Ministry of Planning and Development - Ethiopia

Ministry of Planning and Development - Ethiopia This page provide information about activity's that took place at FDRE Ministry of Planning and Dev't

የአፍሪካ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የአየር ንብረት እርምጃዎችን በምግብ ስርዓቶች እና በግብርና ላይ ለማጠናከር ያለመ አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ።አዲስ አበባ ጳጉሜን 2 / ...
07/09/2026

የአፍሪካ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የአየር ንብረት እርምጃዎችን በምግብ ስርዓቶች እና በግብርና ላይ ለማጠናከር ያለመ አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ።

አዲስ አበባ ጳጉሜን 2 / 2018 ዓ.ም (የፕ.ል.ሚ)

በአፍሪካ የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ያላቸውን ንቁ ተሳትፎ ለማጠናከር ያለመ አህጉራዊ መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ።

በአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ትብብር (Alliance for Food Sovereignty in Africa) እና በተባባሪ ድርጅቶች አዘጋጅነት ለሶስት ቀናት የሚቆየው ይህ ታላቅ ጉባኤ በምግብ ስርዓቶችና በግብርና ላይ የአፍሪካን አቅም ለማጠናከር እና የተናበበ አህጉራዊ አቋም ለመገንባት ያለመ ነው።

በጉባኤው ከመላው አፍሪካ የተውጣጡ 100 የሚጠጉ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች፣ አርሶ አደሮች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የአፍሪካ ህብረት ተወካዮች እና የአየር ንብረት ተደራዳሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የቀድሞ የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የያደም (YADAM) ፋዉንዴሽን መስራች እና የአፍሪካ የስነ-ምግብ አምባሳደር አቶ ደመቀ መኮንን በመርሃ-ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር ስነ-ምግብ የአንድ ግለሰብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ለአገርና ለአህጉር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት እንዲሁም ለተሻለ አእምሯዊና አካላዊ ልማት ወሳኝ መሰረት መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም ስነ-ምግብ፣ ጤና እና የአየር ንብረት ለውጥ ተነጣጥለው የማይታዩና ለአጠቃላይ ስነ-ምህዳር ጤናማነት ከፍተኛ ድርሻ ያላቸው መሆናቸውን አብራርተዋል።

የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የፅህፈት ቤት ሃላፊ ሀና አበበ በበኩላቸው፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ፍፁም አሰፋን በመወከል ባደረጉት ንግግር፣ የአየር ንብረት ለውጥ በአፍሪካ የምግብ ዋስትና እና በግብርና ምርታማነት ላይ እያደረሰ ያለውን ተፅዕኖ ለመቋቋም ጠንካራ አህጉራዊ አቋም መያዝ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ የግብርና ዘዴዎችን፣ የስነ-ምህዳር ጥበቃን እና የስነ-ምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ አሰራሮችን መተግበር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

ጉባኤዉ በአፍሪካ የምግብ ስርዓትና ግብርና ዘርፍ የሚታዩ ተደራራቢ ፈተናዎችን በመፍታት፣ ዘላቂ የግብርና አሰራሮችን በማጎልበት እና አፍሪካውያን በአለም አቀፍ መድረኮች አንድ ወጥ አቋም እንዲይዙ በማድረግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ይጠበቃል።

07/09/2026

ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬቶች የቆመች ኢትዮጵያ!

እንኳን ለጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን!ኢትዮጵያ የብልጽግና ትልሞቿን በፅኑ መሠረት እየገነባች ነው፡፡ ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት ፖሊሲዎች እና ዕቅዶች እየተመራች ለኹለ...
07/09/2026

እንኳን ለጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

ኢትዮጵያ የብልጽግና ትልሞቿን በፅኑ መሠረት እየገነባች ነው፡፡ ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት ፖሊሲዎች እና ዕቅዶች እየተመራች ለኹለንተናዊ ብልጽግና እየተጋች ትገኛለች፡፡ በየዘመን አንጓዉ ያጋጠሟትን ፈተናዎች በተደመረ ዐቅም እየተሻገረች፤ ከችግሮች እና ፈተናዎች ዕድሎችን መንጭቃ እያወጣች፤ ነገዋን በጠንካራ መሠረት ላይ እያጸናች ነው፡፡

ለዘመናት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ከዓድማስ እስከ ዓድማስ የሚያውለበልበው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነገዉን ታሳቢ አድርጎ እንደ ቢሾፍቱ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ባሉ መሠረተ ልማቶች እና ኹለንተናዊ ለውጦች ውስጥ እያለፈ ነው፡፡ ፡፡ ነባር እና ዐዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች እየለሙ እና ተደራሽነታቸዉ እያደገ ነው፡፡ ግብርናችን ከዝናብ ጥገኝነት እየተላቀቀ እና የገጠሩም የከተሜዉም የሥራ ዕድል እየኾነ ነው፡፡ የታዳሽ ኃይል አማራጮቻችን ከውኃ፣ ከነፋስ፣ ከፀሐይ፣ ከጂኦተርማል እና ከኑክሊየር ኃይል እንዲኾኑ የመደመር መንግሥት ሌት ተቀን እየሠራ ነው፡፡

ከተሞቿ ጎስቋላ ገጽታቸዉ እየተቀየረ እና ነገን እየዋጁ፤ መሠረተ ልማቶቿ እየተስፋፉ እና እየተቀናጁ፤ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ዐቅሟ እየተጠናከረ፤ የቀጣናዉ የታዳሽ ኃይል ማእከልነቷ እያደገ፤ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ ደረጃ ጥቅም ላይ እያዋለች ለመጪዉ ትውልድ ኹለንተናዊ ብለጽግና እየሠራች ነው፡፡

የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያበስሩ፤ እመርታዊ ዕድገቷን የሚያፋጥኑ ፅኑ መሠረቶች ላይ እየተገነቡ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያንም ሥርዐቱን ለማጽናት እና መሻታቸዉን እውን ለማድረግ ያላቸዉን ቁርጠኝነት በመንግሥት ጥሪዎች በሚያሳዩዋቸው ተሳትፎዎች እየገለጹ ነው፡፡

በ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ ከሌሊት እስከ ሌሊት ፈተናዎችን ተቋቁመዉ ድምፅ መስጠታቸዉ እና ውጤቱን በደስታ መቀበላቸው፤ በአረንጓዴ ዐሻራ በየዓመቱ እያደገ የመጣ ተሳትፎ እና ስኬት ማስመዝገባቸው፤ የልዩነት ሐሳቦችን በሰላማዊ መንገድ ለመግራት ሀገራዊ ምክክርን መምረጣቸው ኢትዮጵያውያን በመደመር መንግሥት ትልሞች ላይ የያዙትን የጋራ ተስፋ እና ለስኬቱም እያደረጉ ያለዉን ርብርብ የሚያሳይ ነው፡፡

የዴሞክራሲ ሥርዐትን በማንበር፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመከተል፤ የከተሞችን ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ ወደ ገጠር በማላመድ፤ የታዳሽ ኃይል አቅርቦትን በመሻሻል፤ የትራንስፖርት መሠረተ ልማቱን በማዘመንና በማስፋፋት ለኢትዮጵያ ኹለንተናዊ ብልጸግና ፅኑ መሠረት እየተቀመጠ ነው፡፡ ለዚህም ነው ጳጒሜን 2ን “የማንሰራራት ቀን” በሚል ስያሜ እያከበርን የምንገኘው፡፡

ጳጒሜን 2 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

አዲስ አበባ

ጳጉሜን 2የማንሰራራት ቀንከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬቶች የቆመች ሀገር !
07/09/2026

ጳጉሜን 2

የማንሰራራት ቀን

ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬቶች የቆመች ሀገር !

ጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን
07/09/2026

ጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን

ኢትዮጵያ የራሷን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሥነ ምሕዳር እያነፅች እንደሆነ ያውቁ ኖሯል?ለበለጠ መረጃ:➜ መላ ኤአይ: mela.aii.et➜ ፋይዳ: id.gov.et➜ መሶብ: https://mesob...
06/09/2026

ኢትዮጵያ የራሷን የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሥነ ምሕዳር እያነፅች እንደሆነ ያውቁ ኖሯል?

ለበለጠ መረጃ:

➜ መላ ኤአይ: mela.aii.et

➜ ፋይዳ: id.gov.et

➜ መሶብ: https://mesobcenter.et/

➜ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት: aii.et

ጳጉሜን 1 የእመርታ ቀንእመርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት!ከጳጉሜ ቀናት አከባበር መርሐ-ግብሮች አንዱ የሆነው "የእመርታ ቀን"  ዛሬ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሠራራት!...
06/09/2026

ጳጉሜን 1
የእመርታ ቀን
እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት!
ከጳጉሜ ቀናት አከባበር መርሐ-ግብሮች አንዱ የሆነው "የእመርታ ቀን" ዛሬ ጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "እመርታ ለኢትዮጵያ ማንሠራራት!" በሚል መሪ ቃል በኢኮኖሚ ዘርፍ ተቋማት አዘጋጅነት በግብርና ሚኒስቴር የኮንፈረንስ ማዕከል ተካሂዷል፡፡

የእመርታ ቀን አከባበር በምስል

የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚያረጋግጥ መሠረታዊ ለውጥ አከናውነናል:- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህየኢትዮጵያን ማንሠራራት የሚያመላክተው የጳጉሜን 1 የእመርታ ቀን ሀገራዊ መድረክ ምክ...
06/09/2026

የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚያረጋግጥ መሠረታዊ ለውጥ አከናውነናል:- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

የኢትዮጵያን ማንሠራራት የሚያመላክተው የጳጉሜን 1 የእመርታ ቀን ሀገራዊ መድረክ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በይፋ ተከፍቷል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ ከፈተና ወደ ዕድል፣ ከጥገኝነት ወደ ራስን መቻል፣ ከተረጂነት ደግሞ ወደ አምራችነት ተሸጋግራለች።

በሁለንተናዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና በፋይናንስ ሥርዓት ዘመናዊነት ያስመዘገበችው መዋቅራዊ ስኬት ለኢንቨስትመንት እና ሀገር በቀል ሀብት ማሰባሰብ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱን አመላክተዋል።

በበጋ ስንዴ፣ በምግብ ሉዓላዊነትና በሌማት ትሩፋት የተመዘገቡት አኩሪ ውጤቶች የሀገራዊ ነጻነታችንና የጽናታችን ማረጋገጫዎች ናቸው ሲሉም አብራርተዋል።

በ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ እና በማዕድን ዘርፍ በተገኘው እመርታ የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት መቻሉንና የኤክስፖርት ገቢ ማደጉን ጠቅሰዋል።

በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ የተዘረጉት የኢ-ፋይሊንግ እና የኢ-ፔይመንት ዲጂታል አሠራሮች አዲስ የታማኝነትና የቅልጥፍና ባህል መፍጠራቸውን አንስተው፣ አምራችነትን እንደ ዋና ዕሳቤ፣ ስልትና ግብ በመውሰድ እያንዳንዱ ተግባር ዕሴት የሚጨምር መሆን እንዳለበት አሳስበዋል።

"ኢትዮጵያ እየተለወጠች፣ እያመረተችና እያንሠራራች ነው" መሆኑን የገለጹት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እመርታ የመጨረሻ መዳረሻ አይደለም፤ ወደ ከፍታ የሚያሻግረን መንገድ ነው ብለዋል።

በመሆኑም ዛሬ ያገኘነውን እመርታ ወደ ነገ ከፍታ ለመቀየር፣ የበለጠ መሥራት፣ የበለጠ ማምረት እና የበለጠ መፍጠር ይጠበቅብናል ሲሉም አስገንዝበዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእመርታ ቀን መልዕክት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜን 1 ቀን የእመርታ ቀንን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት አባቶቻችን የኢት...
06/09/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእመርታ ቀን መልዕክት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜን 1 ቀን የእመርታ ቀንን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል ብለዋል።

ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንደምንገኝ አስታውሰዋል።

ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን።

እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

06/09/2026

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ministry of Planning and Development - Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ministry of Planning and Development - Ethiopia:

Shortcuts

Share