Ethiopian Sugar Industry Group

Ethiopian Sugar Industry Group Established as public enterprise by the Public enterprise proclamation No. 500/2022.
(1)

Established as public enterprise by the Public enterprise proclamation No. 25/1992.

ግሩፑ 227 ኩንታል ስንዴ ድጋፍ አደረገ__________________________የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለአገራዊ "ተረጂነትን የማስቀረት" ጥሪ 227 ኩንታል ስንዴ ድጋፍ በማድረግ...
03/09/2026

ግሩፑ 227 ኩንታል ስንዴ ድጋፍ አደረገ
__________________________
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለአገራዊ "ተረጂነትን የማስቀረት" ጥሪ 227 ኩንታል ስንዴ ድጋፍ በማድረግ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ከውጭ ዕርዳታ ጥገኝነት ለመላቀቅና ድጋፍ የሚሹ ዜጎችን ከአገር ውስጥ ሀብት በማሰባሰብ ድጋፍ ለማድረግ እንዲሁም በቀጣይነት ተረጂነትን ለማስቀረት ታስቦ በተጀመረው መርሐ ግብር ግሩፑ ሁለት ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የገዛውን የ227 ኩንታል ስንዴ ድጋፍ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ክቡር አቶ ወዮ ሮባ ለልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሥራ አስፈጻሚ አስረክበዋል፡፡
ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር የመንግስት የልማት ድርጅቶች ከልማት ሥራዎቻቸው ጎን ለጎን ማሕበራዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት አንዱ ተግባራቸው መሆኑን ገልጸው ግሩፑም ባለፉት ዓመታት በወረዳው በማዕድ ማጋራት፣ የአቅመ ደካሞችን መኖሪያ ቤት በማደስና ለትምህርት ቤቶች አስፈላጊ ግብአቶችን በማሟላት ይህንን ኃላፊነቱን ሲወጣ ቆይቷል ብለዋል፡፡
የስኳር ፋብሪካዎች በሚገኙባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ ማሕበረሰቦችም ከትምህርት ቤት ግንባታ እስከ ቁሳቁስ ማሟላት፣ መሠረተ ልማትና ማሕበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ግንባታ በማከናወን እና በኤችአይቪ ኤድስ ወላጆቻቸውን ያጡ ሕጻናትን እስከ ከፍተኛ ትምህርት ድረስ ተንከባክቦ በማስተማር ማሕበራዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ላይ እንደሚኝም ክቡር አቶ ወዮ አስገንዝበዋል፡፡
የመንግስት አቅጣጫ የአገር ውስጥ አቅምን በማዳበር ችግሮች ሲከሰቱም ሆነ በቋሚነት ድጋፍ የሚሹ ዜጎችን መደገፍ መሆኑን ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመው በዚህ ዓመት የውጭ እርዳታ ጥገኝነትን ለማስቀረት ታስቦ በተጀመረው መርሐ ግብር ላይ ግሩፑ በመሳተፉ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አብደላ በበኩላቸው ግሩፑ ያደረገው የ227 ኩንታል የስንዴ ድጋፍ ከተደረጉ ድጋፎች ከፍተኛውና የመጀመሪያው መሆኑን አስታውቀው ለዚሁም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ግሩፑ ያደገረገው የስንዴ ድጋፍ በየወሩ እገዛ ለሚደረግላቸው አቅመ ደካማ ዜጎች እንደሚውል የወረዳው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገልጸው የግሩፑ የተጠናከረ ድጋፍ በቀጣይም እንደማይለያቸው እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡

በአምባሳደር ግርማ ብሩ ሰብሳቢነት የሚመራው የግሩፑ የሥራ አመራር ቦርድ የዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታን ጎበኘ__________________________________በክቡር አምባሳደር ግርማ...
02/09/2026

በአምባሳደር ግርማ ብሩ ሰብሳቢነት የሚመራው የግሩፑ የሥራ አመራር ቦርድ የዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታን ጎበኘ
__________________________________
በክቡር አምባሳደር ግርማ ብሩ የሚመራው የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሥራ አመራር ቦርድ የግሩፑን የወደፊት የዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ የግንባታ ሂደትን ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጎብኝቷል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት የህንጻ ግንባታው ኮንትራክተር የቲኤንቲ ኮንትራክሽንና የአማካሪው ድርጅት ባለሙያዎች የግንባታውን ሂደት በተመለከተ ለሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢው አምባሳደር ግርማ ብሩና ለአባላቱ ገለጻ አድርገዋል፡፡
ባለሙያዎቹ በገለጻቸው የሕንጻው የመዋቅር ሥራ 90 በመቶ የአጠቃላይ ግንባታው ሥራ ደግሞ 70 በመቶ መድረሱን ጠቅሰው 27ኛ ወለል ላይ ከደረሰው የመዋቅር ሥራው ጎን ለጎን የማጠናቀቂያ ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡
ለሕንጻው ማጠናቀቂያ የሚውሉ የኤሌክትሮሜካኒካል ግብአቶች በሙሉ በሙሉ ከውጭ አገር መግባታቸውንና ግብአቶቹን ለመግጠም ዝግጅቶች በመደረግ ላይ መሆናቸውንም ባለሙያዎቹ አስረድተዋል፡፡
በጉብኝቱ የግሩፑ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ዋና አማካሪ አምባሳደር ግርማ ብሩ የግሩፑ ዋና መስሪያ ቤት ሕንጻ ግንባታ በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑን ጠቁመው ግንባታውን በተያዘለት ጊዜ አጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ርብርብ እንዲደረግ አሳስበዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይ ከሥራ አመራር ቦርድ አባላት በተጨማሪ የግሩፑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ወዮ ሮባና የማነጅመንት አባላት ተሳትፈዋል፡፡

To: All BiddersSubject: Bid Extension – Tender No. LP/OT/01/SIG/2018/19With reference to the above-mentioned tender for ...
27/08/2026

To: All Bidders
Subject: Bid Extension – Tender No. LP/OT/01/SIG/2018/19
With reference to the above-mentioned tender for the Procurement of Consultancy Services for the Design of Bridges, Cross Drainage Structures, and a 3,000-Hectare Pumped Surface Irrigation System at Omo Kuraz No. 2 Sugar Factory, some prospective bidders have requested an extension of the bid closing and opening date.
In order to provide sufficient time for prospective bidders to prepare and submit their bids, the bid closing and opening date is hereby extended from August 27, 2026, to September 9, 2026.
All other terms and conditions of the bidding document shall remain unchanged.
With best regards,

CC
 Procurement & Property Management Department
 Project Management Department
 Public Relation and Participation Department
Sugar Industry Group

26/08/2026
የግሩፑ ዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች የግምገማና የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ ተጠናቀቀ______________________________የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና መስሪያ ቤት ሠራተ...
23/08/2026

የግሩፑ ዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች የግምገማና የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ ተጠናቀቀ
______________________________
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ ተጠናቋል፡፡
የግሩፑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ወዮ ሮባ በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ባደረጉት ንግግር የግሩፑ ሠራተኞቸ ሥራቸውን እሴት በሚጨምርና ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማከናወ እንዲሁም በበጀት ዓመቱ የተመዘገበውን የተሻለ አፈጻጸም አጠናክሮ ማስቀጠልን ታሳቢ ተደርጎ ለሁለት ቀናት የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና ውጤታማ እንደነበር ገልጸዋል፡፡
የተለያዩ ግብዓቶችንና ማሺነሪዎችን አቀናጅቶ ወደውጤት የሚቀይረውና ተቋምን ውጤታማ ለማድረግ የሰው ኃይል አቅም መገንባት ወሳኝ መሆኑ ሌላው የዓቅም ግንባታ ስልጠናውን አስፈላጊ አድርጓል ብለዋል ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው በማጠቃለያቸው፡፡
ሠራተኛው በተመደበበት የሥራ መደብ ላይ ኃላፊ መሆኑን በመገንዘብ ሥራዎችን በኃላፊነትና በጊዜ የለኝም መንፈስ የድርሻውን መወጣት እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል፡፡
እያንዳንዱ ሠራተኛ ከፈጻሚነት አልፎ በተቋሙ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴዎች ላይ አስተዋጽኦ ለማበርከት ጥረት ማድረግ ተገቢ መሆኑንም ክቡር አቶ ወዮ ሮባ ጠቁመዋል፡፡
ሁሉም ሠራተኛ የተቋሙ ባለቤት መሆኑን በመረዳት የስኳር ፋብሪካዎችን ወደሙሉ አቅም ለማድረስ እና ከዚህ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ላይ የድርሻውን መወጣት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡
አሁን ያለው የሠራተኛው ተነሳሽነት ግለቱን በጠበቀ መልኩ እንዲቀጥል በማሳሰብ ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው መድረኩን አጠቃልለዋል፡፡

የበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም በግልና በጋራ ውጤታማ እንቅስቃሴ የተመዘገበ ነው ተባለ______________________________________የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በ2018 ...
22/08/2026

የበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም በግልና በጋራ ውጤታማ እንቅስቃሴ የተመዘገበ ነው ተባለ
______________________________________
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በ2018 በጀት ዓመት ላስመዘገበው የተሻለ አፈጻጸም የዋና መስሪያ ቤት እና የፋብሪካዎች ሠራተኞች እንዲሁም የሥራ መሪዎች በጋራ ባደረጉት ውጤታማ እንቅስቃሴ የተመዘገበ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የግሩፑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ወዮ ሮባ የግሩፑ ዋና መስሪያ ቤት ሠራተኛች የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክን በንግግር ሲከፍቱ እንደገለጹት በስኳር ዘርፍ ሁሉም መመዘኛዎች በ2018 በጀት ዓመት ለተመዘገቡ የተሻሉ ውጤቶች የዋና መስሪያ ቤትና የፋብሪካዎች ሠራተኞች እንዲሁም የሥራ መሪዎች በግልና በጋራ ባደረጉት ያላሰለሰ ጥረትና ትጋት የተገኙ ናቸው ብለዋል፡፡
በተገባደደው በጀት ዓመት በዋና ዋና ሥራዎች ማለትም በስኳር ምርት፣ በተጓዳኝ ልማት፣ በመሬት ዝግጅትና በአገዳ ተከላ እንዲሁም ለፋብሪካዎች በተሰጡ የተለያዩ ድጋፎች እና የምርቶች ሽያጭን ጨምሮ በፋይናንስ አሠራርና በኦዲት ክንውኖች ረገድ የተከናወኑና የተገኙ ውጤቶች ከጊዜ ወደጊዜ መሻሻል አሳይተዋል ብለዋል ዋና ሥራ አስፈጻሚው፡፡
ከጊዜ ወደጊዜ የተሻሉ ለውጦች መመዝገባቸው ይበል የሚያሰኙ ቢሆንም መሬትን ጨምሮ በእጃችን የሚገኙ የልማት አቅሞችን አሟጠን በመጠቀም ስኳር ፋብሪካዎች በሙሉ አቅማቸው እንዲሰሩ ለማስቻል ከፍተኛ ጥረት በቀጣይ ማድረግ እንደሚጠበቅም ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው በንግግራቸው ጠቅሰዋል፡፡
ግሩፑ ከራሱ አልፎ ለአገር ምጣኔ ሀብት እድገት በማበርከት ላይ የሚገኘውን የጎላ አስተዋጽዖ የበለጠ አጠናክሮ ለማስቀጠል በሁሉም መስክ የላቀ ቅልጥፍናና ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባም ዋና ሥራ አስፈጻሚው በንግግራቸው ጠቅሰዋል፡፡
የዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በበጀት ዓመቱ ያስመዘገቡትን የተሻለ አፈጻጸም በ2019 በጀት ዓመት በላቀ ሁኔታ እንዴት መድገም እንደሚችሉ በቡድን ተከፋፍለው ውይይት ከማድረጋቸውም በላይ ላጋጠሟቸው ተግዳሮቶች መፍትሔዎችን ጠቁመዋል፡፡
በመድረኩ ላይ በኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን የእርሻ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዴንት፣ የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ መሠረታዊ የሠራተኞች ማህበር ሊቀመንበርና የሥራ አመራር ቦርድ አባል አቶ ጋዲሳ ደሳለኝ፣ የግሩፑ ከፍተኛ የማነጅመንት አባላት፣ የስኳር ፋብሪካዎች ሥራ አስኪያጆች፣ የግሩፑ መካከለኛ የሥራ መሪዎች እና የዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

የአቅም ግንባታ ስልጠናው ውጤታማ ነበር______________________________ለኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና መስሪያ ቤት እና ለኦሞ ኩራዝ ስኳር እንዲሁም ለአርጆ ዲዴሳ ፋብሪ...
21/08/2026

የአቅም ግንባታ ስልጠናው ውጤታማ ነበር
______________________________
ለኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና መስሪያ ቤት እና ለኦሞ ኩራዝ ስኳር እንዲሁም ለአርጆ ዲዴሳ ፋብሪካዎች የሥራ መሪዎች ለሁለት ቀናት የተሰጠው የዓቅም ግንባታ ስልጠና ውጤታማ እንደነበር ተገለጸ፡፡
የዋና መስሪያ ቤትና የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች የሥራ መሪዎች ሥራዎቻቸውን ጊዜውን በዋጀ መልኩ ለመምራትና በበጀት ዓመቱ የተመዘገበውን የተሻለ አፈጻጸም አጠናክሮ ማስቀጠልን ታሳቢ ተደርጎ ለሁለት ቀናት የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና ውጤታማ እንደነበር ነው የግሩፑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ወዮ ሮባ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ባደረጉት ንግግር የገለጹት፡፡
የስልጠናው ርዕሰ ጉዳዮች የሥራ መሪዎቹን ከአዳዲስ ሀሳቦችና አሠራሮች ጋር ከማስተዋወቅ ባለፈ ሁሉም የግሩፑ የሥራ መሪዎች የበለጠ እርስ በርስ እንዲቀራረቡና ልምድ እንዲለዋወጡ ዕድል የፈጠረ እንደነበርም ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለዋል፡፡
የዋና መስሪያ ቤትና የፋብሪካዎቹ መካከለኛ የሥራ መሪዎች ተቋሙን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመለወጥ የሚያስችል የባለቤትነት ስሜት እና አስተሳሰብ መያዛቸው መዳበርና መጎልበት ያለበት አዎንታዊ ለውጥ መሆኑንም ነው ዋና ሥራ አስፈጻሚው በንግግራቸው የጠቆሙት፡፡
በተለይ የስኳር ፋብሪካዎች የሥራ መሪዎች ከስልጠናው ባገኙት ሃሳቦችና የተለወጡ አሰራሮች በመታገዝ በየፋብሪካዎቻቸው የሸንኮራ አገዳ ሽፋን ለማስፋፋት በትጋት መስራት የሚጠበቅባቸው ዋንኛ ተግባር መሆኑንም ክቡር አቶ ወዮ ሮባ አሳስበዋል፡፡
በዚሁ የስልጠና ማጠናቀቂያ ውይይት ላይ የፋብሪካዎች የ2019 በጀት ዓመት መነሻ ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የአቅም ግንባታ ስልጠናው ውጤታማ ነበር______________________________ለኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና መስሪያ ቤት እና ለኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች የሥራ መሪዎች ለሁ...
21/08/2026

የአቅም ግንባታ ስልጠናው ውጤታማ ነበር
______________________________

ለኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና መስሪያ ቤት እና ለኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች የሥራ መሪዎች ለሁለት ቀናት የተሰጠው የዓቅም ግንባታ ስልጠና ውጤታማ እንደነበር ተገለጸ፡፡
የዋና መስሪያ ቤትና የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች የሥራ መሪዎች ሥራዎቻቸውን ጊዜውን በዋጀ መልኩ ለመምራትና በበጀት ዓመቱ የተመዘገበውን የተሻለ አፈጻጸም አጠናክሮ ማስቀጠልን ታሳቢ ተደርጎ ለሁለት ቀናት የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና ውጤታማ እንደነበር ነው የግሩፑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ወዮ ሮባ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ባደረጉት ንግግር የገለጹት፡፡
የስልጠናው ርዕሰ ጉዳዮች የሥራ መሪዎቹን ከአዳዲስ ሀሳቦችና አሠራሮች ጋር ከማስተዋወቅ ባለፈ ሁሉም የግሩፑ የሥራ መሪዎች የበለጠ እርስ በርስ እንዲቀራረቡና ልምድ እንዲለዋወጡ ዕድል የፈጠረ እንደነበርም ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለዋል፡፡
የዋና መስሪያ ቤትና የፋብሪካዎቹ መካከለኛ የሥራ መሪዎች ተቋሙን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመለወጥ የሚያስችል የባለቤትነት ስሜት እና አስተሳሰብ መያዛቸው መዳበርና መጎልበት ያለበት አዎንታዊ ለውጥ መሆኑንም ነው ዋና ሥራ አስፈጻሚው በንግግራቸው የጠቆሙት፡፡
በተለይ የስኳር ፋብሪካዎች የሥራ መሪዎች ከስልጠናው ባገኙት ሃሳቦችና የተለወጡ አሰራሮች በመታገዝ በየፋብሪካዎቻቸው የሸንኮራ አገዳ ሽፋን ለማስፋፋት በትጋት መስራት የሚጠበቅባቸው ዋንኛ ተግባር መሆኑንም ክቡር አቶ ወዮ ሮባ አሳስበዋል፡፡
በዚሁ የስልጠና ማጠናቀቂያ ውይይት ላይ የፋብሪካዎች የ2019 በጀት ዓመት መነሻ ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የግሩፑ የሥራ መሪዎች የዓቅም ግንባታ ስልጠና ተጀመረ___________________________የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የዋና መስሪያ ቤትና የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች የሥራ መሪ...
20/08/2026

የግሩፑ የሥራ መሪዎች የዓቅም ግንባታ ስልጠና ተጀመረ
___________________________
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የዋና መስሪያ ቤትና የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች የሥራ መሪዎች የዓቅም ግንባታ ስልጠና ተጀመረ፡፡
ነሐሴ 14 ቀን 2018ዓ.ም የተጀመረው የዓቅም ግንባታ ስልጠና የግሩፑ የሥራ መሪዎች ሥራዎቻቸውን ውጤታማና ጊዜውን በዋጀ መልኩ ለመምራትና በበጀት ዓመቱ የተመዘገበውን ውጤታማ አፈጻጸም አጠናክሮ ማስቀጠል እንዲቻል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ ወዮ ሮባ ስልጠናውን ባስጀመሩበት ወቅት ገልጸዋል፡፡
ባለፉት ሁለት ቀናት የግሩፑ የሥራ መሪዎች ራሳቸውን በጥልቀት መገምገማቸውንና ትኩረት ተሰጥቷቸውና በዕቅድ ውስጥ ተካትተው ሊፈቱ የሚገቡ ጉዳዮችን መለየታቸውን ያስታወሱት ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው የዓቅም ግንባታ ስልጠናው ለእነዚህ ለተለዩ ጉዳዮች መፍትሔ ለማበጀት ዓቅም የሚፈጥር መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ውጤታማ ተቋም መገንባትና የመፈጸም ዓቅም ማጎልበት፣ የዕቅድ ዝግጅት፣ ድጋፍ፣ ክትትልና ሪፖርት እና ውጤታማ የሀብት አጠቃቀም እንዲሁም Leadership in a Technology Driven World በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡
በርዕሶቹ ላይ ገለጻ ከተደረገ በኋላ የሥራ መሪዎች በቡድን ሰፊ ውይይቶችን በማድረግ እንደሚያዳብሯቸው ታውቋል፡፡

ለፋብሪካዎች የሚደረገው ድጋፍ መሻሻል ማሳየቱ ተገለጸ______________________________________________________የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለስኳር ፋብሪካዎች...
19/08/2026

ለፋብሪካዎች የሚደረገው ድጋፍ መሻሻል ማሳየቱ ተገለጸ
______________________________________________________
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ለስኳር ፋብሪካዎች የሚያደርገው ድጋፍ በዓይነት፣ በመጠን እና በጥራት እንዲሁም በወቅታዊነት ጭምር መሻሻል እያሳየ መምጣቱ ተገለጸ፡፡
የግሩፑ የሥራ መሪዎች የአፈጻጸም ግምገማ ነሐሴ 13 ቀን 2018ዓ.ም በተጀመረበት ወቅት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ክቡር አቶ ወዮ ሮባ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለጹት ስኳር ፋብሪካዎችን በመደገፍ ረገድ የታየው የእስካሁኑ የተሻለ አፈፃፀም በቀጣይ በጥራትና በቅልጥፍና ፋብሪካዎችን የመደገፍ እምቅ አቅምና ብቃት ያለ መሆኑን የሚያመለክት ነው፡፡
የግሩፑ የመጨረሻ ውጤት የሚታየው ስኳር ፋብሪካዎች በሚያመርቱት ምርት መጠንና ጥራት መሆኑን ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመው የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካዎች በበጀት ዓመቱ በስኳር ምርት፣ በአገዳ ተከላና በተጓዳኝ ምርቶች ላስመዘገቡት የተሻለ አፈፃፀም የዋና መስሪያ ቤት የሥራ መሪዎች ወቅታዊ፣ የተቀናጀና ጥራት ያለው ድጋፍ ወሳኝ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡
የግሩፑ ሠራተኛው ተጠቃሚ ሆኖ ለአገርና ለህዝብ ጠቃሚ ነገር ለመስራት በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ውጤታማ የሥራ አፈፃፀሞችን በቀጣይ በማሻሻል እና ፋብሪካዎች አቅማቸውን የሚመጥን ምርት የማምረት ደረጃ ላይ ማድረስ ሲቻል መሆኑን ክቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚው አስታውሰው የሥራ መሪዎቹ በዓመታዊ ግምገማቸው የተገኙ ውጤታማ አፈጻጸሞችን የበለጠ አጠናክሮ ማስቀጠል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
በዓመታዊ የሥራ አፈፃፀም ግምገማ የሥራ መሪዎች ያላቸውን እምቅ አቅም አውጥተው መጠቀም የሚያስችላቸውን ዕድል እንዲያገኙ የሚያስችል ከመሆኑም በላይ ዘርፍ ከዘርፍ፣ መምሪያ ከመምሪያ እንዲሁም ቡድን ከቡድን ይበልጥ ተቀናጅቶ መሥራት የሚችሉባቸውን ምቹ ሁኔታዎች የሚፈጥር በመሆኑ በንቃት መሳተፍ ይገባል ብለዋል፡፡
የሥራ መሪዎቹ በቡድን ተከፋፍለው በተዘጋጁ የመወያያ ነጥቦች ላይ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡

Address

Mexico Square, Philips Building
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Sugar Industry Group posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Sugar Industry Group:

Shortcuts

Share