የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን Ethiopian Maritime Authority -ema

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን Ethiopian Maritime Authority -ema

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን Ethiopian Maritime Authority -ema Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን Ethiopian Maritime Authority -ema, Government Organization, መስቀል አደባባይ ከማርዮት አፓርትመንትስ ጎን ሰንሻይን ህንፃ ቁጥር 4 ከ7/11 ወለል Meskel Square Next to Marriot Apartment Hotel, Sunshine building no 4, 7th/11th floor, Addis Ababa, Addis Ababa.

"የበጎ አድራጎት ተግባራት ማኅበራዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ፣ የዜጎችን በልማት ሥራዎች የመሳተፍ ባህል እያሳደጉ ነው" ክቡር አቶ ደንጌ ቦሩበባህር ዳር ከተማ ለሦስት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ...
22/08/2026

"የበጎ አድራጎት ተግባራት ማኅበራዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ፣ የዜጎችን በልማት ሥራዎች የመሳተፍ ባህል እያሳደጉ ነው" ክቡር አቶ ደንጌ ቦሩ

በባህር ዳር ከተማ ለሦስት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎች ግንባታ መሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ።

ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. (ትሎሚ) — በባህር ዳር ከተማ ለሚገኙ ወተት በር ፣ አየር ጤና እና ድል ችቦ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት መሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል።

የመሠረተ ድንጋይ ማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓቱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ደንጌ ቦሩ፣ የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ አቶ ጎሹ አንዳለማሁ ፣የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ፍራኦል ጣፋ እና ሌሎች የፌዴራል እና የአ/ብ/ክ/ መንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተከናውኗል።

የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ትብብር የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ደንጌ ቦሩ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ መሪነት ባለፉት ዓመታት የበጎ አድራጎትና የማኅበራዊ ተሳትፎ ሥራዎች እየተጠናከሩ መምጣታቸውን ገልጸዋል።

እንደ አቶ ደንጌ ገለጻ፣ እነዚህ ተግባራት የመደመርና የብልጽግና እሳቤዎች ውጤት ሲሆኑ፣ የደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የችግኝ ተከላ፣ የኢኮኖሚ ውስንነት ላለባቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እና የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የመማሪያ ክፍሎች ግንባታን ያካትታሉ።

እነዚህ የበጎ አድራጎት ተግባራት በማኅበረሰቡ ውስጥ ማኅበራዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ፣ የዜጎችን በልማት ሥራዎች የመሳተፍ ባህል እያሳደጉ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በባህር ዳር ከተማ በሦስቱ ትምህርት ቤቶች የሚከናወነው የመማሪያ ክፍሎች ግንባታ በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለተማሪዎች አገልግሎት እንዲውል አቅጣጫ ሰጥተዋል።

የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ አቶ ጎሹ አንዳለማሁ በበኩላቸው፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ ወደ ከተማዋ በመምጣት ሰብዓዊና ሀገራዊ ተልዕኳቸውን ከመወጣት ባለፈ፣ በትምህርት ዘርፍ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት መሠረተ ድንጋይ ማስቀመጣቸው የሚያስመሰግን መሆኑን ገልጸዋል።

ከንቲባው አክለውም፣ የዛሬው የመሠረተ ድንጋይ ማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት በፌዴራልና በክልል መንግሥታት መካከል ያለው ትብብርና መስተጋብር እየጠናከረ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።

የፌዴራል መንግሥት በክልሎች የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየትና ለመሙላት በሚያደርገው ጥረት የሚታየው ለውጥ ከፍተኛ መሆኑንም አቶ ጎሹ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ ፍራኦል ጣፋ በበኩላቸው፣ ባለሥልጣኑ ለነገዋ የተሻለች ኢትዮጵያ የሚበቃ ትውልድ ለመፍጠር የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍ ዕድል በማግኘቱ ደስተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ፍራኦል የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ ውስጥ በፍጥነት እንደሚጠናቀቅ ቃል ገብተዋል።

በሥነ-ሥርዓቱ ወቅት የችግኝ ተከላ የተከናወነ ሲሆን፣ በተጨማሪም ለ700 የሚጠጉ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።

በሥነ-ሥርዓቱ መጨረሻም የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ቢሮ ከፌዴራል ተቋማት ለመጡ እንግዶች ክልሉን የሚያስተዋውቅና ባህላዊ እሴቶቹን የሚያንጸባርቅ ስጦታ አዘጋጅቶ አበርክቷል። ስጦታውም የቢሮው ምክትል ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ዘውዱ ማለደ እና የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጎሹ አንዳለምሁ በኩል ለእንግዶቹ ተበርክቷል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

የኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ዘርፍ በ2018 በጀት ዓመት 17.5 ሚሊዮን ቶን ጭነት ማጓጓዙ ተገለጸየትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ደንጌ ቦሩ በኤክስ ገጻቸው ኢትዮጵያ በ2...
22/08/2026

የኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ዘርፍ በ2018 በጀት ዓመት 17.5 ሚሊዮን ቶን ጭነት ማጓጓዙ ተገለጸ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ደንጌ ቦሩ በኤክስ ገጻቸው ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት 17.57 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የገቢና ወጪ ጭነት ማጓጓዟን እና በሎጂስቲክስ ዘርፍ የታዩ ዋና ዋና የአፈጻጸም መረጃ አካፍለዋል።

በበጀት ዓመቱ 15,929,887.98 ሜትሪክ ቶን የገቢ እና 1,643,028.71 ሜትሪክ ቶን የወጪ ጭነት በመጓጓዝ በጠቅላላው 17,572,916.69 ሜትሪክ ቶን ጭነት መስተናገዱን ገልጸዋል።

የገቢ ጭነቶችን በዓይነት ሲታይ 4.23 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ፣ 9.35 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ጄኔራል ካርጎ እና 2.35 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ደረቅ ብትን ጭነት ተመዝግቧል።

ከ2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የጄኔራል ካርጎ ጭነት በ3,003,989.85 ሜትሪክ ቶን ጨምሯል፤ የነዳጅ ጭነትም በ34,416 ሜትሪክ ቶን አድጓል። በአንጻሩ የደረቅ ብትን ጭነት በ1,257,043.51 ሜትሪክ ቶን ቀንሷል።

👉ቡና በኤክስፖርት ጭነት ቀዳሚ ሆኗል፦

በ2018 በጀት ዓመት ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ የተጓጓዘው ምርት 1,643,029.29 ሜትሪክ ቶን መድረሱ ተገልጿል።

ከዚህ ውስጥ ቡና 440,089.80 ሜትሪክ ቶን በመያዝ 26.79 በመቶ ድርሻ አለው። ጥራጥሬ 311,881.24 ሜትሪክ ቶን ወይም 18.98 በመቶ፣ የቅባት እህል 234,549.94 ሜትሪክ ቶን ወይም 14.28 በመቶ እና አትክልትና ፍራፍሬ 191,597.85 ሜትሪክ ቶን ወይም 11.66 በመቶ ድርሻ አላቸው።
ትሎሚ

የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን በማጠናከር ቀልጣፋና ውጤታማ ተቋም ለመገንባት በትኩረት እየሰራን  ነው" ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜየትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የሙያ ምድብ የስራ ፍሰት የአደ...
17/08/2026

የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን በማጠናከር ቀልጣፋና ውጤታማ ተቋም ለመገንባት በትኩረት እየሰራን ነው" ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የሙያ ምድብ የስራ ፍሰት የአደረጃጀት፣ የተቋቋሙ ቴክኒካል ብቃት ማዕቀፍ ዝግጅት በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አመራር እና ባለሙያዎች ተገምግሟል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ እና የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ክቡር ዶ/ር መኩሪያ ሀይሌ በተገኙበት በቀረበው ጥናት፣ የሚኒስቴሩን የስራ አፈጻጸም፣ አደረጃጀትና የሙያ ብቃት በመገምገም የስራ ፍሰትን ለማሳለጥና የተቋሙን ውጤታማነት ለማሳደግ የሚያግዙ አቅጣጫዎች ተመላክተዋል።

በጥናቱ የበላይ አመራሩ በበላይነት መምራቱ፣ ግብረመልስን ተቀብሎ በወቅቱ ማስተካከያ ማድረጉ እና የባለሙያዎች የስራ ተነሳሽነት እንደጠንካራ ጎኖች ተለይተዋል። በአንጻሩ የዳይሬክቶሬቶች ቁጥር መብዛት እንደክፍተት ተለይቶ፣ ቁጥሩን በማመጣጠን የአደረጃጀት ቅልጥፍናን ማሳደግ እንደሚገባ ተመላክቷል።

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ሀይሌ ሚኒስቴሩ በአፈጻጸም ጥሩ ውጤት ካላቸው ተቋማት መካከል እንደሚመደብ ገልጸው፣ የዳይሬክቶሬቶች ቁጥር በመመጠን አደረጃጀቱን ይበልጥ ቀልጣፋ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በዌቭ ሁለት የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም የጋራ ምዘና  የሚኒስቴር መስሪያቤቱ ሪፎርም  አፈፃፀም የተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ።ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም  በትራንስፖር...
17/08/2026

በዌቭ ሁለት የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም የጋራ ምዘና የሚኒስቴር መስሪያቤቱ ሪፎርም አፈፃፀም የተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ።

ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና በተጠሪ ተቋማት ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፣ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት፣ ከግብርና ሚኒስቴር እና ከትምህርት ሚኒስቴር የተውጣጡ የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በሰጡት ግብረ መልስ በዌቭ ሁለት የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም የሚኒስቴር መስሪያቤቱ አፈፃፀም የተሻለ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

የሱፐርቪዥን ቴክኒክ ኮሚቴ ስብሳቢ ዶ/ር ብርሃኑ አሰፋው በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና በተጠሪ ተቋማት በዌቭ ሁለት የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ስራዎች አፈፃፀም ጋር ተያይዞ የተሰሩ ስራዎች በመልካም አፈጻጸም ላይ እንደሚገኙ ገልፀው የተከናወኑ ተግባራት ቀጣይነት እንዲኖራቸው እና ተግባራዊ እንዲሆኑ አስተያየታቸውን ስጥተዋል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ደ
ዴኤታ ክቡር አቶ ደንጌ ቦሩ እንደ ተቋም ሀገርን እና መንግስትን ሊያገለግል የሚያስችል የሪፎርም ስራ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው በኮሚቴው ሌት ከቀን የተሰሩ ስራዎችን እና የመጣውን ውጤት አስመልክተው ኮሚቴውን አመስግነዋል።

የሪፎርም ስራው ተቋማት ለብዙ ዓመታት ሊጠቀሙበት የሚያስችል በመሆኑ የሪፎርም ስራውን ከመነሻ እሰከ መዳርሻ ያለውን ሂደት እንደ መልካም አጋጣሚ ልንጠቀምበት ይገባል ያሉ ሲሆን በሱፐርቪዥን የተሰጡ አስተያየቶችን እንደ ግብአት በመውስድ ቀሪ ስራዎች በአጭር ጊዜ እንዲፈፅሙ አቅጣጫ ስጥተዋል።
ትሎሚ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት በዌቭ ሁለት የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር የሪፎርም ዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ተገመገሙነሐሴ 7/2018 ዓ.ም (ትሎሚ):- የ...
13/08/2026

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት በዌቭ ሁለት የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር የሪፎርም ዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች ተገመገሙ

ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም (ትሎሚ):- የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን፣ የመንገድ ደህንነት እና መድህን ፈንድ አገልግሎት ፣የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን በዌቭ ሁለት የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ስራዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ግምገማው ያካሄዱት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር አለሙ ሰሜ፣ የቴክኒክ ኮሚቴዎች እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት አመራሮች በጋራ በመሆን ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን፣ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት፣ ከግብርና ሚኒስቴር እና ከትምህርት ሚኒስቴር የተውጣጡ የኮሚቴ አባላት ለአንድ ዓመት ያህል ሲሰራበት የነበረውን የሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ የደረሰበት ደረጃ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ገምጋሚ ኮሚቴው ተቋሙ ያከናወናቸውን የሪፎርሙ እና የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች በተለያዩ የስራ ክፍሎችም በመዘዋወር የአካል ምልከታም አድርጓል ፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር

ብሔራዊ የማሪታይም መረጃ መለዋወጫ  ማዕከል (NMISC) ለማዘጋጀት ሲካሄድ የነበረው ወርክሾኘ ተጠናቀቀ======ሐምሌ30፣2018 ዓ.ም( ኢማባ) በኢትዮጵያ ብሔራዊ የማሪታይም መረጃ መለዋወጫ...
06/08/2026

ብሔራዊ የማሪታይም መረጃ መለዋወጫ ማዕከል (NMISC) ለማዘጋጀት ሲካሄድ የነበረው ወርክሾኘ ተጠናቀቀ
======
ሐምሌ30፣2018 ዓ.ም( ኢማባ)
በኢትዮጵያ ብሔራዊ የማሪታይም መረጃ መለዋወጫ ማዕከል (NMISC) ለማደራጀት ያለመ ወርክ ሾፕ ከሐምሌ 27/2018 እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ከዓለም አቀፉ የማሪታይም ተቋም (IMO) ጋር በመተባበር መድረኩን ያዘጋጀ ሲሆን በመድረኩ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የመድረኩ ዋና ዓላማ በቀይ ባህር እና በምዕራባዊ ህንድ ውቅያኖስ አካባቢ የሚከሰቱ እንቅስቃሴዎችን በተቀናጀ መልኩ መረጃ ለመለዋወጥ እንዲያስቻል መሆኑ ተገልጿል። በወርክ ሾፑ ላይ የማሪታይም ሴክዩሪቲ እና በዘርፉ የሚያጋጥሙ ቀውሶችን በተቀናጀ እና በተናበበ መልኩ እንዴት መረጃ መለዋወጥና ችግሮቹን መፍታት ይቻላል በሚለው ዙርያ ከዓለም አቀፉ የማሪታይም ተቋም የመጡ ሙያተኞች አማካኝነት ስልጠናዎች ተሰጥጣል። ይህንን መረጃ ለመለዋወጥ ኢትዮጵያ የብሔራዊ የማሪታይም መረጃ መለዋወጫ ማዕከል(NMISC) እንዴት ታቋቁም እና እንዴትስ ማስተዳደር ይገባታል የሚሉት ከአለም አቀፍ ተሞክሮዎች አንጻር ውይይት ተደርጎበታል።
አቶ ፍራኦል ጣፋ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር ዓለም አቀፉ የማሪታይም ድርጅት (IMO) ኢትዮጵያ ለሚታደርገው የማሪታይም ዘርፍ የአቅም ግንባታ ስራዎች ለሚያደርገው ድጋፍ አመስግነው ፤ ኢትዮጵያ የንግድ መርከቦች ያላት ቢቻ ሳትሆን በቀጠናው በማሪታይም ደህንነት ላይ የሚፈጠሩ ስጋቶችን ለመከላከል የተቀናጀ የማሪታይም መረጃ መለዋወጫ ማዕከል እንደሚያስፈልጋት ገልጸው፣ ባለስልጣን መ/ቤቱ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የመረጃ መለዋወጫ ማዕከሉ በተሟላ ሁኔታ እንዲደራጅ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው ፡፡ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ምየኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎትበኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ...
06/08/2026

መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው ፡፡

ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።

እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።

በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡

በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።

በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።

በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤

በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።

በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።

በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።

መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን አመራር እና ሰራተኞች በአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ========ሐምሌ 27፣2018 ዓ.ም (ኢማባ) የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣንአመራ...
03/08/2026

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን አመራር እና ሰራተኞች በአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
========
ሐምሌ 27፣2018 ዓ.ም (ኢማባ) የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣንአመራር እና ሰራተኞች በአገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው በአንድ ጀንበር 800ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሃ ግብር ላይ በምስራቅ ሽዋ ጤዴቻ ገበሬ ማህበር እና በሞጆ ግሪን ሎጂስቲክስ ሃብ የራሳቸውን አሻራ አኑረዋል።

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ፍራኦል ጣፋ ኢትዮጵያ ለስምንተኛ ጊዜ እያከናወነች ያለችው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአየር ንብረት ለውጥ የራሱ የሆነ አስተዋፆ እንዳለው እና ከዛ በተጨማሪ ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ጉልህ ድርሻ እንደሚጫወት ገልፀዋል።

አቶ ፍራኦል አያይዘውም ባለሥልጣኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ዙሮች ችግኞችን ሲተክል መትከል ብቻ በራሱ ግብ እንዳልሆነ በማመን የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ የተሻለ የመፅደቅ ምጣኔ ማስመዝገብ መቻሉን እና ዛሬም የሚተከሉ ችግኞች እንክብካቤ እንደሚደረግላቸው ገልፀዋል።

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአገር አቀፍ ደረጃ በሚል መሪ ሃሳብ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን የተቋሙ አመራር እና ሰራተኞችም የራሳቸውን አሻራ አኑረዋል።

ታሪክ ለመስራት ሰዓታት ብቻ ቀረው!የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር - የችግኝ ተከላ መርሃግብር #ተስፋንእንትከል  #አረንጓዴዐሻር
02/08/2026

ታሪክ ለመስራት ሰዓታት ብቻ ቀረው!

የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር - የችግኝ ተከላ መርሃግብር
#ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር

አንድ ቀን ብቻ ቀረው!የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር  #ተስፋንእንትከል  #አረንጓዴዐሻር
02/08/2026

አንድ ቀን ብቻ ቀረው!
የ2018 የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር
#ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር

Address

መስቀል አደባባይ ከማርዮት አፓርትመንትስ ጎን ሰንሻይን ህንፃ ቁጥር 4 ከ7/11 ወለል Meskel Square Next To Marriot Apartment Hotel, Sunshine Building No 4, 7th/11th Floor, Addis Ababa
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 08:00 - 17:00
Sunday 08:00 - 17:00

Telephone

+251911312772

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን Ethiopian Maritime Authority -ema posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን Ethiopian Maritime Authority -ema:

Shortcuts

Share