ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን-Kolfe Woreda 05 Communication

ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን-Kolfe Woreda 05 Communication አዳዲስና ወቅታዊ መረጃዎች እንዲደርስዎት የኮልፌ ወረዳ 05 ኮሚዩኒኬሽን ማህበራዊ ገጾችን ይቀላቀሉ....

https://linktr.ee/Kolfeworeda05Communication

በወረዳው አስተዳደር  መጪው  አዲስ አመት በዓልን  አስመልክቶ ኢግዚብሽንና ባዛር ግብይይት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው፡፡ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን ነሐሴ  30 /2018 ዓ.ምመጪው አዲስ አመ...
05/09/2026

በወረዳው አስተዳደር መጪው አዲስ አመት በዓልን አስመልክቶ ኢግዚብሽንና ባዛር ግብይይት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው፡፡

ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን
ነሐሴ 30 /2018 ዓ.ም

መጪው አዲስ አመት በዓልን አስመልክቶ በወረዳ 05 አስተዳደር በዘነበወርቅ አደባባይ ኤግዚቢሽንና ባዛር ግብይይት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው ።

በባዛሩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳኛቸው ሹመት የተዘጋጁ ኤግዚብሽንና ባዛሮች በዋናነት ነዋሪዎች በአቅራቢያቸው ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሆነና የወረዳው ነዋሪ በአቅራቢያው በተዘጋጁ ኤግዚብሽንና ባዛሮች ላይ በመገኘት ግብይት እንዲጠንይከር ጥሪ አቅርበዋል።

እስከ በአሉ ድረስም ምርቶች በስፋት እንደሚቀርቡ የገለፁት አቶ ዳኛቸው ለኤግዚብሽኑና ባዛሩ አስፈላጊ ዝግጅት ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

አቶ አሰፋ አዱኛ የወረዳው ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅህፈት ቤት ሀላፊ በበኩላቸው አዲስ አመትን በማስመልከት የወረዳ አስተዳደር በባዛሮች፣ በገበያ ማእከላትና በ2 የቅዳሜና እሁድ ገቢያዎች ምርቶችን በስፋትና በጥራት ማቅረቡን ገልፀዋል።

ሀላፊው አክለው ህብረተሰቡ በአልን በደስታ እንዲያሳልፍ እና የኑሮ ውድነት ለማረጋጋት ባዛሩ ጠቀሜታ እንዳለው ገልፀው በዓሉን ምክንያት በማድረግ የኢንዱስትሪ፣ የግብርና፣ እንዲሁም የእንስሳት ተዋፅኦ መቅረቡን አስታውቀዋል።

በወረዳው በዘነበወርቅ አደባባይ በተከፈተው ኤግዚብሽን እና ባዛር በወረዳው የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ፣ ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት፣ አርሶ አደሮች እንዲሁም የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የሚሰሩ ነጋዴዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

በሁለቱ የገበያ ማእከላት ኤግዝብሽኑ የባህል አልባሳት፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ ማርና የማር ውጤቶች፣ የኢንደስትሪ ምርቶች ፣ የግብርና ምርቶች፣ የእንስሳት ተዋጽኦዎች፣አትክልትና ፍራፍሬዎችን ጨምሮ ሌሎች ለበአል የሚውሉ የተለያዩ ምርቶች የቀረቡ ሲሆን እስከ ጳጉሜ 05/2018 ድረስም የሚቆይ ነው።

በክፍለ ከተማው አስተዳደር በወረዳ 05 አዲስ አመት በዓልን  አስመልክቶ  የተዘጋጀው ባዛር ነዋሪዎች በአቅራቢያቸው ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሆነ ተገለፀ።ኮልፌ ወረዳ...
04/09/2026

በክፍለ ከተማው አስተዳደር በወረዳ 05 አዲስ አመት በዓልን አስመልክቶ የተዘጋጀው ባዛር ነዋሪዎች በአቅራቢያቸው ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሆነ ተገለፀ።

ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን ነሐሴ 29 /2018 ዓ.ም

በክፍለ ከተማው ወረዳ 05 አስተዳደር መጪው አዲስ አመት በዓልን አስመልክቶ በትላንትናው እለት በአየር ጤና አደባባይ የተከፈተው ኤግዚቢሽንና ባዛር ነዋሪዎች በአቅራቢያቸው ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሆነ በባዛሩ ላይ የተለያዩ ምርቶችን ያቀረቡ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።

በወረዳ 05 በአየር ጤና አደባባይ በተከፈተው ኤግዚብሽን እና ባዛር በክፍለ ከተማው የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ኢንተርፕራይዞች ፣ ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት፣ አርሶ አደሮች እንዲሁም የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የሚሰሩ ነጋዴዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

የባዛሩ ተሳታፊዎች እንዳሉት አዲስ አመትን አስመልክቶ ጥራትና ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውን የተለያዩ ምርቶችን ማቅረባቸውን ተናግረዋል።

በኤግዝብሽኑ የባህል አልባሳት፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ ማርና የማር ውጤቶች፣ የኢንደስትሪ ምርቶች ፣ የግብርና ምርቶች፣ የእንስሳት ተዋጽኦዎች፣አትክልትና ፍራፍሬዎችን ጨምሮ ሌሎች ለበአል የሚውሉ የተለያዩ ምርቶችን መቅረቡንም አብራርተዋል።

ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ ከተማ አዲስ አበባ- የዓለም አቀፍ ሽልማቶች ሚስጥርአዲስ አበባ ያሸነፈቻቸው የዓለም አቀፍ ሽልማት ዋነኛ ሚስጥር የሚገኘው ከመሠረተ ልማትና ውጤታማ  ስራዎች ብቻ ሳይ...
04/09/2026

ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ ከተማ አዲስ አበባ- የዓለም አቀፍ ሽልማቶች ሚስጥር

አዲስ አበባ ያሸነፈቻቸው የዓለም አቀፍ ሽልማት ዋነኛ ሚስጥር የሚገኘው ከመሠረተ ልማትና ውጤታማ ስራዎች ብቻ ሳይሆን፣ ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ ከተማ ለማድረግ አጠቃላይ የሁለንተናዊ ብልፅግና ጉዞ ማዕከል በሆነው የሰብዓዊ ልማት እና ትውልድን በማነጽ ላይ በሰራችው ስር ነቀል ለውጥ ጭምር ነው።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ “የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም”ን በብቃት በመምራታቸው በዓለም አቀፉ “አክት ፎር ኤርሊ ይርስ” (Act For Early Years) ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት ዕድገት ሻምፒዮን” ተብለው ተሸልመዋል። ይህ ትልቅ እውቅና ከተማዋን ለህፃናት የምትመች ከተማ እና ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ የአፍሪካ መዲና ለማድረግ የሰነቀችውን ራዕይ የሚያንፀባርቅ፣ እንዲሁም ለትውልድ ግንባታ የሚደረገው ኢንቨስትመንት ያመጣውን ለውጥ በጉልህ የሚያሳይ ነው።

የዚህ ስኬት እና የከተማዋ አስደናቂ እድገት ማሳያ የሆነው ከቁጥር በላይ የሆነው መረጃ የመጫወቻ ስፍራዎች እና የሕፃናት ማቆያዎች መስፋፋት ነው። 20 የመጫወቻ ስፍራዎች ብቻ የተነሳው የከተማዋ አስተዳደር በሦስት ዓመታት ውስጥ ብቻ 5 ሺህ 500 ማድረስ ችሏል። በሌላ በኩል 5 ሺህ 3 የሚሆኑት የልጆችን የዕድገት ደረጃና ሥርዓት ታሳቢ ያደረጉ የመጫወቻ ቦታዎችም ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። በተጨማሪም የሕዝብ የሕፃናት ማቆያዎች ከ11 ብቻ ተነስተው በአሁኑ ሰዓት 1 ሺህ 100 ደርሰዋል። ይህ በተለያዩ ሞዴሎች የተደራጀው የማቆያ ቁጥር በጥቅሉ 1 ሺህ 155 የደረሰ ሲሆን፣ 27 ሺህ 302 ሕፃናት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል።

ይህ ስኬታማ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም በመዲናችን የሚገኙ 1.3 ሚሊዮን ገደማ ሕፃናትን፣ በተለይም 330 ሺህ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ታዳጊዎች ተደራሽ ለማድረግ ያለሙ አምስት አንኳር ጉዳዮችን ያካተተ ነው።

አዲስ አበባ ዛሬ አለምን ያስገረመችው እና የትኩረት ማዕከል የሆነችው በውብ የኮሪደር ልማቷ፣ በወንዝ ዳርቻዎቿ ውበት፣ ወይም በሌሎች ፕሮጀክቶቿ ብቻ አይደለም። ብሩህ አእምሮ ያለው ጤናማ ትውልድ በማፍራት፣ ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ ከተማ መሆኗን በተግባር በማሳየትና የዜጎችን በተለይም የሕፃናትን ሕይወት በሚቀይር የሰብዓዊ ልማት ሥራዋ ጭምር ነው። ይህ በሰብዓዊነት እና በትውልድ ላይ የተደረገው ጥልቅ ኢንቨስትመንት የመንግስትን የመደመር እሳቤ መሬት ያወረደ፣ ዜጎችን በአንድነት አስተባብሮ ከተማዋን እውነተኛ የብልፅግና ተምሳሌት ያደረጋት ሲሆን፣ ተደጋጋሚ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን እንድትቀዳጅ ያስቻላት ዋነኛ ሚስጥርም ይኸው ነው።

በክፍለ ከተማው አስተዳደር በወረዳ 05 መጪው  አዲስ አመት በዓልን  አስመልክቶ ኢግዚብሽንና ባዛር በይፋ ተከፈተ፡፡ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን ነሐሴ  28 /2018 ዓ.ምበክፍለ ከተማው መጪ...
03/09/2026

በክፍለ ከተማው አስተዳደር በወረዳ 05 መጪው አዲስ አመት በዓልን አስመልክቶ ኢግዚብሽንና ባዛር በይፋ ተከፈተ፡፡

ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን
ነሐሴ 28 /2018 ዓ.ም

በክፍለ ከተማው መጪው አዲስ አመት በዓልን አስመልክቶ በወረዳ05 አስተዳደር በአየር ጤና አደባባይ ኤግዚቢሽንና ባዛር በይፋ ተከፍቷል ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ምክትል ኮሚሽነር አቶ መሐመድ ልጋኒ የኤግዚቢሽንና ባዛር መከፈቱን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ11 ዱም ክፍለ ከተማዎችና እና በሁሉም ወረዳዎች በዛሬው እለት ኤግዚብሽንና ባዛሮች መከፈቱን አንስተዋል።

የተዘጋጁ ኤግዚብሽንና ባዛሮች በዋናነት ነዋሪዎች በአቅራቢያቸው ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ የሚያስችል እንደሆነና የክፍለ ከተማው ነዋሪ በአቅራቢያው በተዘጋጁ ኤግዚብሽንና ባዛሮች ላይ በመገኘት ግብይት እንዲፈፅምም ጥሪ አቅርበዋል።

እስከ በአሉ ድረስም ምርቶች በስፋት እንደሚቀርቡ የገለፁት አቶ መሐመድ ለኤግዚብሽኑና ባዛሩ አስፈላጊ ዝግጅት ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

አቶ አከበረኝ ወጋገን የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅህፈት ቤት ሀላፊ በበኩላቸው አዲስ አመትን በማስመልከት የክፍለ ከተማው አስተዳደር በባዛሮች፣ በገበያ ማእከላትና በ22 የቅዳሜና እሁድ ገቢያዎች ምርቶችን በስፋትና በጥራት ማቅረቡን ገልፀዋል።

ሀላፊው አክለው ህብረተሰቡ በአልን በደስታ እንዲያሳልፍ እና የኑሮ ውድነት ለማረጋጋት ባዛሩ ጠቀሜታ እንዳለው ገልፀው በዓሉን ምክንያት በማድረግ የኢንዱስትሪ፣ የግብርና፣ እንዲሁም የእንስሳት ተዋፅኦ መቅረቡን አስታውቀዋል።

በወረዳው በአየር ጤና አደባባይ በተከፈተው ኤግዚብሽን እና ባዛር በክፍለ ከተማው የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ኢንተርፕራይዞች ፣ ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት፣ አርሶ አደሮች እንዲሁም የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች የሚሰሩ ነጋዴዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

በኤግዝብሽኑ የባህል አልባሳት፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ ማርና የማር ውጤቶች፣ የኢንደስትሪ ምርቶች ፣ የግብርና ምርቶች፣ የእንስሳት ተዋጽኦዎች፣አትክልትና ፍራፍሬዎችን ጨምሮ ሌሎች ለበአል የሚውሉ የተለያዩ ምርቶች የቀረቡ ሲሆን እስከ ጳጉሜ 05/2018 ድረስም የሚቆይ ነው።

በመርሀ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአርሶ አደርና የከተማ ግብርና ምክትል ኮሚሽነር አቶ መሐመድ ልጋኒ ፣የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አከበረኝ ወጋገን፣ክብርት ወ/ሮ ቦጋለች ተድላ የክፍለ ከተማዉ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ፣አቶ ኢብራሒም መሐመድ የክፍለ ከተማው የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊን ጨምሮ ሌሎች የክፍለ ከተማ ፣ የወረዳ አመራሮች እና ነዋሪዎች ተገኝተዋል ።

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬ...
03/09/2026

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል።

‎በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል።

‎ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው።
‎ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፉ Act For Early Years  ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” ተብለው እውቅና ተሰጣቸው።ይህ እውቅና የከንቲባ አዳነች አቤቤ አመራራቸውንና...
02/09/2026

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም አቀፉ Act For Early Years ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” ተብለው እውቅና ተሰጣቸው።

ይህ እውቅና የከንቲባ አዳነች አቤቤ አመራራቸውንና የከተማ አስተዳደሩ ለሕፃናት እድገት እያደረገ ያለውን ኢንቨስትመንት በተለይም በ"የአዲስ አበባ የወደፊት ተስፋ የቅድመ ልጅነት እድገት ተነሳሽነት" የተሰጠ እውቅና ነው።

ኢኒሼቲቩ ቀዳማይ ልጅነትን በመንግሥታት ፖሊሲዎች እና በዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት አጀንዳ ማዕከል ላይ ለማስቀመጥ በትኩረት ይሰራል።

ይህ እውቅና የተሰጠው ከቀድሞው የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም አቀፍ ትምህርት ልዩ መልዕክተኛ ጎርደን ብራውን በኩል የኢኒሼቲቭ አጋሮች በመወከል ሲሆን ፣ UNICEF እና UNESCOን ጨምሮ ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የተሰጠ ነው።

እውቅናው አዲስ አበባን በአፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት እድገት የከተማ አመራር ተምሳሌት ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያጠናክረው ይታመናል።

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎችጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
02/09/2026

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች

ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”

ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”

ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”

ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”

ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”

በወረዳ አስተዳደሩ የሚሰጡ አገልግሎቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉ በመምጣታቸው ምልልሶችን  መቅረፍ ተችሏል ሲሉ  ተገልጋዮች ገለፁ።ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን ነሀሴ27/2018 ዓ.ምበኮልፌ ...
02/09/2026

በወረዳ አስተዳደሩ የሚሰጡ አገልግሎቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉ በመምጣታቸው ምልልሶችን መቅረፍ ተችሏል ሲሉ ተገልጋዮች ገለፁ።

ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን
ነሀሴ27/2018 ዓ.ም

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር የሚሰጡ አገልግሎቶች በየጊዜው እየተሻሻሉ በመሆኑ የነበረውን ምልልስና እንግልት መቅረፍ በመቻሉ ጊዚያችንን መቆጠብና ምልልስን መቀነስ ተችሏል ሲሉ ተገልልጋዮች ገልፀዋል።

የወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት የአገልግሎት ቀን የሆኑትን ረቡዕና አርብን ምክንያት በማድረግ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ስለሚሰጡ አገልግሎቶች የተገልጋዮችን ሀሳብ አስተያየት አነጋግሯል።

ተገልጋዮቹም በሰጡት ሀሳብ በወረዳ አስተዳደሩ የሚገኙ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀድሞ ከነበረው አንፃር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉ በመምጣታቸው የነበረውን ምልልስ በመቅረፉ ቀልጠፋና ፈጣን በሆነ መልኩ በተሻለ አቀባበል ጥራት ያለው አገልግሎት እያገኘን ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ቀድሞ ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶች ምልልስ የበዛባቸውና ጊዜንና ጉልበትን የሚያበክኑ ነበሩ፤በአሁኑ ወቅት ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት በመኖሩ መደሰታቸውን ተገልጋዮች በንግግራቸው አብራርተዋል።

 🎯ሳምንታዊ የፀረ ሙስና መልዕክትፍትሐዊ ተጠቃሚነት የሚረጋገጠው ከሙስና የፀዳ አሰራር ሲሰፍን ነው!!
02/09/2026


🎯ሳምንታዊ የፀረ ሙስና መልዕክት

ፍትሐዊ ተጠቃሚነት የሚረጋገጠው ከሙስና የፀዳ አሰራር ሲሰፍን ነው!!

የ2019 ዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ በቂ የበዓል ፍጆታ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ፡፡የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ መጪውን የአዲስ ዓመ...
01/09/2026

የ2019 ዘመን መለወጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ በቂ የበዓል ፍጆታ በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ፡፡

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ መጪውን የአዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ በአገር ውስጥ ለሚገኙ ሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

ወ/ሮ ሀቢባ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የከተማ አስተዳደሩ መጪውን የአዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ የምርት እጥረት እንዳይፈጠር ከክልሎች እና ከአጎራባች ከተሞች ጋር በቅርበት ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው ለዚህም በቂ የበዓል ፍጆታ ምርቶች መዘጋጀታቸውን አሳውቀዋል።

ወ/ሮ ሀቢባ አክለውም ከ28/12/18 ዓ ም ጀምሮ በዓሉን በማስመልከት በ11ዱም ክ/ከተሞች የበዓል ባዛሮች በይፋ ስራ የሚጀምሩ መሆኑን ገልፀው የእሁድ ገበያዎችም ሳምንቱን ሙሉ ክፍት እንደሚሆኑ ተናግረዋል።

በባዛሮቹ ከበዓል ፍጆታዎች በተጨማሪ የኢንዱስትሪ ምርቶች፣ ለትምህርት የሚሆኑ ግብዓቶች እና የተለያዩ አልባሳቶች የሚቀርቡ መሆናቸውን ወ/ሮ ሀቢባ አሳውቀዋል።

በዓሉን ምክንያት በማድረግ አርቴፊሻል የሆነ የዋጋ ንረት እንዳይፈጠር የቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ያሳወቁት ክብርት ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ በየደረጃው የሚገኙ የህገ-ወጥ ንግድ መከላከልና የገበያ ማረጋጋት ግብረ-ኃይል አባላት ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እንዲሰሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ በመግለጫቸው የበዓል ፍጆታ ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ በቂ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀው፣ ህገ-ወጥ የሆነ ማንኛውም የንግድ እንቅስቃሴ ሲያጋጥም የከተማችን ነዋሪ በ8588 ነፃ የስልክ ጥሪ በመደወል ጥቆማ መስጠት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኮልፌ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን-Kolfe Woreda 05 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share