10/09/2018
የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር 8ኛዉ የጋራ ጉባኤ ተካሄደ
የደቡብ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር የ2010 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2011 በጀት ዓመት ዕቅድ ከህዝብ ክንፍ፣ ባለድርሻ አካላትና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ ነሐሴ 29 እና 30/2010 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር ከተሰጠዉ ተግባርና ኃላፊነት ሴክተሩ ለሀገራችን ልማት መፋጠንና ለህዝባችን ተጠቃሚነት የሚያበረክተዉ ድርሻ ዘርፈ ብዙ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የኢንዱስትሪ ዘላቂ ሠላም ማስፈን፣የዜጎን ፍትሃዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የስራ ስምሪት ማስፋፋትና የህገ-ወጥ የሰዎች ዝዉዉር የሚገታበትና ዜጎች በሀገራቸዉ ሰርተዉ የሚለወጡበት ተግብራትን ሴክተራችን ከተሰጠዉ ተልዕኮ አንጻር በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በ8ኛዉ የጋራ ጉባኤ የተለያዩ ባለድረሻ አካላት መልዕክት ያስተላለፉበትና የሴክተሩን ተልዕኮ ከምን ጊዜዉም በላይ በብቃት የሚወጡበት የተጀመረዉ ሀገራዊ የለዉጥ ንቅናቄ መደመር፣ፍቅርና ይቅርታን ከግብ ለማድረስ ለዜጎቻችን ጠንክረን የምንሰራበትና ዕርስ በዕርስ የመደጋገፍ ባህላችንን የምናጎለብትበት እንደሆነም ቃል በመግባትና የጋራ አቋም በማዉጣት ተጠናቋል፡፡