24/08/2026
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ለኦዲተርሮች እና ለአስተዳደር ሰራተኞች ሙያዊ ስልጠና መስጠት ጀመረ።
*************************************************
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ የሚከናወኑ የኦዲት ሥራዎችን ጥራት፣ ቅልጥፍና እና ታማኝነት ይበልጥ ለማሳደግ ዘመናዊ አሰራርን የተከተለ ሙያዊ ስልጠና ለኦዲተሮች እና ለአስተዳደር ሰራተኞች መስጠት ጀመረ።
ይህ ስልጠና የተዘጋጀው የከተማው ተቋማት የፋይናንስ አስተዳደር፣ የንብረት ቁጥጥር እና የኦዲት አሰራር ሂደት ለማዘመን እና የሰራተኞችን አቅም ለማሳደግ ታስቦ መዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ ጠቅሰው ተቋሙ አሰራሩን በማዘመን ውስን የሆነውን የህዝብ ሃብት በአግባቡ መያዙን የማረጋገጥ ተልዕኮውን በብቃት እንዲወጣ ለማድረግ ይህ ስልጠና የላቀ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
ዋና ኦዲተር አመንቴ መቻሉ አክለው ኦዲተር መስሪያ ቤቱ ተቋማዊ አቅሙን በመገንባት የከተማዋን የፋይናንስ ደህንነት እና መልካም አስተዳደር ለማረጋገጥ የሚያስችሉ መሰል ስልጠናዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው በስልጠና የተሳተፉ ሰራተኞች ያገኙትን እውቀት ተጠቅመው ህግንና ስርዓትን የተከተለ ጥራት ያለው የኦዲት ሪፖርት ማቅረብ የሚያስችል አቅም ማጎልበት ይገባል ብለዋል።
**********************************************
የኮሙንኬሽን ዳይሬክቶሬት
ነሐሴ 18/2018