የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ - Addis Ababa Culture & Arts bureau

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ - Addis Ababa Culture & Arts bureau

የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ - Addis Ababa Culture & Arts bureau This is The Official Page Of Addis Ababa City Adminstration Culture &Arts Bureau

“ኪነ-ጥበብ ለአካል ብቃት፤ ለአእምሮ ንቃት” በሚል መሪ ቃል ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው ታላቅ የኪነ-ጥበብ የንቅናቄ መድረክ በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ!፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨...
04/09/2026

“ኪነ-ጥበብ ለአካል ብቃት፤ ለአእምሮ ንቃት” በሚል መሪ ቃል ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው ታላቅ የኪነ-ጥበብ የንቅናቄ መድረክ በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ባኪ በቢሮ | ነሃሴ 29/2018 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ በተፈሪ መኮንን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ባዘጋጀው በዚህ መድረክ ላይ ከ300 በላይ አማተር የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የከተማዋን የኪነ-ጥበብ እንቅስቃሴ ወደ አዲስ የፈጠራ ምዕራፍ ማሸጋገርና የባለሙያዎችን አቅም ማሳደግ ነው። ኪነ-ጥበብ የማኅበረሰብን ማንነት ከማንጸባረቅ ባለፈ አማተሩን ከእውቅ አርቲስቱ ጋር የሚያቀራርብ፣ ማኅበራዊ ትስስርን የሚያጠናክርና በሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ ጉልህ ድርሻ ያለው በመሆኑ፣ ቢሮው ይህንን እምቅ አቅም ለመጠቀምና ባለሙያዎችን ወደ ተሻለ የሙያ ደረጃ ለማሸጋገር ይህንን አዲስ የሥልጠና፣ የንቅናቄና የልምምድ እድል አመቻችቷል።

በማጠቃለያ መድረኩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ አመራሮች የስራ መመሪያና አደራ ያስተላለፉ ሲሆን፣ የቢሮው ም/ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አዲሱ ሻንቆ ሰልጣኞች ያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር በመቀየርና ሙያዊ ስነ-ምግባርን በመላበስ የሀገራቸውን ስም እንዲያስጠሩ ጥሪ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል የቢሮው የኪነ-ጥበብ ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሉባባ ጀማል የሀገርን ባህልና እሴት ጠብቆ ኪነ-ጥበብን ወደ ላቀ ደረጃ የማሸጋገር ኃላፊነት የወጣቶችና የባለሙያዎች ድርሻ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተጨማሪም የኪነ-ጥበብ ኢንዱስትሪ ማበልፀግና ማስፋፋት ዳይሬክተር አቶ ፀጋ ተመም ባስተላለፉት መልዕክት፣ መዲናችን አዲስ አበባ ለዘርፉ በሰጠችው ልዩ ትኩረት ውብ የማሳያ መድረኮች መገንባታቸውን ጠቅሰው፣ የኪነ-ጥበብ ማህበረሰቡም ይህንን የሚመጥን ጥራት ያለው ስራ ማቅረብ አለበት ካሉ በኋላ ቢሮው ዘርፉን የበለጠ ለማጠናከር ለተለያዩ ባለድርሻ አካላትና መምህራን የሚሰጠውን ድጋፍና ስልጠና አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

ንቅናቄው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ የተሳካ እንዲሆን ከፍተኛ አስዋጽኦ ላደረጉ አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀት በቢሮው ከፍተኛ አመራሮች ተበርክቶላቸዋል።

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬ...
03/09/2026

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል።

‎በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል።

‎ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው።
‎ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፉ Act For Early Years  ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” ተብለው እውቅና ተሰጣቸው።ይህ እውቅና የከንቲባ አዳነች አቤቤ አመራራቸውንና...
03/09/2026

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፉ Act For Early Years ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” ተብለው እውቅና ተሰጣቸው።

ይህ እውቅና የከንቲባ አዳነች አቤቤ አመራራቸውንና የከተማ አስተዳደሩ ለሕፃናት እድገት እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት በተለይም በ"የአዲስ አበባ የወደፊት ተስፋ የቅድመ ልጅነት እድገት ተነሳሽነት" የተሰጠ እውቅና ነው።

ኢኒሼቲቩ ቀዳማይ ልጅነትን በመንግሥታት ፖሊሲዎች እና በዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት አጀንዳ ማዕከል ላይ ለማስቀመጥ በትኩረት ይሰራል።

ይህ እውቅና የተሰጠው ከቀድሞው የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም አቀፍ ትምህርት ልዩ መልዕክተኛ ጎርደን ብራውን በኩል የኢኒሼቲቭ አጋሮች በመወከል ሲሆን ፣ UNICEF እና UNESCOን ጨምሮ ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የተሰጠ ነው።

እውቅናው አዲስ አበባን በአፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት እድገት የከተማ አመራር ተምሳሌት ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያጠናክረው ይታመናል።

02/09/2026

የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ ጥበብ ቢሮ ታላቅ የዕደ ጥበባት አውደ ርዕይ ከነሐሴ 29 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በመገናኛ የካ ክ/ከተማ፣ በሜክሲኮ ታክሲ ተራ፣ አዲሱ ገበያ ጃንቦ ህናፃ እና በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ግቢ ውስጥ በርካታ የስራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች በተገኙበት በድምቀት ይካሄዳል፡፡

የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ ጥበብ ቢሮ 14ኛውን ከተማ አቀፍ የንባብ ፌስቲቫል አስመልክቶ ከምሁራንና ከተለያዩ የሙያ ዘርፍ ተወካዮች ጋር የሐሳብ መዋጮ መድረክ አካሄደ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ባኪ...
01/09/2026

የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ ጥበብ ቢሮ 14ኛውን ከተማ አቀፍ የንባብ ፌስቲቫል አስመልክቶ ከምሁራንና ከተለያዩ የሙያ ዘርፍ ተወካዮች ጋር የሐሳብ መዋጮ መድረክ አካሄደ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ባኪ ቢሮ | ነሀሴ 26/2018 ዓ.ም

ቢሮው “ከስክሪን ቀንሰን መጽሐፍትን እንግለጥ” በሚል መሪ ሐሳብ ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ በቆየው 14ኛው ከተማ አቀፍ የንባብ ፌስቲቫል፣ በመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ፣ በፓናል ውይይቶች፣ በሐሳብ መዋጮ መድረኮችና በእውቅናና ምስጋና መርሃ ግብሮች አጠናቋል።

በመድረኩ “ንባብን እንደገና እንጀምር” በሚል መነሻ ሐሳብ ያጋሩት የቢሮ ኃላፊ ክብርት ዶ/ር ኂሩት ካሳው፣ ፌስቲቫሉ የንባብ ባህልን ለማጠናከር ጠቃሚ ውጤቶችን ማስገኘቱን ገልጸዋል።

በዚህም በሁሉም ክፍለ ከተሞች የንባብ ክበቦች መቋቋማቸውን ጠቅሰው፣ ከመጪው የትምህርት ዘመን ጀምሮ መርሃ ግብሩ በትምህርት ቤቶችም ተጠናክሮ እንደሚሰራበት አመላክተዋል።

በውይይቱ ላይ የዘመናዊ ስክሪንና የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም በንባብ ባህል ላይ እያሳደረ ያለው ተጽዕኖም ተነስቷል። ቴክኖሎጂን ሙሉ በሙሉ መተው ሳይሆን፣ የስክሪን አጠቃቀምን በማመጣጠን ለንባብ በቂ ጊዜ መመደብ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በተለይም ግለሰቦች በየቀኑ የሚያነቡትን የገጽ ብዛትና ለንባብ የሚመድቡትን ሰዓት በማቀድ የንባብ ልምዳቸውን ማዳበር እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

የአብርኆት ቤተመጻሕፍት ዳይሬክተር ዶ/ር ሙሉቀን ታሪኩ በበኩላቸው፣ለንባብ የተፈጠሩ አዳዲስ እድሎችንና የተገነቡ ቤተመጻሕፍትን በአግባቡ መጠቀም የህብረተሰቡ ድርሻ መሆኑን አስገንዝበው ለዚህ ተደራሽነትን ለማስፋፋት በሞሰብ የአንድ ማዕከል ውስጥም ባለጉዳዮች የሚስተናገዱበት ዕድል እንዲፈጠር እየተመቻቸ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ደራሲ ዘነበ ወላ በበኩላቸው፣ ንባብ የሰውን የማሰብና የመተንተን አቅም በማሳደግ የተሟላ ስብዕና ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም በተለይ ወጣቱ ትውልድ ከማህበራዊ ሚዲያና ከሌሎች የዲጂታል መዝናኛዎች ጋር የሚያሳልፈውን ጊዜ በማመጣጠን ወደ መጽሐፍ ንባብ እንዲመለስ ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ ላይ የንባብ ባህልን ለማስፋፋት የመጻሕፍት ልገሳን ማጠናከር፣ በተለያዩ ተቋማት የንባብ ማዕከላትና ክበቦችን ማስፋፋት እንዲሁም አዳዲስ አንባቢዎችን ለመፍጠር የተቀናጀ ሥራ ማከናወን እንደ መፍትሔ አቅጣጫዎች ቀርበዋል።

በአጠቃላይ ቴክኖሎጂንና ማህበራዊ ሚዲያን በአግባቡ ከመጠቀም ጎን ለጎን፣ ንባብን የዕለት ተዕለት ልምድ ማድረግ የተሻለ ዕውቀት ያለው፣ የሚያስብና የሚተነትን ትውልድ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑ በመድረኩ ላይ ተገልጿል።

"ከማህበራዊ ሚዲያ ወደ ማህበራዊ የንባብ እንለወጥ"

በመዲናዋ 20 ተጨማሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ - ከንቲባ አዳነች ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በተያዘው በጀት ዓመት በአዲስ አበባ 20 አዳዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አ...
01/09/2026

በመዲናዋ 20 ተጨማሪ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ - ከንቲባ አዳነች
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

በተያዘው በጀት ዓመት በአዲስ አበባ 20 አዳዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ይከፈታሉ አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቀጣይ አምስት ዓመትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት ማጠቃለያ መድረክ ተካሂዷል።

ከንቲባ አዳነች በዚህ ወቅት ÷ በምርጫ ለሕዝብ የገባነውን ቃል ለመፈጸም 24/7 በትጋት በመስራት አዲስ አበባን ተምሳሌታዊ ከተማ እናደርጋታለን ብለዋል።

ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚተገበረው የመዲናዋ ስትራቴጂክ ዕቅድ ከሀገራዊ ርዕይ፣ ፖሊሲና ስትራቴጂ አንጻር የተቃኘ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም ጠንካራ የተቋም ግንባታ፣ የተቀናጀ ጥራት ያለውና ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ አይበገሬ አረንጓዴ ኢኮኖሚ መፍጠር፣ የፋይናንስ አቅምን ማጠናከር እንዲሁም ዘላቂ ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ ላይ ትኩረት ይደረጋል ነው ያሉት፡፡

አሁን ላይ በከተማ አስተዳደሩ 11 የመሶብ ማዕከላት መኖራቸውን ጠቁመው ÷ በ2019 በጀት ዓመት ተጨማሪ 20 ማዕከላት እንደሚከፈቱ ተናግረዋል፡፡

ማዕከላቱ የሚከፈቱት ወረዳዎችን በክላስተር በማደራጀት እንደሆነና በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት 66 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላትን ለመክፈት መታቀዱን አመልክተዋል።

በሁሉም ዘርፍ የተሳለጠ እና ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ከንቲባዋ አረጋግጠዋል፡፡

ለተከታታይ ሁለት ቀናት ስናካሂድ የነበረውን የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድና የ2019 በጀት ዓመት ዝርዝር እቅድ ውይይት አጠናቀናል።  በውይይታችንም  እቅዶ...
31/08/2026

ለተከታታይ ሁለት ቀናት ስናካሂድ የነበረውን የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድና የ2019 በጀት ዓመት ዝርዝር እቅድ ውይይት አጠናቀናል።

በውይይታችንም እቅዶቹን ይበልጥ ተጨባጭ በማድረግ በቀጣይ አምስት ዓመታትም አልቀን በመፈፀም፣ የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት ሳንሸራርፍ ለመፈፀም፣ የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ እጅግ ጠቃሚ እና ገንቢ ተግባቦት እና ዝግጁነት ፈጥረናል።

ከሀገራዊ ፖሊሲና ስትራቴጂያችን በመነሳት ህዝባችንም በድጋሚ ሲመርጠን “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌታዊ ሀገር” ብለን የገባነውን ቃል ለመፈፀም እንደ አዲስ አበባ “አዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌት” ለማድረግ የጀመርነውን ጉዞ ዋና ርዕያችን አድርገናል።

ለእቅዳችን ስኬት መሰረቶች የሆኑት ባለፋት አምስት ዓመታት አቅደን አልቀን ያስመዘገብነው ውጤት፣ የህዝብና መንግሥት ከደህነት የመውጣት ፍላጎት፣ በከተማችን የተፈጠረው የስራ ትጋት፣ በታማኝነት ማገልገል፣ በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ በፍጥነትና በጥራት የመፈፀም ልምድ፣ በጀትን በመቆጠብ መጠቀም ትልቅ ስንቅ ናቸው።

በቀጣይ ትኩረታችንም ተቋማዊ ብቃትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ በአሰራር፣ በአደረጃጀት፣ የዘመነ ቴክኖሎጂ በሚጠቀም የላቀ አገልግሎት መስጠት፣ የተቀናጀ ጥራት ያለው ሰፊ መሰረት ልማት በፍጥነት መገንባት፣ አዲስ መሰረተ ልማት መገንባት ብቻ ሳይሆን ነባሮቹን በሚገባ ማስተዳደር፣ የንፁህ መጠጥ ውኃና የቤት አቅርቦት ማሳደግ፣ የማህበራዊ ዘርፍ (ጤና፣ ትምህርት …) ተደራሽነትና ጥራት እንዲሁም ፍትሃዊነትን በማረጋገጥ አልቀን መፈፀም፣ ዓለማቀፍ ስታንዳርድ ያሟላ የጤና አገልግሎት መስጠት፣ የጤና ቱሪዝም ማዕከል መሆን፣ የከተማችንን የቱሪዝም መዳረሻ ከተማነት ማረጋገጥ፣ አዲስ አበባን ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ አፍሪካዊት ከተማ ማድረግ፣ ለወጣቶች ተጠቃሚነት፣ የሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ እንዲሁም በኢኮኖሚና ማህበራዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ፣ የበጎ ፍቃድ ስራዎችን ባህል በማድረግ ማህበራዊ ፍትህን ማንገስ፣ የኮሪደርና ወንዝ ዳርቻ ልማትን ማጠናከር፣ እንዲሁም ማህበራዊ ፍትህን ማንገስ፣ አምራችነትን ማሳደግ፣ ተረጂነትን መቀነስ፣ የስራ እድልን በሰፊው መፍጠር፣ የከተማ ግብርና፣ የፍሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን ማዘመን፣ ፅዳትና የቆሻሻ አወጋገድን ባህል ማድረግ … ወዘተ፤ በአጠቃላይ ከተማችንን ጽዱ፣ ውብ እና ለሁሉም የምትመች ከተማ ማድረግ የእቅዳችን ትኩረቶች ናቸው።

የእቅዳችን ቅኝትም ስትራቴጂክ እይታ ያለው፤ ራዕያችንን ለማሳካት አቅዶ መተግበር፤ የተለጠጠ፣ አካታች፣ ፍትሃዊ እንዲሁም አሳታፊ እንዲሆን ማድረግ ነው።

ይህ የእቅድ ውይይት አመራራችን በዋናነት እቅዱን በተሟላ ሁኔታ የተረዳ፣ ስትራቴጂክ አመራር የሚሰጥ፣ በአስተሳሰብ አንድነት የሚቆም፣ ከተለያየ የጥቅም ትስስር ነፃ የሆነ፣ የይቻላል መንፈስን የተላበሰ፣ በአፈፃፀም ተቀራራቢ የሆነ፣ ትጋት እና የአመራር ዲሲፒሊን ያለው፣ ግልፅነት እና ተጠያቂነት እያሰፈንን ህዝቡ የከተማችንን ራዕይና ግብ የተጋራ እንዲሆን በተለየ መንገድ የሄድንበት የውይይት መድረክ ነው።

ልማትን በመንግስት ብቻ ማሳካት እይቻልም። በመሆኑም መላው የከተማችን ነዋሪዎች፣ ግለሰቦችና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ፣ የግሉን ዘርፍ ማበረታታት፣ በጊዜ የለንም መንፈስ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ አሳድገን በከተማችን ለማሳካት የተወጠነውን ትልቅ ራዕይ ለመፈፀም በላቀ እንተጋለን።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ዛሬ የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት  መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል። በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የ...
31/08/2026

ዛሬ የከተማ አስተዳደራችንን የቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መላው የከተማችን አመራሮች በተገኙበት አስጀምረናል።

በስድስተኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ህዝባችን የሰጠንን ሃላፊነት መነሻ ያደረገ ስትራቴጂክ እቅድ ነድፈን ቃላችንን በተግባር ቆጥረን ፈፅመን የከተማችንን ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን እንዲሁም ከተማችን ደግሞ ተወዳዳሪ እንድትሆን አድርገናል።

ይህንኑ መነሻ በማድረግ የከተማችን ነዋሪ እምነት አድሮበት ዳግም መርጦን ሀላፊነት ሰጥቶናል።
የዛሬው ውይይትም የከተማችን ነዋሪ የጣለብንን እምነት እና የሰጠንን ሀላፊነት መነሻ ያደረገ፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት እና የ2019 በጀት ዓመት የእቅድ ዝርዝር ግቦች ላይ ተወያይተን በማዳበር የባለፉት አምስት ዓመታት አፈፃፀምን በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጁነታችንን የምናረጋግጥበት መድረክ ነው።

እነዚህን ዝርዝር ውይይቶች ስናደርግ 24/7 የመፈጸም ባህላችንን ይበልጥ በማሳደግ፣ አመራራችን ከፊት ሆኖ የበለጠ እየሮጠ ህዝባችንንና የልማት አጋሮቻችንን በማስተባበርና ተሞክሮዎችን በማስፋት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በሀገራዊ ማንሰራራት ውስጥ የአዲስ አበባን የብልፅግና ተምሳሌትነት ለማረጋገጥ እንተጋለን።

በተጨማሪም በክረምት የያዝናቸው የ90 ቀን ስራዎች ውስጥ የ60 ቀናት አፈፃፀማችንንም የምንገመግምበት የውይይት መድረክ ነው።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአዲስ አበባ ባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ አማተር ባለሙያዎችን ያቀፈ ታላቅ የኪነ-ጥበብ ንቅናቄ መድረክ ማስጀመሩን አስታወቀ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ባኪ ቢሮ | ነሐሴ 25/2018 ዓ.ምኪነ-ጥበብ የህ...
31/08/2026

የአዲስ አበባ ባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ አማተር ባለሙያዎችን ያቀፈ ታላቅ የኪነ-ጥበብ ንቅናቄ መድረክ ማስጀመሩን አስታወቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ባኪ ቢሮ | ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም

ኪነ-ጥበብ የህብረተሰብን ማንነት ከማንጸባረቅ ባለፈ ለሀገር ማህበራዊ ትስስር፣ ኢኮኖሚያዊ እሴት እና ፖለቲካዊ መረጋጋት የሚጫወተው ሚና የጎላ መሆኑ ይታወቃል። ይህንን የዘርፉን እምቅ አቅም ወደ ሙሉ ሀገራዊ ፋይዳ ለመቀየር የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ ከዛሬ ነሐሴ 25 - 29/ 2018 ዓ.ም የሚቆይ ታላቅ የኪነ-ጥበብ ንቅናቄ መድረክ ማካሄድ ጀምሯል።

በዚሁ አምስት ቀናት በሚቆየው የንቅናቄ መድረክ በቴአትር፣ በፊልም፣ በባህላዊ ውዝዋዜ እና ዘመናዊ ዳንስ ዘርፎች የተሰማሩ ከ300 በላይ የአማተር ኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

በአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ የኪነ-ጥበብ ኢንዱስትሪ ማበልፀግና ማስፋፋት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፀጋ ተመም እንደገለጹት፤ መድረኩ ለተሳታፊዎች በየሙያ ዘርፋቸው የተለያዩ ቴክኒካል ትምህርቶች፣ ሙያዊ ውይይቶች እንዲሁም ጥራታቸውን የጠበቁ የተግባር ልምምዶች ይሰጣሉ ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም ይህ ንቅናቄ የአማተር ባለሙያዎችን ክህሎትና የፈጠራ አቅም በማሳደግ ወደ ፕሮፌሽናል ደረጃ እንዲሸጋገሩ እንደሚያስችል ገልጸዋል። በተጨማሪም የከተማዋን ብሎም የሀገሪቱን የኪነ-ጥበብ እንቅስቃሴ በማጠናከር አዲስ አበባን የባህልና የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት የሚያፋጥን መሆኑን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ - Addis Ababa Culture & Arts bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ - Addis Ababa Culture & Arts bureau:

Shortcuts

Share