Gullele woreda 9 communication

Gullele woreda 9 communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gullele woreda 9 communication, Government Organization, Addis Ababa.
(1)

05/06/2026
በሁሉም  ፈጣሪ አምላክ ረድቶን 7ኛውን ዙር ምርጫ ባጠናቀቅንበት ማግስት   ዛሬ 8ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ክፍት አድርገናል። ለህዝባችን በገባነው ቃ...
04/06/2026

በሁሉም ፈጣሪ አምላክ ረድቶን 7ኛውን ዙር ምርጫ ባጠናቀቅንበት ማግስት ዛሬ 8ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ክፍት አድርገናል።

ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት ዛሬ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ ገንብተን በቴክኖሎጂ ተደራጅቶ 96 ተገልጋዮችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግዱ መስኮቶች ያሉት፣ በ22 ተቋማትና በ114 አገልግሎቶች ስራ አስጀምረናል።

ማዕከሉ ከፍ ባለ ጥራት እጅግ ውብ፣ ፅዱ፣ አካታች የሆነ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ፣ የህፃናት ማቆያ ያለው፣ ለሰራተኞችም ለተገልጋዮችም ምቹ ሆኖ የተገነባ ነው።

በቀጣይም በርካታ አገልግሎቶችን ወደ መሶብ ማዕከል በማስገባት ነዋሪዎች ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት እንዲያገኙ እናደርጋለን።

የከተማችን ነዋሪዋች መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አግልግሎት ለዘመናት አስልቺ ከነበረውና ውጣ ውረድ ከበዛበት እና በእጅ መንሻ ከተማረራችሁበት ቢሮክራሲ የሚያላቅቃችሁ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ! በማዕከላቱ በቦታ ሳትገደቡ በሚቀርባችሁ በየትኛውም ማዕከል በመገኘት ተገልገሉ።

ይህ ማዕከል ተጠናቆ ስራ እንዲጀምር ያስተባበራችሁትን በሙሉ ከልብ አመሰግናለሁ ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቧቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ጉለሌ የእንጦጦ የወንዝ ዳርቻ ልማት  ለቱሪዝም መስህብ የሆነና ዜጎችን በስራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚ ያደረገ ፤ለነዋሪዎች ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ፤አስደማሚ የእጅ አሻራዎች የስራ ውጤት የሆነውን የል...
04/06/2026

ጉለሌ የእንጦጦ የወንዝ ዳርቻ ልማት ለቱሪዝም መስህብ የሆነና ዜጎችን በስራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚ ያደረገ ፤ለነዋሪዎች ምቹ ሁኔታ የፈጠረ ፤አስደማሚ የእጅ አሻራዎች የስራ ውጤት የሆነውን የልማት ፕሮጀክችት ይጎብኙ!!

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁየአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡ምርጫውን አ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ

የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡

ኢትዮጵያ መርጣለች !! 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ በድምጹ የሚመራውን ሕጋዊ መንግሥት ለማቋቋም ያለው ጉጉት እጅግ በጣም የላቀ መሆኑን ትልቅ አስረጅ ሆኖ በፖለቲካ ታሪካችን ውስጥ ...
02/06/2026

ኢትዮጵያ መርጣለች !!

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ በድምጹ የሚመራውን ሕጋዊ መንግሥት ለማቋቋም ያለው ጉጉት እጅግ በጣም የላቀ መሆኑን ትልቅ አስረጅ ሆኖ በፖለቲካ ታሪካችን ውስጥ ተመዝግቧል።

የፖለቲካ ሀሳብን በሰላማዊ መንገድና በሕዝበ ውሳኔ መዳኘት የሰለጠነ ህዝብ አስተሳሰብ ነው።

የጉለሌ ነዋሪውም በየአካባቢው ወደሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች በማምራት የተለጠፉትን ውጤቶች በጉጉት እየተመለከተ ይገኛል።

የእንጦጦ ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት እና የአገልግሎት መስጫዎች ፕሮጀክት በውስጡ ምን ይዟል፦👉 597 ሄክታር ቦታ የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ ልማት፤👉 15 ሄክታር መሬትን በማልማት በአረንጓዴ ተ...
02/06/2026

የእንጦጦ ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት እና የአገልግሎት መስጫዎች ፕሮጀክት በውስጡ ምን ይዟል፦

👉 597 ሄክታር ቦታ የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ ልማት፤

👉 15 ሄክታር መሬትን በማልማት በአረንጓዴ ተሸፍኗል፤

👉 የ210 ቀፎ ዘመናዊ የንብ እርባታ፤

👉 የአበባ እና የእጽዋት ጋርደኖች ልማት፤

👉 የአካባቢውን ማህበረሰብ የስራ ባህል የሚዘክሩ ሃውልቶችና ቅርሶች ግንባታ፤

👉 22 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ፤

👉 8 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መንገድ፤

👉 6 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር የተሽከርካሪ መንገድ፤

👉 4 ኪሎ ሜትር የሃይኪንግ መንገድ፤

👉 2 አዲስ የተሽከርካሪ ድልድዮች ግንባታ፤

👉 3 ነባር የተሽከርካሪ ድልድዮች ዕድሳት ፤

👉 39 የውሃ መከላከያ ግድቦች ግንባታ (ቼክ ዳም) ወዘተ... በስጡ አጠቃልሎ ይዟል።

ዛሬ የተመረቀው ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለው የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት (በምሥል)
02/06/2026

ዛሬ የተመረቀው ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለው የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት (በምሥል)

02/06/2026
02/06/2026
‎ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት፣ ዛሬ ጠዋት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ስራ አስጀምረናል።‎‎ይህ ትልቅ ተነሳሽነት፤ የ...
02/06/2026

‎ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት፣ ዛሬ ጠዋት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ስራ አስጀምረናል።

‎ይህ ትልቅ ተነሳሽነት፤ የተራቆቱ አካባቢዎችን በዘመናዊ የአፈር ጥበቃ እና በወንዝ ማጣራት ወደ አረንጓዴ ስፍራዎች በመቀየር፣ የፍራፍሬ ፓርኮችን ከእግር ጉዞ እና ከብስክሌት መንገዶች ጋር በማቀናጀት መዲናችንን አድሷል።

‎በአጠቃላይ 22.25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን የሚሸፍነው ይህ ፕሮጀክት፤ የማይቆራረጥ የልማት ስራችን ህያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሃገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ አሕመድ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gullele woreda 9 communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gullele woreda 9 communication:

Share