07/09/2026
“ወርቃማው ሰኞ” ለሀገር ማንሰራራት
(ጉለሌ ወረዳ 9 ኮሙኒኬሽን 2/13/18)
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 አስተዳደር በተካሄደው የ“ወርቃማው ሰኞ” የመንግሥት ሰራተኞች ውይይት መድረክ ላይ የተሳተፉ ሰራተኞች፣ መድረኩ ለሃገር ማንሰራራትና ለተቋማዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገለጹ።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉት ሰራተኞች እንደተናገሩት፣ በሳምንቱ መጀመሪያ የሚካሄደው ይህ የውይይት መድረክ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል፣ የአስተሳሰብ አንድነት ለመፍጠርና የስራ ተነሳሽነትን ለማሳደግ የሚረዳ ነው::
በተጨማሪም ሰራተኛው በቁርጠኝነትና በተነሳሽነት ህዝብን ለማገልገል የሚያስችለውን አቅም እንደሚፈጥርለት ጠቁመዋል።
የውይይቱ ዋነኛ ዓላማውም በመንግሥት መስሪያ ቤቶች ውጤታማ አሰራርን በመገንባትና የአገልግሎት ጥራትን በማረጋገጥ ለአገራዊ ማንሰራራት የበኩሉን አዎንታዊ ድርሻ እንዲወጣ ማስቻል መሆኑ ተመልክቷል።