Ministry of Health,Ethiopia

Ministry of Health,Ethiopia This is the official page of the Ministry of Health of the FDRE, a government department responsible for Ethiopian's people Health.
(523)

The Ministry of Health shall have Powers and Duties to:-
- formulate the country’s health sector development programme; follow up and evaluate the implementation of same;
-support the expansion of health services coverage; follow up and coordinate the implementation of health programs financed by foreign assistance and loans;
-direct, coordinate and follow up implementation of the country’s health

information system;
- devise and follow up the implementation of strategies for the prevention of epidemic and communicable diseases;
-follow up and coordinate the implementation of national nutrition strategies;
-take preventive measures in the events of emergency situations that threaten public health, and coordinate measures to be taken by other bodies;
-ensure adequate supply and proper utilization of essential drugs and medical equipment in the country;
-prepare the country’s health services coverage map; provide support for the expansion of health infrastructure;
-supervise the administration of federal hospitals;
-collaborate with the appropriate bodies in providing quality and relevant health professionals’ trainings within the country;
-provide appropriate support to promote research activities intended to provide solutions for the country’s health problems and for improving health service delivery;
- expand health education through various appropriate means;
- ensure the proper ex*****on of food, medicine and health care regulatory functions.

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን በመጎብኘት የተለያዩ የጤና ልማት ፕሮጀክቶችን ስራ አስጀምረዋል__________ለጤና ሚኒስቴር እና የክልል ...
05/08/2026

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን በመጎብኘት የተለያዩ የጤና ልማት ፕሮጀክቶችን ስራ አስጀምረዋል
__________

ለጤና ሚኒስቴር እና የክልል ጤና ቢሮዎች የጋራ መድረክ አማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ባህር ዳር ከተማ የገቡት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን በመጎብኘት የተለያዩ የጤና ልማት ፕሮጀክቶችን ስራ አስጀምሯል።

የሆስፒታሉን የተለያዩ የስራ እንቅስቃሴዎችን ተዘዋዉረዉ የጎበኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በፈለገ ህይወት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግቢ በ 200 ሚልዮን ብር ወጪ የተገነባ የኦክስጂን ማምረቻ ማእከልን መርቀዉ ስራ አስጀምሯል።

በተመሳሳይ የሆሲፒታሉ የቀዶ ጥገና እና የጨቅላ ህጻናት ህክምና ማዕከል እድሳት እንድደረግለት በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን የዲጅታል ቋት ማእከልና ማህበረሰቡን ከመድሃኒቶች እና አገልግሎቶች ጋር ማገናኘት ዓላማ ያደረገውን የጤንነቴ መተግበሪያ መርቀው ስራ አስጀምሯል።

በጤንነቴ መተግበሪያ አገልግሎት ከ 560 በላይ የተለያዩ የመድሃኒት አይነቶች መረጃ ተጭነዉ ወደ ስራ መገባቱ የተገለጸ ሲሆን ከመድሃኒት አገልግሎትና ተያያዝ መረጃዎች ጋር ተያይዞ ያለዉን ችግር በመሰረታዊነት የሚቀርፍ የጤንነቴ መተግበሪያ አገልግሎት በሁሉም ክልሎች በፍጥነት እንዲተገበርና የህብረተሰባችን ተጠቃሚነት እንዲረጋጥ ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ አሳስበዋል።

የመርሃ ግብሩ ታዳሚዎች በሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ችግኝ ተከለዋል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

ህብረተሰቡ የቲቢ ምርመራን በአቅራቢያው ማግኘት የሚያስችለው NPOC-TB አዲስ ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ዋለ_________የቲቢ ምርመራን ለህብረተሰቡ በአቅራቢያው ለማድረስ የሚያስችለው የNear P...
05/08/2026

ህብረተሰቡ የቲቢ ምርመራን በአቅራቢያው ማግኘት የሚያስችለው NPOC-TB አዲስ ቴክኖሎጂ ስራ ላይ ዋለ
_________

የቲቢ ምርመራን ለህብረተሰቡ በአቅራቢያው ለማድረስ የሚያስችለው የNear Point of Care (NPOC-TB) ምርመራ ቴክኖሎጂ የማስተዋወቅና የአሰልጣኞች ስልጠና መድረክ ተካሄዲል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ድጉማ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር አዲሱ ቴክኖሎጂ በመጀመሪያ በተመረጡ የጤና ተቋማት ተግባራዊ ሆኖ በቀጣይ በመላ አገሪቱ እንደሚስፋፋ አስታውቀዋል።

ቴክኖሎጂው የቲቢ ምርመራ መዘግየትንና ያልተመረመሩ ታማሚዎችን በመቀነስ የቲቢ ቁጥጥርን ለማጠናከር ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም አመልክተዋል። ሰልጣኞችም ያገኙትን እውቀትና ክህሎት ወደ ታችኛው የጤና አገልግሎት ደረጃ በማውረድ ለሌሎች ባለሙያዎች ስልጠናና ድጋፍ እንዲሰጡ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ሀይሉ በበኩላቸው፣ የቲቢ ምርመራና ክትትልን ለማጠናከር አዳዲስ የላብራቶሪ ቴክኖሎጂዎችን በማስገባት እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፣ NPOC-TB ቴክኖሎጂም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን አስረድተዋል።

የጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሕይወት ሰለሞን እንዳሉት፣ NPOC-TB የቲቢ ምርመራን ፈጣንና ተደራሽ ከማድረጉም በላይ የታካሚዎችን ጉዞ፣ የናሙና ማጓጓዣና ተደጋጋሚ የጤና ተቋም ጉብኝት በመቀነስ ከሪፈራል ምርመራ ጋር የሚያያዙ ወጪዎችንና መዘግየቶችን ለመቀነስ ያግዛል ብለዋል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለምትወስዱ ተመዛኞች በሙሉ________የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ ጤና ባለሙያዎች ከነሀሴ 13 - 15/2018 ዓ.ም ለሚሰ...
05/08/2026

የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና ለምትወስዱ ተመዛኞች በሙሉ
________

የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ ጤና ባለሙያዎች ከነሀሴ 13 - 15/2018 ዓ.ም ለሚሰጠው የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የመፈተኛ ጣቢያ የምትመርጡት እስከ ነገ ሀምሌ 30/2018 ዓ.ም ድረስ እንድታጠናቅቁ እናሳስባለን፡፡

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

የእናቶች እና ህፃናት ጤናን ለማሻሻል የሚረዳ የአድቮከሲ ኢኒሼቲቭ ላይ ውይይት ተደረገ__________የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ኢኒሼቲቩን ካቀረበው ከጌትስ ፋውንዴሽን ልኡካን ቡድን ...
05/08/2026

የእናቶች እና ህፃናት ጤናን ለማሻሻል የሚረዳ የአድቮከሲ ኢኒሼቲቭ ላይ ውይይት ተደረገ
__________

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ኢኒሼቲቩን ካቀረበው ከጌትስ ፋውንዴሽን ልኡካን ቡድን ጋር ባደረጉት ውይይት ለተደረገው ትብብር ፋውንዴሽኑን አመስግነዋል።

የእናቶች ጤናን በማሻሻል የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ያሉት ዶ/ር መቅደስ፤ የእናቶች እና የሕፃናትን ጤና መንከባከብ የሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት ነው ብለዋል።

በመንግስት ተቋማት መካከል የምግብ እና የስርዓተ-ምግብ (Nutrition) ቅንጅትን ስለማጠናከር የተወያዩ ሲሆን፤ ኢኒሼቲቩ በእናቶች እና ሕፃናት ጤና መሻሻል ላይ የሚጨበጥ ውጤት ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

የክትባት አገልግሎትን ከስርዓተ-ምግብ (Nutrition) ጋር ማቀናጀት፤ እና የእናቶች፣ የሕፃናት እና የጨቅላ ህፃናት ጤናን የተመለከቱ የዘላቂ ልማት ግቦችን (SDG) ለማሳካት በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል።

ለቅስቀሳ (Advocacy) እንቅስቃሴው (initiative) የተዘጋጀ የተግባር እቅድ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

የጡት ማጥባት አስፈላጊነት እና ጥቅሞች___________የጡት ማጥባት ለሕፃናት ጤናማ እድገትና የበሽታ መከላከል አቅም እንዲሁም ለእናቲቱ ጤና እጅግ አስፈላጊ የሆነ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው። ህጻ...
05/08/2026

የጡት ማጥባት አስፈላጊነት እና ጥቅሞች
___________

የጡት ማጥባት ለሕፃናት ጤናማ እድገትና የበሽታ መከላከል አቅም እንዲሁም ለእናቲቱ ጤና እጅግ አስፈላጊ የሆነ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው። ህጻናት በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት የእናት ጡት ወተት ብቻ (Exclusive Breastfeeding) ማግኘት አለባቸው።

👉በጡት ማጥባት ወቅት ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ፦

▪️የመጀመሪያውን ወተት (እንገር / Colostrum) ለህጻኑ ይስጡ:- እንገር የመጀመሪያው የእናት ወተት ሲሆን ሕፃኑን ከበሽታዎች የሚጠብቅ በጣም ከፍተኛ የመከላከያ ኃይል ያለው ነው። ይህ ወተት ከፍተኛ የበሽታ መከላከል አቅም ያላቸውን ንጥረ ነገሮች ይዟል።

▪️ጡት ማጥባትን በመጀመሪያው 1 ሰዓት ውስጥ ይጀምሩ:- ሕፃኑ ከተወለደ በኋላ በመጀመሪያው 1 ሰዓት ውስጥ ጡት ማጥባት መጀመር ለሕፃኑ ሕይወት ማዳን፣ ለእናቱም ፈጣን ማገገም ይረዳል። እንዲሁም የጡት ወተት ምርት በቶሎ እንዲጀምር እና በቂ የሆነ ወተት እንዲመነጭ ያደርጋል።

▪️ህጻኑ/ኗ በፈለገ/ች ጊዜ ያጥኑ:- ሕፃኑ/ኗ በፈለገ/ች ጊዜ በቀንና በሌሊት በተደጋጋሚ ጡት ያጥቡ። ይህ የወተት ምርትን ያበረታታል።

▪️ትክክለኛ የማጥባት ሁኔታን ይጠቀሙ (Positioning & Latching)፦ በአግባቡ ለማጥባት እናቲቱ በተመች ሁኔታ ተቀማጣ ማጥባት አለባት። ሕፃኑ አፉን በደንብ ከፍቶ ጠቆር ያለዉን የጡትዎን ክፍል አብዛኛዉን በመጉረስ፣ ጉንጮቹ ሞላ በመድረግና በመሀል ትንሽ እያረፈ በደንብ መሳቡን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡

▪️ሙሉ በሙሉ በጡት ወተት ብቻ ማሳደግ፦ በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ውስጥ ውሃን ጨምሮ ምንም አይነት ተጨማሪ ምግብ ወይም ፈሳሽ ሳይሰጥ በጡት ወተት ብቻ ህጻናትን ማሳደግ ይገባል። ይህም የጡት ወተት በመጀመሪያዎቹ 6 ወራት ለህጻናት እድገት የሚያስፈልጉትን ንጥረ ምግቦች እንዲሁም ውሃን ስለሚይዝ ነው።

▪️የበሽታ መከላከል ጥቅሞች፦ የጡት ወተት ሕፃናትን ከተቅማጥ፣ ከሳንባ ነቀርሳ (Pneumonia) እና ከጆሮ ኢንፌክሽን የሚከላከል ሲሆን እናቶችንም ከጡት እና ከማህፀን ካንሰር ተጋላጭነት ይከላከላል።

▪️በህመም ወቅት ጨምረው ጡት ያጥቡ:- ከ 6 ወር በታች የሆኑ ህጻናት በተለያየ ህመም በሚጠቁበት ወቅት ከሌላ ጊዜ አብልጠው/ጨምረው ያጥቡ። ይህም በህመም ወቅት በሽታን ለመቋቋም እንዲሁም በቶሎ ለማገገም ይረዳቸዋል።

▪️ከ6 ወር ጀምሮ(181 ቀን) ከተጨማሪ ምግብ ጎን ለጎን ጡት ማጥባትን ይቀጥሉ:- ከ 181ኛ ቀን ጀምሮ እድሜውን የሚመጥን፣ የተመጣጠነና የተሰባጠረ ተጨማሪ ምግብ በመጀመር ጡት ማጥባቱን እስከ 2 ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ይቀጥሉ።

▪️የበቂነት ምልክቶች፦ ሕፃኑ በቀን ቢያንስ ከ6-8 ጊዜ የሚሸና ከሆነ እና በቂ የክብደት እድገት የሚያሳይ ከሆነ፥ ህጻኑ በቂ ወተት ማግኘቱን ማረጋገጥ ይቻላል።

▪️የእናቶች ስነ-ምግብ ሁኔታ፦ የሚያጠቡ እናቶች ከሌላው ጊዜ ተጨማሪ ሁለት ጊዜ የተሰባጠረ ምግብ ማገኘት የሚገባዘው ሲሆን፣ በቂ ፈሳሽ (ውሃ፣ ሾርባ) እና አትክልትና ፍራፍሬዎችንም አብዝተው መመገብ ይኖርባቸዋል።

👉 የአባቶች እና የቤተሰብ ሚና፦

▪️የቤት ውስጥ ስራዎችን ማገዝ፦ አባቶችና ቤተሰብ የሚያጠቡ እናቶችን በቤት ውስጥ ስራ በማገዝ በቂ የእረፍት ጊዜ እንዲኖራቸው ማድረግ አለባቸው።

▪️ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ መስጠት፦ በእናቶች ላይ የሚፈጠረውን ድካም እና ጭንቀት ለመቀነስ አዎንታዊ እና ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ ማድረግ ወሳኝ ነው።

▪️የተመጣጠነ ምግብ ማቅረብ፦ እናቲቱ በቂ እና የተመጣጠነ ምግብ ማግኘቷን ማረጋገጥ እና ማበረታታት።



Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

"ለህፃናት የመጀመሪያው ክትባት የእናት ጡት ወተት ነው!" ዶ/ር ደረጄ ድጉማ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ________የጡት ማጥባት ሳምንት የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ ...
04/08/2026

"ለህፃናት የመጀመሪያው ክትባት የእናት ጡት ወተት ነው!"
ዶ/ር ደረጄ ድጉማ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ
________

የጡት ማጥባት ሳምንት የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ "ጡት ማጥባት ለዘላቂ የህይወት ጅማሮ ውጤታማ ተግባራትን እናጠናክር" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በቂርቆስ ጤና ጣቢያ የማስጀመሪያ ኘሮግራም በማካሄድ ተከብሯል።

በማስጀመሪያው ኘሮግራም ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ በመልዕክታቸው እናቶች ህጻናትን እንደወለዱ በአንድ ሰዓት ውስጥ የእናት ጡት ወተት ማጥባት አስፈላጊ እንደሆነ አንስተው እስከ 6 ወር ያለ ተጨማሪ ምግብ እንዲሁም እስከ 2ዓመት የእናት ጡት ማጥባት ጠቃሚ እንደሆነ አብራርተዋል።

አያይዘውም ለህጻናት የተስተካከለ የአእምሮ እና ለጤናማ የሰውነት እድገት የእናት ጡት ወተትን ማጥባት ያስፈልጋል ብለው ለህፃናት የመጀመሪያው ክትባት የእናት ጡት ወተት እንደሆነ አክለው ለእናቶችም ለስነ አእምሮ ጤና ወሳኝ ነው ብለዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዱሬቲ ጀማል በበኩላቸው ጡት የማጥባት ልምድን በተሻለ ለማስጠበቅና የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ መንግስት በጤናው ስርዓት በስራ ቦታዎች እንዲሁም በማህበረሰብ ደረጃ ለጡት ማጥባት አመቺ ሁኔታን ለመፍጠር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በማስጀመሪያ ኘሮግራሙ ላይ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ,የአለም ጤና ድርጅት ተወካይ ,የዩኒሴፍ ተወካይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

04/08/2026

"ተስፋን እንትከል!"
የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ የጤና ሚኒስትር ዶር መቅደስ ዳባ ያስተላለፉት መልእክት

#ተስፋንእንትከል
#አረንጓዴዐሻራ


Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6

Call for ArticlesSPECIAL BULLETIN28th ANNUAL REVIEW MEETING (ARM) OF THE HEALTH SECTOR_____________The Ministry of Healt...
04/08/2026

Call for Articles
SPECIAL BULLETIN
28th ANNUAL REVIEW MEETING (ARM) OF THE HEALTH SECTOR
_____________

The Ministry of Health (MOH) organizes the health sector's Annual Review Meeting (ARM) following the end of every Fiscal year. The event brings stakeholders together to share their best experiences, celebrate successes, plan the sector’s future, and set priorities.
Accordingly, preparations to hold the 28th ARM are underway.

The first Health Sector Medium-term Development and Investment Plan (HSDIP I) period has already concluded, and preparations are underway for HSDIP II. Hence, articles on best practices, success stories, and other aspects of HSDIP's goals, objectives, and key results are expected to be disseminated to ARM audiences and beyond.

For more information, click here https://www.moh.gov.et/Call_For_Article_28th_ARM

Call for Volunteers: High-Level International Events____As Ethiopia proudly prepares to host a series of major internati...
04/08/2026

Call for Volunteers: High-Level International Events
____

As Ethiopia proudly prepares to host a series of major international events, including CPHIA 2026, the African Union Assembly, and, ultimately, COP32, health preparedness will play a critical role in protecting delegates, participants, and the host community throughout these landmark gatherings.

Under the leadership of the Ministry of Health (MoH-E), the health sector will deliver comprehensive services through four key pillars: Pre-Hospital Services; Clinical and Medical Services; Public Health; Food Safety, Hygiene, Sanitation & Environmental Health

Volunteers play a crucial role in the successful delivery of these services. To manage this effort, a Volunteer Selection Committee has been established with clear reporting lines to the Ministry of Health. All volunteer management will comply with international standards and Ethiopia’s Voluntary Services Implementation Guideline (2021), ensuring the highest standards of accountability and coordination.

For more Information and registration, click here https://ict.moh.gov.et/en/volunteer/guests/68f628da-db93-4c37-a294-dc94e87d9f5c

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

ሕጻናት ከተወለዱ በአንድ ሰዓት ውስጥ ጡት ማጥባት ይጀምሩ፣ እንገርን ይስጡ!   Website: moh.gov.etFacebook: Ministry of Health,EthiopiaTwitter: x.co...
04/08/2026

ሕጻናት ከተወለዱ በአንድ ሰዓት ውስጥ ጡት ማጥባት ይጀምሩ፣ እንገርን ይስጡ!



Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

Address

Sudan Road (Goma Kuteba)
Addis Ababa
P.O.BOX1234

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 17:30
Sunday 08:30 - 17:30

Telephone

+251115518031

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ministry of Health,Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ministry of Health,Ethiopia:

Shortcuts

Share