07/09/2026
"የማንሠራራት ቀን" ምክንያት በማድረግ የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ ተከፈተ።
በአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ጳጉሜን 2 የሚከበረውን "የማንሠራራት ቀን" ምክንያት በማድረግ የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ ተከፈተ:: በአውደ ርዕዩ ላይ ኮርፖሬሽኑ በቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ውስጥ ያለፈባቸውን ሂደቶች የሚያሳዩ ፎቶ ግራፎች ለእይታ ቀርበዋል፡፡
የኮርፖሬሽኑ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አየለ ከፋለ አውደ ርዕዩን በከፈቱበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰችበት ከፍታ በታላቅ ጥረት የተገኘ መሆኑን አስታውሰው ከሰው ልጅ መሠረታዊ ፍላጎቶች አንዱ በሆነው የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት የተሰማራው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት ተቋሙ ባከናወናቸው ተግባራት ተስፋ ሰጪ ስኬት ማስመዝገብ እንደተቻለ ጠቁመዋል:: በቀጣዩ በ2019 በጀት ዓመትም እየተመዘገበ ያለውን አበረታች ውጤት ይበልጥ በማዳበር የተሻለ ስኬት ለማስመዝገብ ግንባታው ሂደት ውስጥ ተሳታፊ የሆኑ ሥራ ተቋራጮች እና አማካሪዎች እንዲሁም መላው ህብረተሰብ ከኮርፖሬሽኑ ጎን በመቆም እያሳዩት ያለውን የሥራ ተነሳሽነት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበው ኮርፖሬሽኑም አስፈላጊውን ድጋፍ ናክትትል በማድረግ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር መኮንን ሚጀና በበኩላቸው ኮርፖሬሽኑ ወጪ ቆጣቢ ቤቶችን በመገንባት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን አመልክተው በቀጣይም የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ በመከተል ግንባታውን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስና የመኖሪያ ቤት ችግርን ለመቅረፍ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡
በፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ ላይ ኮርፖሬሽኑ ከጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በተጨማሪ በቸግኝ ተከላ መርሀ ግብር አረንጓዴ አሻራ በማኖር እንዲሁም በማዕድ ማጋራትና በሌሎችም ሰው ተኮርተግባራት ያከናወናቸውን አበይት ሁነቶች የሚያመለክቱ ምስሎች ለእይታ ቀርበዋል፡፡
"የኢትዮጵያ ማንሠራራት" የሚለውን መሪ ቃል ተከትሎ የተከፈተው የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ እሰከ መጪው ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በዛሬውየመክፈቻ መርሀ ግብር ላይ የኮርፖሬሽኑ የበላይ አመራሮች እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጭ:-
https://linktr.ee/aahdc
ዻጉሜን 2 ቀን 2018 ዓ/ም
የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን
ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት