Ethiopian Roads Administration

Ethiopian Roads Administration Government Organization

የመንገድ ፈንድ በ2018 በጀት ዓመት 28 ቢሊዮን ብር ሰበሰበ፤ በ2019 በጀት ዓመት ደግሞ ከ32 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ አቀደቢሾፍቱ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓም(ኢመአ): የኢትዮጵያ መ...
05/09/2026

የመንገድ ፈንድ በ2018 በጀት ዓመት 28 ቢሊዮን ብር ሰበሰበ፤ በ2019 በጀት ዓመት ደግሞ ከ32 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ አቀደ

ቢሾፍቱ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓም(ኢመአ): የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመንገድ ፈንድ የጥገና በጀት ድጋፍ ከሚደረግላቸው የሁሉም ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች የመንገድ ኤጀንሲ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ሲያካሂድ የቆየውን የምክክር ውይይት አጠናቀቀ። በውይይት መድረኩ የመንገድ ፈንድ የ2018 በጀት ዓመት ገቢ አፈጻጸም 28 ቢሊዮን ብር መሆኑ ተገለጿል፤ በ2019 በጀት ዓመት ደግሞ ከ32 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዷል።

የፈንዱ ገቢ ምንጮች በነዳጅ ላይ ከሚጣል ታሪፍ፣ ከቅባትና ዘይት ታሪፎች፣ የሀገሪቱን ድንበር አቋርጠው ከሚገቡ ተሽከርካሪዎች ክፍያ፣ ከአመታዊ ክብደትን መሰረት ካደረገ ዓመታዊ የፈቃድ ማደሻ እንዲሁም ከክብደት ወሰን በላይ ጭነት ቅጣቶች የሚገኘውን ገቢ ናቸው።

በመንገድ ፈንድ የሚደገፉ 72 ኤጀንሲዎች ከአመታዊ ዕቅድ ዝግጅት እስከ ክፍያ አፈጻጸም ድረስ ባሉት ሂደቶች ላይ በቴክኒክ፣ በኦዲትና በአማካሪዎች አማካኝነት የቅርብ ክትትል ይደረግባቸዋል። በተጨማሪም ኤጀንሲዎቹ በአማካሪዎቹ ስራው በትክክል መሰራቱን አረጋግጠው በሚልኳቸው የምስክር ወረቀቶች (ሰርተፍኬቶች) ላይ ተመስርቶ ክፊያ ይፈጸማል፣ ቁጥጥርም ይደረጋል።

የመንገድ ኤጀንሲዎቹ አጠቃላይ አፈጻጸም ከዕቅድ በላይ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት እያጋጠሙ ያሉ የበጀት ፍላጎትና አቅርቦት አለመጣጣም፣ የግብዓት ዋጋ መጨመር፣ አንዳንድ አካባቢ የሚስተዋለው የጸጥታ ሁኔታና መሰል ችግሮች በሥራዎቻቸው ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳደረዋል። በተላይ የጥገና በጀት ማነስ፣ የነባር ግንባታ ማሽነሪዎች ዕድሳት መዘግየት እና የአዳዲስ ማሽነሪዎች ግዢ አለመፈጸም አፋጠኝ መፍትሄ የሚፈልጉ መሆናቸው ተጠቁሟል። ችግሮቹን በዘላቂነት ለመፍታትም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው ተመላክቷል።

በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ጽሕፈት ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል መንግሥቴ ባስተላለፉት መልእክት፤ ከመንገድ ፈንድ የሚመደበውን በጀት በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋልና አስፈላጊውን ክትትል ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። አያይዘውም የፋይናንስና የሥራ አፈጻጸም ሰነዶች የሚረጋገጡበት ጠንካራ ሥርዓት መዘርጋትና ተፈጻሚ ማድረግ፣ እንዲሁም ለሕብረተሰቡ የተሳለጠ የመንገድ ተደራሽነትን ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከክልልና የከተማ መስተዳድር ኤጀንሲዎች ጋር ዓመታዊ የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነውቢሾፍቱ ፣ ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. (ኢመአ)— የኢትዮጵያ መን...
04/09/2026

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከክልልና የከተማ መስተዳድር ኤጀንሲዎች ጋር ዓመታዊ የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው

ቢሾፍቱ ፣ ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. (ኢመአ)— የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በመንገድ ፈንድ የጥገና በጀት ድጋፍ ከሚደረግላቸው የሁሉም ክልሎች እና የዋና ከተማ መስተዳድሮች የመንገድ ኤጀንሲዎች የሥራ ኃላፊዎች ጋር የሚያካሂደው ዓመታዊ የዕቅድ አፈጻጸም የውይይት መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ እየተተካሄደ ነው።

የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን እንደገለጹት፤ የመድረኩ ዋና ዓላማ የሥራ አፈጻጸሞችን በበጎ ጎን ማየት ብቻ ሳይሆን በሥራ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ የአሠራር ክፍተቶችን በግልጽ በመወያየት ቀጣይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ነው። በመድረኩ ያለፈው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም በዝርዝር የሚገመገም ሲሆን፣ አዳዲስ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት ይደረግበታል።

ዋና ዳይሬክተሩ የመንገድ ግንባታና ልማት በአገሪቱ ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጣቸው የመሠረተ ልማት ዘርፎች ቀዳሚው እና የልማት ጉዞውን ለማፋጠን የሚያገለግል ቁልፍ ምሰሶ መሆኑን ገልጸዋል። በመንግሥት ልዩ ትኩረት ምክንያት ዛሬ ላይ ደረጃቸውን የጠበቁ የመንገድ መዋቅሮች በከፍተኛ ሁኔታ መስፋፋታቸውንና አሁንም በስፋት እየተገነቡ መሆናቸውን አብራርተዋል። መንገድ የተራራቁ ሕዝቦችን በማገናኘት፣ ለአርሶ አደሮች ምርት ገበያ፣ ለትምህርትና ለጤና ተደራሽነት፣ ለኢንቨስትመንት እንዲሁም ለቱሪዝም ዕድገት ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም አክለዋል።

ይሁን እንጂ የተገነቡ መንገዶች በዲዛይናቸው መሠረት የረጅም ዘመን አገልግሎት እንዲሰጡ ወቅታዊ ጥገና ሊደረግላቸው እንደሚገባ ኢንጂነር መሀመድ አሳስበዋል። መሠረተ ልማቱ ለብልሽት ከተጋለጠ ለተሽከርካሪ መለዋወጫ የሚወጣውን የውጭ ምንዛሬ በማናር በሀገር ሀብት ላይ ከፍተኛ ጫና ስለሚፈጥር፣ ቀጣይነት ያለው የጥገና ሥራና ቋሚ የፋይናንስ ድጋፍ ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ይህን የፋይናንስ ፍላጎት በዘላቂነት ለመመለስ መንገድ ፈንድ ከ28 ዓመታት በፊት ራሱን ችሎ መቋቋሙን ያስታወሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ተቋሙ ከነዳጅ፣ ከቅባትና ዘይት ታሪፎች፣ የሀገሪቱን ድንበር አቋርጠው ከሚገቡ ተሽከርካሪዎች ክፍያ፣ ከፈቃድ ማደሻና ከክብደት ወሰን በላይ ጭነት ቅጣት ገቢዎችን በመሰብሰብ ዓላማውን በስኬት እያሳካ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ከ2014 በጀት ዓመት ጀምሮ መንገድ ፈንድ በአዋጅ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሥር መደራጀቱ ደግሞ ለሥራ ቅልጥፍና ትልቅ ዕድል መፍጠሩ ተብራርቷል።

በ2019 በጀት ዓመት ከመንገድ ፈንድ የገቢ ምንጮች የሚሰበሰበውን ገቢ በመገመት ለፌደራል፣ ለክልል እና ለከተማ መንገድ ኤጀንሲዎች ለመደበኛና ለወቅታዊ ጥገና፣ ለከባድ (መልሶ) ጥገና፣ ለመንገድ ደኅንነት እንዲሁም የኤጀንሲዎችን አቅም ለመገንባት የሚያስፈልጉ መሣሪያዎች ግዢ የሚውል በጀት መደልደሉም በዚሁ መድረክ ተገልጿል።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/

በ2018 በጀት ዓመት የ580 ኪሎ ሜትር አዳዲስ መንገዶች ግንባታ መከናወኑ ተገለጠ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት የ580 ኪሎ ሜትር አዳዲስ መ...
01/09/2026

በ2018 በጀት ዓመት የ580 ኪሎ ሜትር አዳዲስ መንገዶች ግንባታ መከናወኑ ተገለጠ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት የ580 ኪሎ ሜትር አዳዲስ መንገዶች ግንባታ እና 12 ሺህ 882 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የተለያዩ የመንገድ ጥገና ሥራዎች መከናወናቸው ተገለጸ። ተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድን አስመልክቶ በዓለምገና ኢንጅነሪንግ እና ማኔጅመንት ማሠልጠኛ ማዕከል ከአመራሮችና ከሠራተኞች ጋር አጠቃላይ ዓመታዊ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በተቋሙ ፕላንግና ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት በቀረበው ሪፖርት መሠረት፤ በበጀት ዓመቱ የ238 ኪሎ ሜትር የነባር መንገዶች ደረጃ ማሻሻል እንዲሁም የ16 ኪሎ ሜትር የነባር መንገዶች ማጠናከር ሥራዎች በስኬት ተከናውነዋል። ተቋሙ በበጀት ዓመቱ የምህንድስና ግዢ፣ የዲዛይን ፕሮጀክቶች እንዲሁም የተቋማዊ አቅም ግንባታ ተግባራትን ማከናወኑ ተገልጿል።

በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ 24 የመንገድ ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት የሆኑ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል የኢተያ - አርሲ ሮቤ፣ የእስቴ - ስማዳ፣ የድሬዳዋ ባይፓስና ሽንሌ፣ የጅግጅጋ ከተማ ማለፊያ (ባይፓስ) መንገድ እንዲሁም የሳውላ - ቃቆ መንገድ ፕሮጀክቶች በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው። ተቋሙ በተያዘው አዲስ በጀት ዓመት ከ1 ሺህ 67 ኪሎ ሜትር በላይ አዳዲስ መንገዶችን ለመገንባት እና ከ16 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍኑ የተለያዩ መንገዶችን ለመጠገን አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱ ተመላክቷል።

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢንጅነር) በወቅቱ ባስተላለፉት መልእክት፤ የ2018 በጀት ዓመት ተቋሙ የተመሠረተበትን 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ያከበረበት ልዩ የታሪክ ምዕራፍ መሆኑን አስታውሰዋል። ተቋሙ ባለፉት 75 ዓመታት ሰፊ የመንገድ መሠረተ-ልማት አውታሮችን በመዘርጋት ኢትዮጵያን እርስ በርስ ማስተሳሰር የቻለና ለአገሪቱ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የማይተካ የበኩሉን አስተዋጽኦ ያበረከተ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ በ2019 በጀት ዓመት በመንገድ ዘርፉ የተጣሉትን አገራዊ ግቦች በውጤታማነት ለማሳካት የተጀመረው ተቋማዊ ሪፎርም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የአሠራር ሽግግሮችንና የዲጂታላይዜሽን በአግባቡ ከመተግበር ጎን ለጎን የሥራ ባህልንና የበጀት አጠቃቀምን በተጠያቂነትና በግልጽነት መንፈስ መምራት እንደሚገባ በጥብቅ አሳስበዋል፡፡

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/

የጎንጂ-ቆለላ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት 98.82 በመቶ አፈጻጸም ላይ ደረሰአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ)፤ በጎንጂ ቆለላ ወረዳ የሚገነባው የቆሬ - አዲስ ዓለም የአስ...
31/08/2026

የጎንጂ-ቆለላ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት 98.82 በመቶ አፈጻጸም ላይ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (ኢመአ)፤ በጎንጂ ቆለላ ወረዳ የሚገነባው የቆሬ - አዲስ ዓለም የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት የ10.59 ኪሎ ሜትር ግንባታን በማጠናቀቅ 98.82 በመቶ አጠቃላይ አፈጻጸም ላይ ደርሷል። ከባህር ዳር ወደ ሞጣ በሚወስደው መንገድ ላይ ከምትገኘው ቆሬ ቀበሌ ተነስቶ ምስራቅ አቅጣጫ በመጓዝ ሂዳሴ መንደርን አቋርጦ አዲስ ዓለም ከተማ የሚገባው ይህ ፕሮጀክት፣ በአጠቃላይ 10.74 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው። ቀድሞ የነበረውን የጠጠር መንገድ ወደ አስፋልት ደረጃ የሚያሳድገው ይህ ግንባታ፣ የመንገዱ ስፋት በገጠር 10 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በወረዳ 21.5 ሜትር ሆኖ እየተገነባ ይገኛል።

ግንባታው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን በአካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ አዲስ ተስፋ ይዞ ይመጣል። በተለይም አርሶ አደሩ በአካባቢው በስፋት የሚያመርታቸውን እንደ ጤፍ፣ ሰሊጥ፣ በርበሬና ማሽላ ያሉ የግብርና ምርቶችን ያለምንም እንግልት በወቅቱ ወደ ገበያ ለማቅረብና የቱሪዝም መዳረሻዎችን በቀላሉ ለማገናኘት ጉልህ ሚና ይኖረዋል። ከዚህም በላይ ነዋሪዎች ቀድሞ ለመጓጓዝ ይወስድባቸው የነበረውን የጉዞ ጊዜ በአንድ ሰዓት ያህል በማሳጠር የዕለት ተዕለት ህይወታቸውን ያቀልላቸዋል።

ይህ ታላቅ ተስፋ የተሰነቀበት ፕሮጀክት ግንባታው እስከአሁን ድረስ ያጋጠሙና በሥራው ፍጥነት ላይ ጫና ያሳደሩ እንደ የጸጥታ፣ እና የወሰን ማስከበር ችግሮች እንዲሁም የነዳጅ እጥረት ተግዳሮቶችን ቀርፎ አሁን ያለበት ደረጃ ደርሷል። ሥራው እንዳይቋረጥ ከተለያዩ የመንግስት አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት፣ ለግንባታው የሚሆን ነዳጅ በቅድሚያ እንዲያገኝ በማድረግና ከፍተኛ ክትትል በማድረግ የተከለሰው የፕሮጀክቱ ማጠናቀቂያ ቀን በጥቅምት ወር 2019 ዓ.ም እንዲሆን ተደርጓል።

የበጀት ፍሰቱን በተመለከተ ቫትን ጨምሮ ከ333 ሚሊዮን ብር በላይ የተመደበለት ሲሆን፣ የስራ ተቋራጭነቱን ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ሲያከናውነው የሃይዌይ ኢንጂነርስ ኤንድ ኮንሰልታንትስ ኃ/ተ/ግ/ማ ደግሞ የአማካሪነት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል። ተቋራጩ አፈጻጸሙን እንዲያሻሽልና ቀሪ ሥራዎችን በተያዘው የበጀት ዓመት እንዲያጠናቅቅም በየደረጃው ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገለት ነው።

በአሁኑ ወቅት የጠረጋ፣ የአፈር ቆረጣና ሙላት፣ የሰብ ቤዝ፣ የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም ሙሉ የ10.74 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራዎች 100 በመቶ ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። በተጨማሪም የፍሳሽ ማስወገጃ (ድሬኔጅ) ሥራው 98.58 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን፤ እንደ እግረኛ መንገድና የመንገድ ምልክቶች ያሉ ቀሪ ሥራዎችንም 50 በመቶ በማድረስ ፕሮጀክቱን ሙሉ በሙሉ ወደ ማጠናቀቂያው ምዕራፍ ለማሸጋገር የመጨረሻ ደረጃ ሥራዎች በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/

9ኛው የመንገድ ጥናትና ሥርፀት ኮንፈረንስ ተካሄደአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም(ኢመአ): የመንገድ ልማትና አስተዳደር ሥራዎችን በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ ለማገዝ የተዘጋጀው 9ኛ...
28/08/2026

9ኛው የመንገድ ጥናትና ሥርፀት ኮንፈረንስ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም(ኢመአ): የመንገድ ልማትና አስተዳደር ሥራዎችን በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ ለማገዝ የተዘጋጀው 9ኛው የመንገድ ጥናትና ሥርፀት ኮንፈረንስ ተካሂዷል።

በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን፣ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሂሩት ዮሐንስ እና የቀድሞው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛይድ ወልደገብርኤልን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ተገኝተዋል።

ባለፉት ስምንት ዓመታት የተካሄዱት ተከታታይ የምርምር ኮንፈረንሶች በሀገሪቱ የመንገድ ልማት ላይ ውጤታማ ለውጦችን ማምጣት ችለዋል። በአሁኑ 9ኛ ኮንፈረንስም በርካታ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን፣ ተያያዥ አውደርዕይም ተካሂዷል። በጥናቶቹ በሌሎች አገራትና ፕሮጀክቶች ላይ ተተግብረው ውጤታማ የሆኑ የመንገድ ግንባታና አስተዳደር ልምዶች የተዳሰሱ ሲሆን፣ እነዚህ ተሞክሮዎች ለሀገሪቱ የመሠረተ ልማት ዕድገት አዳዲስ ዕድሎችን ይዘው ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በተለይም በአሁኑ ወቅት በዘርፉ ላይ ፈተና እየሆኑ ያሉትን እንደ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ እና የመንገድ መሸራተት (ናዳ) ያሉ ዋና ዋና ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራዊ የመፍትሔ ሐሳቦች በኮንፈረንሱ ላይ በስፋት ተመክሮባቸዋል። ከተቀመጡት የመፍትሔ አቅጣጫዎች መካከልም ዘላቂነትን ለማረጋገጥ በሲሚንቶ ኮንክሪት በሚሠሩ መንገዶች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሠራ በጥናት ተመልክቷል።

በመድረኩ የተሳተፉ ባለሙያዎች በኮንፈረንሱ ያገኟቸውን አዳዲስ ዕውቀቶች፣ ቴክኖሎጂዎችና ፈጠራዎች በመጠቀም በመንገድ ግንባታ፣ ዲዛይን፣ ጥገና እና አስተዳደር ሥራዎች ላይ የላቀ ሙያዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ተብሎ ይታመናል።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/

የጣርማበር - መለያያ ሰፌድ ሜዳ የጠጠር መንገድ ጥገና እየተካሄደለት ነውአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21/2018 (ኢመአ)፦ ከጣርማበር መለያያ እስከ ሰፌድ ሜዳ ለሚዘልቀው የጠጠር መንገድ ጥገና እየ...
27/08/2026

የጣርማበር - መለያያ ሰፌድ ሜዳ የጠጠር መንገድ ጥገና እየተካሄደለት ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21/2018 (ኢመአ)፦ ከጣርማበር መለያያ እስከ ሰፌድ ሜዳ ለሚዘልቀው የጠጠር መንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። ጥገናው የሕዝቡን የትራንስፖርት ችግር ለማቃለል ታስቦ በትኩረት እየተከናወነ ያለ ሥራ ነው።

ይህ አጠቃላይ 118 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የመንገድ ፕሮጀክት፣ ከዚህ ቀደም በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ አማካኝነት ግንባታው ሲካሄድ የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሳይጠናቀቅ ተስተጓጉሎ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት ግን ለትራንስፖርት እጅግ አስቸጋሪ በሆነው 21.6 ኪሎ ሜትር የመንገዱ ክፍል ላይ ሰፊ የጥገና ሥራ እየተሠራ ይገኛል።

እስካሁንም በማሽን የቦይ ማጽዳት፣ የድንጋይ ሙሌት፣ በጭቃ የተበላሹ አካባቢዎችን የማስወገድ እንዲሁም በግሬደር የመንገዱን አካል የማስተካከልና የማጠናከር ሥራዎች ተከናውነዋል። የጥገና ሥራውን የኢመአ የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ ኃይል እያከናወነው ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ደግሞ የዓለምገና መንገድ ኔትወርክ ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ቢሮ በበላይነት እየተከታተለው ነው።

የዚህ መንገድ መጠገን ማኅበረሰቡን ለእንግልትና ለትራንስፖርት መጉላላት ከዳረጉ ችግሮች የሚያላቅቅ ሲሆን፣ የትራፊክ አደጋን ከመቀነስና ጊዜን ከመቆጠብ ባሻገር የግብርና ምርቶችንና የተለያዩ ግብዓቶችን ወደ ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።

በቀጣይም ከዚህ ቀደም ይስተዋሉ የነበሩ ማነቆዎችን በመቅረፍ ሙሉ የግንባታ ሒደቱን በቀጣዩ በጀት ዓመት ለማቀላጠፍ በትኩረት እየተሠራ ነው።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/

መልካም በዓል!
25/08/2026

መልካም በዓል!

የሶዶ መንገድ አውታር አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት  1,890 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጥገና አከናወነ፤ አፈጻጸሙም 96.3% ሆኖ ተመዝግቧልሶዶ፣ ነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ.ም(ኢመአ): በኢት...
24/08/2026

የሶዶ መንገድ አውታር አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት 1,890 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጥገና አከናወነ፤ አፈጻጸሙም 96.3% ሆኖ ተመዝግቧል

ሶዶ፣ ነሐሴ 18 ቀን 2016 ዓ.ም(ኢመአ): በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ስር የሚገኘው የሶዶ መንገድ አውታር አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት ያቀዳቸውን የፊዚካልና የፋይናንሻል የሥራ ግቦች በስኬት አጠናቀቀ። ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 1.81 ቢሊዮን ብር በጀት መድቦ የነበረ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.56 ቢሊዮን ብሩን (86.18%) ለተለያዩ የጥገናና መሰረተ ልማት ሥራዎች ማዋል ችሏል።

በፊዚካል አፈጻጸም ረገድም ከተቀመጠው 1,963 ኪሎ ሜትር የጥገና ዕቅድ ውስጥ 1,890 ኪሎ ሜትር በማጠናቀቅ 96.3% አፈጻጸም አስመዝግቧል።

ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ 3,242.5 ኪሎ ሜትር የመንገድ ሽፋን ያስተዳድረል፡፡ ከዚህም ውስጥ 68 በመቶው (2,196.5 ኪ.ሜ) የአስፋልት ኮንክሪት ሽፋን ሲሆን ቀሪው 32 በመቶው (1,046 ኪ.ሜ) በጠጠር የተሸፈነ መንገድ ነው። በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና የጥገና ሥራዎች ዝርዝር አፈጻጸም እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

መደበኛ ጥገና፡ በበጀት ዓመቱ በከፍተኛ ትኩረት የተከናወነ ሲሆን በፋይናንሻል በኩል ከተመደበው 920.46 ሚሊዮን ብር በላይ 983.30 ሚሊዮን ብር (106.83%) ወጪ ተደርጎበታል። በፊዚካል በኩልም 1,731.02 ኪ.ሜ መንገድ በመጠገን የ98.33% አፈጻጸም ታይቷል።

ወቅታዊ ጥገና፡ በቅርንጫፉ የራስ ኃይልና በግል ተቋራጮች በጋራ የተከናወነ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 445.41 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ 157.57 ኪሎ ሜትር መንገድ ወቅታዊ ጥገና ተደርጎለታል።

ከባድ ጥገና፡ 1.20 ኪሎ ሜትር መንገድ የተጠገነ ሲሆን 67.03 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል።

የድልድይ መልሶ ግንባታ፡ ከተመደበው 3.23 ሚሊዮን ብር በጀት 100% ሙሉ በሙሉ ጥቅም ላይ በመዋል ተጠናቋል።

የደህንነትና የመሬት ናዳ መከላከል፡ ለድንገተኛ አደጋዎችና ለመሬት ናዳ መከላከያ ሥራዎች ከ44 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገ ሲሆን፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ከአደጋ ስጋት ነጻ እንዲሆን አስችሏል።

ጽሕፈት ቤቱ በበጀት ዓመቱ የተለያዩ የግብዓት እጥረቶች ቢያጋጥሙትም፣ የኪራይ መሣሪያዎችን በመጠቀምና የውስጥ አቅምን (የራስ ኃይልን) በማጠናከር ችግሮቹን መፍታት ተችሏል። ለ2019 በጀት ዓመትም በበጀት ዓመቱ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን (የቡድን ሥራ፣ የሠራተኞች መዝናኛና የሕፃናት ማቆያ ግንባታዎችን ማጠናቀቅን ጨምሮ) እንደ ግብዓት በመውሰድ ለዋና ዋና መንገዶች (Trunk Roads) ልዩ ትኩረት በመስጠት ለመስራት ታቅዷል።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/

Address

Ras Abebe Aregay Street
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 12:30
13:30 - 18:30
Tuesday 08:30 - 12:30
13:30 - 18:30
Wednesday 08:30 - 12:30
13:30 - 18:30
Thursday 08:30 - 12:30
13:30 - 18:30
Friday 08:30 - 12:30
13:30 - 18:30

Telephone

+251115517170

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Roads Administration posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Roads Administration:

Shortcuts

Share