘብ ለሀገር ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፡ አቶ ስምኦን እና የ“ጭቶ ቡና” የስኬት ጉዞEED ግንቦት 25/2018 ዓ.ምቡና ለኢትዮጵያዊያን መጠጥ ብቻ አይደለም፤ ባህል፣...
02/06/2026

በስደት ያጠራቀሙትን እውቀትና ገንዘብ ለሀገር ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፡ አቶ ስምኦን እና የ“ጭቶ ቡና” የስኬት ጉዞ

EED ግንቦት 25/2018 ዓ.ም

ቡና ለኢትዮጵያዊያን መጠጥ ብቻ አይደለም፤ ባህል፣ ታሪክ፣ የማህበራዊ ህይወት መስተጋብርና የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ጭምር ነው። በዚህ ሰፊ የቡና ባህልና ብዝሃ-ህይወት ውስጥ ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመናዊ ማኑፋክቸሪንግና እሴት በመጨመር (Value Addition) ረገድ የብዙዎችን ትኩረት እየሳበና የኢንዱስትሪው አዲስ ተስፋ እየሆነ የመጣ አንድ ስኬታማ የሀገር በቀል ኢንተርፕራይዝ አለ:- ጭቶ ቡና።

ይህ ኢንተርፕራይዝ በልዩ ጣዕሙና በጥራቱ የሚታወቀውን የኢትዮጵያን ቡና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ፣ የሀገራችንን የቡና ገበያ ወደ አዲስ ምዕራፍ ሊያሸጋግር የሚችል ትልቅ አቅም ይዞ ብቅ ብሏል።

የኢንተርፕራይዙ መስራች አቶ ስምኦን ሰርፁ ይባላሉ። አቶ ስምኦን ለረጅም ዓመታት ኑሯቸውን በውጭ ሀገር አድርገው የነበረ ቢሆንም፣ የሀገራቸውን ጥሪ ሰምተው በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። ወደ ሀገር ቤት ሲመለሱም ዝም ብለው አልነበረም፤ በማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ በመሰማራት ከፍተኛ ጥራት ያለውና እሴት የተጨመረበትን የኢትዮጵያ ቡና ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ትልቅ ራዕይ ሰንቀው እንጂ።

አቶ ስምኦንና ጭቶ ቡና ጥሬ ቡናን ዝም ብሎ ከመላክ ይልቅ በዘመናዊ ማሽኖች የተቆላ፣ የተፈጨና የታሸገ ከፍተኛ ጥራት ያለው ምርት በማዘጋጀት ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ላይ ይገኛሉ። ይህ ጉዟቸው ደግሞ በቅርቡ እጅግ አስደሳች ወደሆነ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል፤ ድርጅቱ በቅርብ ጊዜ በትልቁ የዓለም የገበያ መዳረሻ በሆነችው ቻይና ላይ አዲስ ቅርንጫፍ መክፈት ችሏል።

የጭቶ ቡና የዛሬ ስኬት በቀላሉ የተገኘ አይደለም። ጉዞው የጀመረው ከ4 ዓመታት በፊት ነበር። በወቅቱ በነበረው የፍራንኮ ቫሉታ ዕድል በመጠቀም ዘመናዊ የቡና ማቀነባበሪያ ማሽኖችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት፣ ስራቸውን በኪራይ ቤት ውስጥ በጠበበ ቦታ ጀመሩ። ስራ ሲጀምሩም በ5 ሰዎች ብቻ ነበር። ዛሬ ላይ ግን ጭቶ ቡና ያንን የፈተና ጊዜ አልፎ በመስፋፋት ላይ ይገኛል። በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ለገጣፎ የሚገኘውና በጥራትና በዘመናዊ አሰራር ላይ ባደረገው ትኩረት አሁን ላይ ከ40 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተረጋጋና ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠር ችሏል።

አቶ ስምኦን ስለ ጉዟቸውና ስላጋጠሟቸው እክሎች ሲናገሩ “ችግር የማደግ ምልክት ነው። እኛ ችግሮችን እንደ ፈተና በመውሰድ፣ ፈተናውን እንዴት ማለፍ እንደሚቻል ብቻ ትኩረት አድርገን እንሰራለን” በማለት የጠንካራ ስራና የዕድገት አስተሳሰብ (Growth Mindset) መርሆቸውን ይገልጻሉ።

ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና የወደፊት ተስፋ
ጭቶ ቡና በአሁኑ ወቅት የቡናውን ተፈጥሯዊ ጣዕምና መዓዛ ሳይለቅ፣ የዓለም አቀፍ ገበያን የጥራት መመዘኛ በሚያሟላ መልኩ እጅግ ዘመናዊ ማሽኖችን በመጠቀም ምርቱን እያዘጋጀ ይገኛል። ይህ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደግሞ ምርቱ በዓለም መድረክ ተወዳዳሪ እንዲሆን አድርጎታል።

ኢንተርፕራይዙ አሁን ካለበት ተስፋ ሰጪ ደረጃ ተነስቶ ይበልጥ እንዲያድግና የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ ግን የመስሪያ ቦታ አቅርቦት ወሳኝ መሆኑን መስራቹ ሳይጠቅሱ አላለፉም። በቀጣይም የተሻለና ሰፊ የመስሪያ ቦታ ቢመቻችላቸው፣ ይበልጥ ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠርና ምርትን በማሳደግ ረገድ ከዚህ የተሻለ የላቀ ውጤት ለማምጣት በትጋት እንደሚሰሩ አቶ ስምኦን ሰርፁ ገልጸዋል።

የጭቶ ቡና ጉዞ ለሌሎች ተመላሽ ዳያስፖራዎችና የሀገር ውስጥ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች ትልቅ ማሳያና አምሳያ ነው። በችግሮች ሳይበገሩ፣ ቴክኖሎጂን ከሀገር ምርት ጋር በማቀናጀት የተጀመረው ይህ ጉዞ፣ የኢትዮጵያን ቡና ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ ይበልጥ ከፍ እንደሚያደርገው ጥርጥር የለውም። ለመሰል ጠንካራ አምራች ኢንተርፕራይዞች የሚደረግ ማንኛውም ድጋፍ ደግሞ የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት የመገንባት ያህል ዋጋ አለው።



‎ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!

https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopment

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!ግንቦት 25 2018 ዓ.ምየመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀ...
02/06/2026

ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!

ግንቦት 25 2018 ዓ.ም

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡

ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡

በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡

ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡

የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ግንቦት 25 2018፣አዲስአበባ፣ኢትዮጵያ

https://www.facebook.com/share/p/1BLYc6SPYK/
01/06/2026

https://www.facebook.com/share/p/1BLYc6SPYK/

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-

• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤

በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡

ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።

Uummanni Itoophiyaa dinqisiisaafi ajaa'ibsiisaadha! Uumaa malee uummata keenya guutummaan beekuufi gamaaggamuu kan danda'u eenyu? Aadaa gabbataa, uummata biyya jaallatuufi fedhiisaa waloo eeguu danda'u ta'uusaa filannoo baranaatiin irradeebiidhaan addunyaatti agarsiiseera. Guyyaa seena-qabeessa har'aatiin:
- Qorriifi dukkanni halkani kan isaani hin sodaachifne,
- Aduun saafaafi bokkaan tasaa kan isaan jilbeenfachiifne,
- Cidhi, gaddi, da'umsiifi taateewwan hawaasummaa kanbiroon kan isaan dhorkine,
- Hiriironni dhedheeroon kan isaan hin nuffisiifne,
- Qaama miidhamtummaan sagalee kennuuf kan isaan hin daangessine,
- Dhukkubniifi dullumni abdii biyyaa arguuf kan isaan hin dhowwine,
- Daa'imasaanii kichuu bor biyya dhaalu baatanii filuun kan isaan hin dadhabsiifne
- Hundumaa caalaa lammiilee iyyiifi sodaachiifni diinaa isaan hin dhaabsifne,
Ciminni bu'aa bayii hedduu keessatti agarsiiftan gatii diimokraasiifi jiraachuu biyyatiif kanfalame waan ta'eef galata guddaatu malaafi.

Uummata kana tajaajiluun carroomuu waan ta'eef filatamtoonni warra isin kabajan kabajjanii uummata sirna diimookraasiif gatii baase kana qulqullummadhaan tajaajiluuf isin haa gahu.

The people of Ethiopia are an extraordinary and remarkable people. Other than the Creator, who can truly know and assess our people in their entirety? Through this year’s election, Ethiopians have once again shown the world that they are a people with a rich culture, deep patriotism, and the ability to safeguard the common good.

On this historic day:

* Citizens who were not intimidated by the cold and darkness of the night,
* Who were not deterred by the midday sun or sudden rain,
* Whom weddings, funerals, childbirth, and other social obligations did not prevent from participating,
* Who were not wearied by long lines,
* Whose physical disabilities did not stop them from casting their vote,
* Those whose illness and old age did not prevent from witnessing the hope of their country,
* Who were not exhausted by carrying their infant children; the future inheritors of the nation,
* And above all, whom the shouting and threats of enemies could not intimidate or stop;

The perseverance you demonstrated amid many challenges and hardships, against all odds, was a contribution made for democracy and for the very survival of the nation. For this, you deserve heartfelt gratitude.

It is a privilege to serve such a people. Therefore, may those who have been elected honor the trust placed in them and serve this people, with integrity and sincerity! A people who have paid a great price for the democratic system. May you be worthy of that responsibility.

መልካም የእሁድ እረፍት ለኢኮኖሚያችን ፈርጦች! ☕🏠==============//=========​ማኑፋክቸሪንግ ማለት ማሽንና ጥሬ ዕቃ ብቻ አይደለም፤ ከጀርባው የቤተሰብ ኃላፊነት፣ የልጆች ተስፋ ...
31/05/2026

መልካም የእሁድ እረፍት ለኢኮኖሚያችን ፈርጦች! ☕🏠
==============//=========
​ማኑፋክቸሪንግ ማለት ማሽንና ጥሬ ዕቃ ብቻ አይደለም፤ ከጀርባው የቤተሰብ ኃላፊነት፣ የልጆች ተስፋ እና የሀገር ኩራት ያለበት ታላቅ ጥበብ እንጂ።

ሳምንቱን ሙሉ ስታመርቱ የነበራችሁ አምራቾቻችን ዛሬ ከቤተሰቦቻችሁ ጋር መልካም የደስታ ጊዜ እንድታሳልፉ እንመኛለን!

የተሳካ ሳምንት የሚጀምረው በታደሰ አእምሮና በእሁድ ዕቅድ ነው። ​ውድ የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ባለቤቶች፤ ነገ አዲስ የሥራ ሳምንት እና ትልቅ ሀገራዊ ጉዳይ አለብን! ሳምንቱን ስንጀምር በታደሰ ተነሳሽነት፣ በጥራትና በፈጠራ ወደፊት ለመራመድ ዛሬ እሁድን በሚገባ እረፍት እናድርግ!

​💡 ትናንሽ እርምጃዎች ወደ ታላላቅ ፋብሪካዎች ይመራሉ። እኛም በዕውቀትና በቴክኖሎጂ ከጎናችሁ ነን!

​🇪🇹 የእሁድ ማሳሰቢያ፡ ዛሬ ለቤተሰብዎ የሚሸምቱት ማንኛውም ዕቃ የሀገር ውስጥ ምርት መሆኑን በማረጋገጥ አምራቾቻችንን ይደግፉ!

​ #እሁድ #ቤተሰብ



‎ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!

https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopmen

የሳምንቱ መጨረሻ ቀናት መልዕክት! 🛠️🇪🇹======////=====​ስኬት በአንድ ጀምበር አይገነባም፤ በየቀኑ በሚደረጉ ጥቃቅን ጥረቶች እንጂ። በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ  ዘርፍ የተ...
30/05/2026

የሳምንቱ መጨረሻ ቀናት መልዕክት! 🛠️🇪🇹
======////=====
​ስኬት በአንድ ጀምበር አይገነባም፤ በየቀኑ በሚደረጉ ጥቃቅን ጥረቶች እንጂ። በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ የተሰማራችሁ አምራቾች በሙሉ፣ በየቀኑ ለምታሳዩት ጽናት ትልቅ ክብር አለን።

​ዛሬ ቅዳሜ ቢሆንም፣ የሀገር ውስጥ ምርትን የመደገፍና የመሸመት ጉዟችን አይቆምም! የሀገራችንን ምርት እንሸምት፣ አምራቾቻችንን እናበረታታ!

​በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተሰማራችሁ ኢንተርፕራይዞች፣ ሳምንቱን በምን ዓይነት ትልቅ ስኬት ወይም መልካም ተሞክሮ አጠናቀቃችሁ?

​1️⃣ አዲስ የገበያ ትስስር ፈጠርን?

2️⃣ የምርት ጥራታችንን አሻሻልን?

3️⃣ አዳዲስ ሠራተኞችን ቀጠርን?

​ከነዚህ ውጪም የሆነ ስኬት ካላችሁ ኮሜንት ላይ አጋሩን፤ እርስ በርስ እንማማር፣ እንነቃቃ!









‎ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ይጎብኙ!

https://linktr.ee/ethiopianenterprisedevelopmen

Address

Ras Abebe Aragay Street
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 09:00 - 17:30

Telephone

+251115150333

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Enterprise Development posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Enterprise Development:

Share