Ethiopian Agricultural Transformation Agency

Ethiopian Agricultural Transformation Agency Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Agricultural Transformation Agency, Public & Government Service, Addis Ababa.

The ATI was established in 2010 to drive agricultural transformation by supporting governmental, non-governmental, and private sector partners to effect change.

  🧅🌊🌽በሸበሌ ወንዝ ዳር፣ መሬት ከሰብል ባሻገር ተስፋ እያበቀለ ነው። በዚህ ስፍራ የተፈጠረውን የልማት ዕድል በመጠቀም፣ የተፈናቀሉ ቤተሰቦች ራሳቸውን ችለው የተሻለ ኑሮ ለመገንባት እየተጉ...
19/08/2026



🧅🌊🌽በሸበሌ ወንዝ ዳር፣ መሬት ከሰብል ባሻገር ተስፋ እያበቀለ ነው። በዚህ ስፍራ የተፈጠረውን የልማት ዕድል በመጠቀም፣ የተፈናቀሉ ቤተሰቦች ራሳቸውን ችለው የተሻለ ኑሮ ለመገንባት እየተጉ ይገኛሉ።🕊️🌿

🧅🌊🌽ይህ ለውጥ በግጭት የተጎዱና የተፈናቀሉ ማህበረሰቦች ከአስቸኳይ ዕርዳታ ጥገኝነት በመላቀቅ ዘላቂ የኑሮ መሠረት እንዲገነቡ በሚያግዘው የሰብአዊ–ልማት–ሰላም (HDP) ትስስር ፕሮጀክት በኩል እየተጠናከረ ይገኛል።🕊️🌿

🧅🌊🌽በኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የሚተገበረውና በዴንማርክ ዓለም አቀፍ ልማት ኤጀንሲ (DANIDA) የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለት ይህ ፕሮጀክት፣ ሰብአዊ ዕርዳታን፣ መልሶ ማቋቋምን፣ የግብርና ልማትን፣ የገበያ ትስስርን እና ሰላም ግንባታን በማቀናጀት የተሻለና ዘላቂ የኑሮ መሠረት ለመገንባት ይሰራል።🕊️🌿

🧅🌊🌽ከ2017 ዓ.ም. እስከ 2021 ዓ.ም. የሚቆየው ይህ ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል በ12 ወረዳዎች እና በአጎራባች ኦሮሚያ ክልል በአንድ ወረዳ ይተገበራል። ፕሮጀክቱ በሰብልና በእንስሳት ኮሜርሻላይዜሽን፣ በተፈጥሮ ሀብት አያያዝ፣ በአግሮ ቢዝነስ ልማት እና በዲጂታል ግብርና ላይ ያተኩራል።🕊️🌿

🧅🌊🌽እስካሁን በሶማሌ ክልል ብቻ ከ90,000 በላይ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና ስደተኞች በተለያዩ የልማት እንቅስቃሴዎች እንዲሳተፉና ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስችሏል። ከዚህ ቁጥር በስተጀርባ ግን የራሳቸውን ኑሮ እንደገና እየገነቡ ያሉ ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች እና ማህበረሰቦች አሉ።🕊️🌿


🧅🌊🌽በደባልደግ ቀበሌ በሸበሌ ወንዝ ዳር የሚገኙ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችና የአስተናጋጅ ማህበረሰብ አባላት በአርሶ አደሮች የምርት ክላስተር በመደራጀት፣ በመስኖ የሚለማ መሬትን በጋራ እያለሙ ይገኛሉ።🕊️🌿

🧅🌊🌽በHDP ፕሮጀክት የቀረበላቸውን ጥራት ያለው ዘር፣ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎች፣ የምክርና የኤክስቴንሽን አገልግሎት፣ እንዲሁም ቴክኒካዊና የአመለካከት ለውጥ ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎችን በመጠቀም፣ ቀደም ሲል በበቂ ሁኔታ ያልለማውን መሬት በማልማት የምግብና የገቢ ምንጫቸውን አሳድገዋል።🕊️🌿

🧅🌊🌽የሽንኩርት ምርታቸው 1,625 ኩንታል የደረሰ ሲሆን፣ ኩንታሉን በአማካይ 7,000 ብር መሸጥ ችለዋል። ከአካባቢው ገበያ በተጨማሪ ምርታቸውን ወደ ጎዴ ከተማ በማጓጓዝ የተሻለ ገበያ በማግኘት የተሻለ ገቢ ማግኘት ችለዋል።🕊️🌿


የሽንኩርት ምርት ስኬትን ተከትሎ፣ ተመሳሳይ የምርት ክላስተር አቀራረብ በበቆሎ ምርትም ተጠናክሯል።🕊️🌿
🧅🌊🌽ሰባት የአርሶ አደሮች የምርት ክላስተሮች 95 ሄክታር በመስኖ የሚለማ መሬት በማልማት 2,755 ኩንታል የበቆሎ ምርት አግኝተዋል። ከምርቱ ሽያጭም 19.28 ሚሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል።
🧅🌊🌽እርዳታ ላይ በእጅጉ ጥገኛ ለነበሩና የኑሮ አማራጮቻቸው ውስን ለነበሩ ቤተሰቦች፣ እነዚህ ውጤቶች ከተሻለ ምርት መሰብሰብ በላይ ትርጉም አላቸው። መሬት፣ ቴክኖሎጂ፣ እውቀትና ክህሎት፣ የጋራ ተሳትፎ እና የገበያ ትስስር ሲጣመሩ፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል መሸጋገር እንደሚቻል የሚያሳዩ ተጨባጭ ማስረጃዎች ናቸው።🕊️🌿


🧅🌊🌽ጉዞው ምርታማነትን በማሻሻል ብቻ አያበቃም። የረጅም ጊዜ ዓላማው እነዚህን አርሶ አደሮች ከምርት ክላስተር ወደ ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር፣ ከዚያም በመጨረሻ ወደ አግሮ ቢዝነስ ኩባንያዎች በማሸጋገር፣ በግብርና የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ንቁ ተሳታፊና ባለቤት እንዲሆኑ ማስቻል ነው።🕊️🌿

📌Website: https://ati.gov.et/
📌Facebook: Ethiopian Agricultural Transformation Agency
📌Twitter or X:
📌LinkedIn: https://www.linkedin.com/posts/ethiopianata
📌YouTube: www.youtube.com/

17/08/2026

...

17/08/2026

Reflections from International Federation of Agricultural Journalists (IFAJ) President Steve Werblow Following his visit to ATI’s Interventions

  ! ይህንን ቀን በማስመልከት፣ በግብርና የእሴት ሰንሰለት በመሰማራት በትጋት እና በቁርጠኝነትና የራሳቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ሕይወት ከመቀየር ባለፈ፣ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ትርጉም ...
12/08/2026

!

ይህንን ቀን በማስመልከት፣ በግብርና የእሴት ሰንሰለት በመሰማራት በትጋት እና በቁርጠኝነትና የራሳቸውንና የቤተሰቦቻቸውን ሕይወት ከመቀየር ባለፈ፣ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ እያበረከቱ ያሉ ወጣቶችን አነቃቂ ታሪኮች እንድታነቡ በደስታ እንጋብዛችኋለን።

እነዚህ ባለራዕይ ወጣቶች፣ ከMastercard Foundation ጋር በመተባበር እየተገበርን ባለው፣ በግብርና ላይ ትኩረት ባደረገውና ከ80% በላይ ሴቶችን በሚያሳትፈው የወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ ፕሮግራም (አደይ) አማካኝነት፣ ለራሳቸው፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለማህበረሰባቸው የተሻለ ነገን ለመገንባት በትጋት እየሰሩ ይገኛሉ።

ወጣቶች ለኢኮኖሚያዊ ለውጥና ለሀገራዊ ዕድገት ወሳኝ የለውጥ አቅም ናቸው። ተገቢውን ዕድል፣ ድጋፍና አመቺ የሥራ አካባቢ ሲያገኙ፣ እምቅ አቅማቸውን በሙሉ በመጠቀም እሴት ማከል፣ ፈጠራን ማሳደግ፣ ግብርናን ማሻገር እና ለዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ ማድረግ ይችላሉ።
Mastercard Foundation

https://ati.gov.et/wp-content/uploads/2026/08/impact-bulletin-August_2026_zy-Re.pdf

📌Website: https://ati.gov.et/
📌Facebook: Ethiopian Agricultural Transformation Agency
📌Twitter or X:
📌LinkedIn: https://www.linkedin.com/posts/ethiopianata
📌YouTube: www.youtube.com/

As we commemorate the upcoming  , we celebrate the potential, energy, and innovation of young people to drive inclusive ...
11/08/2026

As we commemorate the upcoming , we celebrate the potential, energy, and innovation of young people to drive inclusive economic growth and sustainable development.

Through our Agriculture-focused Dignified Employment for Youth in Ethiopia (ADEY) Program, implemented in partnership with the Mastercard Foundation Foundation, more than 611,000 jobs are being created for young people across Ethiopia, with more than #80% of Participants being .

With the right opportunities, support, and enabling environment, young people can play a pivotal role in transforming the economy and unlocking their immense, untapped potential.

09/08/2026

ኢንዲያ ጣሂር ትባላለች፡፡ የ22 ዓመት ወጣትና የአንድ ልጅ እናት ናት፡፡ 12ኛ ክፍልን ተፈትና ውጤት ባለመምጣቱ ቤት ለመቀመጥ ተገደደች፡፡ ኢንዲያ በሥራ እድል ፈጠራ በኩል ተመልምለው በአደይ ፕሮግራም ከተካተቱ ወጣቶች አንዷ ናት፡፡
ኢንዲያ በአደይ ፕሮግራም የክህሎትና ሌሎች ሞያዊ ስልጠናዎችን ወስዳ ከጓደኞቿ ጋር በመደራጀት የፍየል ማድለብ ሥራ እየሠራች ትገኛለች፡፡ ዛሬ በአካባቢዋ ለብዙዎች የሚያስተምር ታሪክ አላት፡፡
እስኪ ሙሉ ታሪኳን ከስር ባለው ቪድዮ እንከታተል
Mastercard Foundation

🌾🐪የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከሶማሊ ክልል ጋር በመተባበር የሶማሊ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤትን በይፋ አስጀመረ🚜🌾🚜🌾የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩ...
06/08/2026

🌾🐪የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከሶማሊ ክልል ጋር በመተባበር የሶማሊ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤትን በይፋ አስጀመረ🚜🌾

🚜🌾የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ከሶማሊ ክልል ግብርና ቢሮ ጋር በመተባበር የሶማሊ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤትን በጂግጂጋ ከተማ በይፋ አስጀምሯል። የምክር ቤቱ መቋቋም በክልሉ የግብርና ዘርፍ ቅንጅታዊ፣ ቀልጣፋ እና ውጤታማ አስተዳደርን በማጠናከር የግብርና ትራንስፎርሜሽንን እና ዘላቂ የልማት አጀንዳው ለማፋጠን ያለመ ነው።

🌾🐪በዛሬው ዕለት የተካሄደው መርሃ ግብር የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ ኃላፊዎችን፣ የልማት አጋሮችን፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችን እና የማኅበረሰብ መሪዎችን አሳትፏል። በዝግጅቱ ላይ ተሳታፊዎች የምክር ቤቱን ተልዕኮ፣ ሥልጣን፣ የአስተዳደር መዋቅር እና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ገለጣ ተደርጎላቸዋል: :

🌾🐪በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎረሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ፍሬው ተገኘ፣ ኢንስቲትዩቱ በሶማሊ ክልል ያለውን ተሳትፎ በማስፋትና ዘላቂ አዎንታዊ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ፕሮግራሞችን በመተግበር ድጋፉን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

🌾🐪በተጨማሪም፣ በ Mastercard Foundation የሚደገፈው ከ80 በመቶ በላይ ተጠቃሚዎቹ ሴቶች የሆኑበት የወጣቶች የሥራ ፈጠራ ፕሮግራም እና በዴንማርክ መንግሥት የሚደገፈው በሰው ሰራሽና በተፈጥሯዊ ምክንያቶች ተፈናቃዮችን ያማከለ የሰብዓዊ ድጋፍ–ልማት–ሰላም (Humanitarian–Development–Peace Nexus) ፕሮጀክት ጠንካራ ውጤቶችን እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

🌾🐪የሶማሊ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር ኢብራሂም ኡስማን በበኩላቸው ፣ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎረሜሽን ኢንስቲትዩትከ ክልሉ የግብርና ትራንስፎርሜሽን የፍኖተ- ካርታ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ምክር ቤቱ ምስረታ ድረስ ያደረገውን ተከታታይና ውጤታማ ትብብር በማድነቅ፣ ምክር ቤቱ የክልሉን የግብርና አቅም በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት እምነታቸውን ገልጸዋል: :

🌾🐪ከቀረቡት ገለጻዎችና ከተካሄደው የባለድርሻ አካላት ውይይት በኋላ፣ የሶማሊ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት በይፋ ተመሥርቶ ሥራውን በአጨር ጊዜ ውስጥ እንደሚጅምር አቶ ኢብራሂም ቃል ገብተዋል።

🌾🐪የምክር ቤቱ መቋቋም በመንግሥት ተቋማት፣ በልማት አጋሮች፣ በግሉ ዘርፍ እና በአርሶ አደሮች መካከል ያለውን ቅንጅት እንደሚያጠናክር ይጠበቃል። በተጨማሪም የግብርና ዘመናዊነትን ለማፋጠን፣ የምግብ ዋስትናን ለማሻሻል፣ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር እና በኢትዮጵያ ሶማሊ ክልል ዘላቂ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽንን ለማሳካት ጠንካራ የቅንጅት መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል።

📌Website: https://ati.gov.et/
📌Facebook: Ethiopian Agricultural Transformation Agency
📌Twitter or X:
📌LinkedIn: https://www.linkedin.com/posts/ethiopianata
📌YouTube: www.youtube.com/

06/08/2026

በኢትዮጵያ ፣ ብዙ ሥራ አጥ ወጣቶች ሕገ-ወጥ ስደትን የተሻለ ሕይወት ለማግኘት ብቸኛው አማራጭ አድርገው ይወስዱታል።
የ23 ዓመቷ ጤናዬ ተረፈ ግን የሥራ ማጣት ፈተና ተስፋ አስቀርጦ ለስደት አልዳረጋትም። ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷ በኋላ የሥራ ዕድል ለማግኘት ብዙ ተቸግራ ነበር፤ ነገር ግን የADEY ፕሮግራም የሙያ ክህሎት፣ ድጋፍ ሕይወትን እንዳዲስ እንድትጀምር ረድቷታል፡፡
ከጤናዬ የምንማረው ወጣት ሴቶች ተገቢ ዕድልና ድጋፍ ሲያገኙ፣ ሕልማቸውን በራሳቸው ማኅበረሰብ ውስጥ እውን ማድረግ እንደሚችሉ ነው።
▶️ ሙሉ ታሪኳን በሚከተለው ቪድዮ ይመልከቱ
Mastercard Foundation

🌱 🌿ዛሬ ከግብርና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በመላው ኢትዮጵያ በተካሄደው   በአንድ  #ጀምበር የመትከል   ተሳትፈናል።🌱 🌿የተከልነው እያንዳንዱ ችግኝ አረንጓዴ እና ጽኑ ኢትዮጵ...
03/08/2026

🌱 🌿ዛሬ ከግብርና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በመላው ኢትዮጵያ በተካሄደው በአንድ #ጀምበር የመትከል ተሳትፈናል።

🌱 🌿የተከልነው እያንዳንዱ ችግኝ አረንጓዴ እና ጽኑ ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ቁርጠኝነት ያሳያል። በጋራ በመሥራት አካባቢያችንን እንጠብቃለን፣ የተጎዱ መሬቶችን እንመልሳለን፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እንሰራለን።

🌱 🌿ይህ የጋራ ጥረት ለእኛና ለመጪው ትውልድ የተሻለና ዘላቂ ልማትን ለመገንባት ያለንን ተስፋ ያጠናክራል።

📌Website: https://ati.gov.et/
📌Facebook: Ethiopian Agricultural Transformation Agency
📌Twitter or X:
📌LinkedIn: https://www.linkedin.com/posts/ethiopianata
📌YouTube: www.youtube.com/

31/07/2026

ለታይ ሰይፉ ትባላለች፤ የ32 አመት ወጣትና የሁለት ልጆች እናት ናት፡፡ በአክሱም ከተማ በአደይ ፕሮግራም በግብርና ዘርፍ በሥራ ዕድል ፈጠራ ከተሰማሩት ወጣት አካል ጉዳተኛ ሴቶች አንዷ ናት፡፡ ለታይ በሥራዋም ሆነ በዐለት ተዕለት ኑሮዋ ፈታኝ ሁኔታ የሆነባት አካል ጉዳቷን ባማከለ መልኩ እንደ ልቧ መንቀሳቀስ አልመቻሏ ነው፡፡ በዚህ ምክንያትም ልጇን ከትምህርት እያረፈደም ቢሆን በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዋ ውስጥ ያግዛታል፡፡ ዛሬ ግን ይህ ታሪክ ተቀይሯል፡፡ እስኪ ሙሉ ታሪኩን በዚህ ቪድዮ ውስጥ ይመልከቱት፡፡

Mastercard Foundation

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251115570678

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Agricultural Transformation Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Agricultural Transformation Agency:

Shortcuts

Share