03/06/2026
የሐዘን መግለጫ
_______________
በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በምርምርና ስልጠና ዘርፍ ላለፉት አስር ዓመታት በተመራማሪነት ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ ቶሎሳ ታዬ ሁንዴሳ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. በደረሰባቸው ድንገተኛ አደጋ በተወለዱ በ33 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ማነጅመንት እና ሠራተኞች በአቶ ቶሎሳ ታዬ ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማንን ጥልቅ ኃዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን!!