ALSA SNNPR LABOR AND SOCIAL AFFAIRS

የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር 8ኛዉ የጋራ ጉባኤ ተካሄደ የደቡብ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር የ2010 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2011 በጀት ዓመት ዕቅድ ከህዝብ ክንፍ...
10/09/2018

የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር 8ኛዉ የጋራ ጉባኤ ተካሄደ
የደቡብ ክልል ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር የ2010 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2011 በጀት ዓመት ዕቅድ ከህዝብ ክንፍ፣ ባለድርሻ አካላትና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ ነሐሴ 29 እና 30/2010 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር ከተሰጠዉ ተግባርና ኃላፊነት ሴክተሩ ለሀገራችን ልማት መፋጠንና ለህዝባችን ተጠቃሚነት የሚያበረክተዉ ድርሻ ዘርፈ ብዙ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የኢንዱስትሪ ዘላቂ ሠላም ማስፈን፣የዜጎን ፍትሃዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የስራ ስምሪት ማስፋፋትና የህገ-ወጥ የሰዎች ዝዉዉር የሚገታበትና ዜጎች በሀገራቸዉ ሰርተዉ የሚለወጡበት ተግብራትን ሴክተራችን ከተሰጠዉ ተልዕኮ አንጻር በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በ8ኛዉ የጋራ ጉባኤ የተለያዩ ባለድረሻ አካላት መልዕክት ያስተላለፉበትና የሴክተሩን ተልዕኮ ከምን ጊዜዉም በላይ በብቃት የሚወጡበት የተጀመረዉ ሀገራዊ የለዉጥ ንቅናቄ መደመር፣ፍቅርና ይቅርታን ከግብ ለማድረስ ለዜጎቻችን ጠንክረን የምንሰራበትና ዕርስ በዕርስ የመደጋገፍ ባህላችንን የምናጎለብትበት እንደሆነም ቃል በመግባትና የጋራ አቋም በማዉጣት ተጠናቋል፡፡



10/09/2018

የማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ ጥምረት የአሰራርና አፈፃፀም ማኑዋል ትዉዉቅ ተደረገ
የክልሉ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ኤጀንሲ ከሚመለከታዉ ከባልድርሻ አካላት፣ ከህዝብ ክንፍና አጋር ድርጅቶች ጋር የማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ ጥምረት የአሰራርና አፈፃፀም ማኑዋል በ22/12/2010 ዓ.ም በይርጋለም ከተማ ፉራ የመሰብስቢያ አዳራሽ ትዉዉቅ ተደረገ፡፡ ቀደም ሲል የማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ አሰራርና አደረጃጀትን ለመወሰን የወጣዉ የደንብ ቁጥር 161/2010 ዓ.ም መሠረት የአሠራርና የአፈጻጸም ማኑዋል አስፈላጊ በመሆኑ በማህበራዊና ኢኮኖሚ ችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎች አስፈላጊዉን እገዛ እንዲያገኙ ታስቦ ሲሆን ማህበራዊ ጉዳዮች የሚባሉት ግለሰቦች፣በርካታ የማህበረሰብ አባላትንና ማህበረሰቡን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚነሱና በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ በማህበረብ ውስጥ የሚከናወኑ ጉዳዮች ናቸዉ፡፡ ማህበራዊ ጉዳዮች ከማህበራዊ ችግሮችም ጋር የሚያገናኙ ሆነዉ በማህበረሰቡ ዉስጥ በድህንትና በሌሎች ምክንያቶች ለችግር የተጋለጡት፣ወላጅ አሳዳጊ አጥተዉ አስቸጋሪ ሁኔታ ዉስጥ የሚገኙ የህጻናትን፣ አካል ጉዳተኞችን፣አረጋዉያንን፣በህፃናት፣በደሃ ሴቶች የሚተዳደሩ ቤተሰብ አባላትን የተገለሉ የህበረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል ሲሆን እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች መስራት የሚችሉ ሆነዉ ዕድል ያልተመቻቸላቸዉ፣እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች በህመም፣በዕድሜ መግፋትንና በመሳሰሉት በስራ ለመስራት የማይችሉ ሆነዉ ለማህበራዊ ችግሮች ተጋላጭ በመሆናቸዉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸዉን ለማቃለል እንዲቻል ከሚከናወኑ ስራዎች አንዱ የማህበራዊ ጥበቃ መርሃ-ግብር መሆኑ ተገልጿል፡፡

10/09/2018
17/08/2018

በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ ሰመጎ ሥር የአርባምንጭ ተሀድሶ ማዕከል አገልግሎት
ማዕከሉ በሁለት ዘርፎች የተዋቀረ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን አንደኛዉ አካላዊ ተሃድሶ /ሲቢአር/ ናቸዉ እነዚህ ተግባራት ተመጋጋቢ በሆነ መልኩ ማህበረሰብን በማሳተፉ ተቋማዊ የአካላዊ ተሀድሶ አገልግሎቶችን ለአካል ጉዳተኞች ማህበረሰብ በማድረስ የሚሰራበት ነው፡፡ ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት አገልግሎቶች በተጨማሪ ለአካል ጉዳተኛ ማህበረሰብ ዘርፈ ብዙ የተቋማት አገልግሎት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥና የኔትወርኪንግ እና ፓርትሽንና ተግባራት ለተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር ይከናወናሉ፡፡
የአካላዊ ተሃድሶ አገልግሎቶች
የአካላዊ ተሃድሶ የአገልግሎት ዘረፍ የሰዉ ሰራሽ አካል፣ የአካል ድጋፍ ምርት እና ስርጭት እንዲሁም የፌዚዮትራፒ አገልግሎቶች በቅብብሎሽ የሚከናወኑ አገልግሎቶችን ያካተተ ነዉ፡፡
አገልግሎቱ የሚሰጠዉ በማዕከሉ ዋና መስሪያ ቤት በሚገኙ የኦርቶፔዲክ እና የፌዜዮትራፒ ወርክሾፖች ውስጥ ሲሆን በዋና መስሪያ ቤት ለሚሰጠዉ አገልግሎት የመስክ አሰሳ እና ምልመላ አካላዊ የተሃድሶ አገልግሎት በሚያቀርቡ የስራ ክፍሎች አንደኛዉ የሰዉ ሰራሽ አካልና የአካል ድጋፍ (Orthopedic Workshop) የስራ ሂደት ሲሆን የእንቅስቃሴ ችግር ላለባቸዉ አካል ጉዳተኞች አገልግሎት ይስጣል፡፡
በስራ ሂደቱ የሚሰሩ ተግባራት በሙያዉ በሰለጠኑ ባለሙያዎች የሚመራ ሲሆን በአካል ላይ የተለያዩ ጉዳት ለደረሰባቸዉ የሰዉ ሰራሽ አካል (Prosthesis) እና የአካል ደጋፍ (Orthosis) የሚደረግበት ስራዓት ነው፡፡
በአርባምንጭ ተሃድሶ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጥባቸዉ የአካል ጉዳት ዓይነቶች እንድሚከተለዉ ናቸዉ
- የአጅ፣የአግር መቆረጥ ጉዳት ያለባቸዉ በሁሉም የዕድሜ ክልል የሚገኙ አካል ጉዳተኞች
- ዕድሜያቸዉ ከአራት ዓመት በታች የሆኑና የእግራቸዉ መረገጫ ከዉልድት ጀመሮ የተቆለመመባቸዉ ህጻናት (Club Foot)
- ክራንች የሚያስፈልጋቸዉ አካል ጉዳተኞችና በሽተኞች የልጅነት ልምሻ ጉዳት የደረሰባቸዉ አካል ጉዳተኞች
- የፌዚዮትራፒ .
- አገልግሎት ፈላጊዎች
- የተሽከርካሪ (Wheel Chair) ተጠቃሚዎች ናቸዉ

16/08/2018

የደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግስትየሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር መልእክት
የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ኤጀንሲ ከተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት የለውጥ ሰራዊትን በመገንባትና በማሰማራት በመንግስት የተሰጠውን ተልዕኮ በመፈፀም የተገልጋይ እርካታን ማረጋገጥ ሲሆን ቁልፍ ተግባራትን ለመፈፀምና ተቋማዊ ለውጥን ለማረጋገጥ ሲባል በርካታ የተግባር እንቅስቃሴዎች ሲደረጉ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ አንፃር በመስፋፋት ላይ የሚገኙ ኢንዱስትሪዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የስራ ቦታዎች ለሥራ ምቹ እንዲሆኑና የስራ ላይ አደጋና በሽታ እንዳይከሰት የመከላከል የሙያ ጤንነትና ደህንነት በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫና የቁጥጥር ሥራዎች የማከናወን፣ሴክተሩን በሚመለከት የወጡ ፖሊሲዎች፣ አዋጆች ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም ሀገራችን የተቀበለቻቸው አለም ዓቀፍ ኮንቬንሽኖችና ስምምነቶችን ተግባራዊ በማድረግ ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናቶችና ምርምሮችን በማካሄድ የረጅም፣ የመካከለኛና አጭር ጊዜ ዕቅዶችን በመንደፍ ለአሰሪዎችና ለሰራተኞች በአጠቃላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን በማከናወን የኢንዱስትሪ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
በክልላችን በተፈጠረው ምቹ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ አኳያ እየተስፋፋ ባለው የግሉ ዘርፍ እንዲሁም መንግስት በተለያዩ ዘርፎች በሚያካሂዳቸው መጠነ ሰፊ የልማት ስራዎች ለበርካታ ዜጎች ሰፊ ጊዜያዊና ቋሚ የስራ እድሎች እንዲፈጠርላቸው ኤጀንሲው የስራ ገበያ አደራጅቶ በመያዝ ሥራና ሰራተኛን በማገናኘት የስራ አጥነት ችግሮችን በመቅረፍ ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ አኳያ ለወቅታዊ የግብርና ልማት ስራዎች በክልላችንና ከክልላችን ውጭ ወደሚገኙ የልማት ድርጅቶች የሚሄዱትን ሰራተኞች በማስተባበር የልማት ድርጅቶችን የሰው ሀይል ፍላጎት ማሟላትና የቤተሰብ ጥሪት የመገንባት ስራዎችን ማገዝ ህገመንግስታችን የሰጠውን የመደራጀት መብት ተጠቅመው የተደራጁ የአሰሪም ሆነ የሰራተኛ ማህበራትን አግባብነት ባላቸው ህጎች ዙሪያ ግንዛቤ በማስጨበጥና በማጠናከር ለእንዱስትሪ ሰላም መስፈን እንዲሁም ለምርትና ምርታማነት መጎልበት የበኩላቸውን እንዲወጡ ማድረግ ትኩረት ሰጥቶ የሚተገብራቸው ስራ ናቸው፡፡
በክልላችንም ሆነ በአገራችን ማህበረዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ከመሆን አልፎ በሀገር ገጽታ ላይ አሉታዊ ጥላ እያሳረፈ የሚገኘውን ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ለመከላከል ወጣቱ በሀገር ውስጥ ባሉና በተመቻቹ የስራ ዕድሎች እንዲጠቀም እንዲሁም ሕብረተሰቡ ስለ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ግንዛቤ ማስጨበጥና ህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎችን ወደ ህግ ፊት እንዲቀርቡ ከማድረግ አንፃር ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር ሰፊ ስራዎችን ይሰራል፡፡ በተጨማሪም የህፃናትን ጉልበት ብዝበዛና የህፃናት ህገ-ወጥ ዝውውር ከመከላከል አኳያ ኤጀንሲው ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን ተግቶ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡
በማህበራዊ ጥበቃ ዘርፍ በማህበራዊ ችግሮች ውስጥ የሚገኙትና ለማህበራዊ ኑሮ ጠንቆች ተጋላጭ የሆኑት የህብረተሰብ ክፍሎች ማለትም አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን፣ ሴተኛ አዳሪዎች፣ ወላጅና አሳዳጊ ያጡ ህፃናትና ሌሎች ከድህነት ወለል በታች ያሉና ማህበራዊ መገለል የሚደርስባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ችግሮቻቸው የሚቀረፈው በማህበረሰብ አቀፍ አደረጃጀትና አሰራር መሆኑን በመገንዘብ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ስልት ቀይሶ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ሴክተሩ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት በሚያደርገው ቀጣይ ጥረት ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጥ እያሳየ መምጣቱ እሙን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሀገራችን ለምታራምደው የሰላም፣ የልማትና ዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መፋጠን ሁነኛ ድርሻ እያበረከተ መገኘቱን ለማየት የሚያስችል ነው፡፡ በዚህ መሠረት የለውጥ ሰራዊት ግንባታ ለሴክተሩ ተልዕኮ መሳካት ወሳኝ ድርሻ የሚያበረክት አቅም ስለሆነ በግባታው ሂደት ጠንካራ ቁመና ያለው የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር የልማት ሰራዊት በመገንባት ሴክተሩ በሚሰጠው ዘርፈ ብዙ አገልግሎት ተደራሽ፣ ፍታሃዊና የህዝብን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ ተፈፃሚ በማድረግ መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና በተያዘው ንቅናቄ ውስጥ እምርታ የማሳያት ጥረት ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ALSA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ALSA:

Share