30/01/2026
በአዲስ አበባ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ክላስተር 3 ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት የ6ወር ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ እና በአዋጅና ደንብ እንዲሁም በመመሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ።
***ጥር 07/2018 ዓ.ም***
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን ቂርቆስ ቅርንጫፍ ክላስተር 3 የ2018 በጀት ዓመት የ6ወር አፈጻጸም እና በአዋጅና ደንብ እንዲሁም በመመሪያ ከጤና ፎረም፣ ከባለድርሻ አካላት፣ ከንግዱ ማህበረሰብና ከነዋሪው ጋር ዉይይት ተካሄደ።
የቂርቆስ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ሲስተር አለምሽ አባይ ባለፉት ስድስት ወራት በጽ/ቤቱ የህብረተሰብ ጤና እና ደህንነት ለማስጠበቅ በመደበኛ ቁጥጥር እንዲሁም በዘመቻ በርካታ ስራዎች መከናወናቸዉን ጠቅሰዉ በእቅድ ከተያዙት ስራዎች በተጨማሪ ሌብነትና ብልሹ አሰራር ከመከላከል አንጻር፣ተቋማዊ ውጤታማነት በማሻሻል የሰራተኛና ተገልጋይ እርካታ ከማሳደግ አንጻር፣ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠርና አገልግሎትን ከማሻሻል አንጻር እንዲሁም የህዝብ፣ሲቪል ማኅበራትና የግል ሴክተር ተሳትፎ ስርዓትን ከማሳደግ አንፃር በ6 ወራት ውጤታማ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።
በአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ቂርቆስ ቅርንጫፍ ክላስተር 3 ፅ/ቤት በዛሬው ዕለት የ6 ወር እቅድ አፈጻጸምና በአዋጅ፣ ደንብና መመሪያ ዙሪያ የወይይት ሰነድ በማድረግ የቂርቆስ ቅርንጫፍ ክላስተር 3 ጽ/ቤት ስራ አስካጅ አቶ ዳኛቸው ግዛው ለባለድርሻ አካላት በዛሬው ዕለት ግንዛቤ ያቀረቡ ሲሆን በመቀጠል ከአዋጅና ደንብ መመሪያ ጋር የብቃት ማረጋገጥ ባለሙያ አቶ ሙሉጌታ ጋሻው ከትምባሆ እና አደንዛዥ እጽ ጋር በተያያዘ ከመመሪያና አዋጅ ጋር በማመሳከር በቀረበው ሰነድ ተወያይተዋል።
ጽ/ቤቱም በ2018 ግማሽ አመትየህብረተሰብን ጤና ደህንነቱን የጠበቀ አገልግሎት ለሚሰጡ 349 ተቋማት ብቃት መረገገጫ መስጠቱን አስታውቆል።
በመጨረሻም ባለድርሻ አካላቱ የማህበረሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ከቤቱም ለቀረቡ ሀሳቦች፣ አስተያየቶችና ጥያቄዎች የክላስተር 3 የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ግዛው ምላሽ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን አንዳንድ ቀሪ ስራዎች ያሉ መሆናቸውን በመግለጽ የባለድርሻ አካላቱ ተሳትፎና ሚና ወሳኝ መሆኑን ገለጸው በቀጣይነት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አቅጣጫ በማስቀመጥ የጥቆማ ነጻ 8864 ላይ ጥቆማ በመስጠት እንደሚቻል በመግለጽ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ መድረኩ ተጠናቋል::