Addis Ababa City Government Bureau of Justice

Addis Ababa City Government Bureau of Justice Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Addis Ababa City Government Bureau of Justice, Government Organization, Mexico, Addis Ababa.

05/06/2026
04/06/2026

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - ግንቦት 27፣ 2018 ዓ.ም

04/06/2026
በሴቶች መብት እና ሴቶች ላይ በሚፈጸም ጾታዊ ጥቃት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡ስልጠናው በአዲስ አበባ ...
04/06/2026

በሴቶች መብት እና ሴቶች ላይ በሚፈጸም ጾታዊ ጥቃት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡

፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡

ስልጠናው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ ህግ ስርጸት እና ምክር መስጠት ዳሬክቶሬት የተዘጋጀ ሲሆን የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር አመራሮች ተሳትፈመዋል፡፡

በወቅቱ የፍትህ ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቸቶ አሰፋ መብራቴ መምህራን በሴቶች መብት እና ሴቶች ላይ በሚፈጸም ጾታዊ ጥቃት ህጉ ምን ይደነግጋል የሚለውን አውቆ ነገ ሃገር የሚረከቡ ተማሪዎች ባለማወቅ የጥቃቱ ሰለባ እንዳይሆኑ ግንዛቤ እንዲፈጥሩላቸው የተዘጋጀ የአሰልጣኞች ስልጠና መሆኑን ገልጸው ሰልጣኞች የስልጠናውን አላማ ለተፈለገው አላማ ማዋል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በአዲስ አበባ መምራን ማህበር ተጠሪ ወይዘሮ እየሩሳሌም ብዙነህ በበኩላቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ የህግ ስርጸት ዳይሬክቶሬት በነባር እና አዳዲስ ህጎች ዙሪያ ለማህበሩ በተደጋጋሚ ግንዛቤ ፈጠራ መስራቱን ገልጸው በማመስገን ዛሬም የሴቶችን ጥቃት አስመልክቶ በተሰጠው ስልጠና የመምህራን ማህበር አመራሮች ለተማሪዎቻቸው ግንዛቤ መፍጠር እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡

ዐቃቢ መሰረት ጸሃይ ስልጠናውን ሲሰጡ በኢትዮጲያ ህገመንግስት አንቀጽ 35 የተደነገጉትን የሴቶች መብቶች ፣በኢትዮጲያ አሰሪ እና ሰራተኛ አዋጅ ፣በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዲሱ የመንግስት ሰራቶች አዋጅ 87/2017 ስለ ትንኮሳ እና አዎንታዊ ድጋፍ ፣በኢትዮጲያ አዲሱ የወንጀል ህግ የሴቶችን ጥቃት በተመለከተ እንዲሁም የቤተሰብ ህጉ ከአለም አቀፍ ስምነቶች ጋር በምነጻጸር የተብራራ ሲሆን ሴቶችን አስመልክቶ የተደረጉ አለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ተወስተዋል፡፡

03/06/2026

የወርሀ ሚያዝያ እና ግንቦት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት

03/06/2026

“የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግሥት በራሳቸው ሊኮሩ ይገባል” - ኡሁሩ ኬንያታ

የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እና የኢጋድ ታዛቢ ቡድን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደት አስመልክቶ የመጀመሪያ ዙር የግምገማ ውጤት ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።

የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ የሆኑት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግሥት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ባሳዩት ድንቅ የሆነ አፈጻጸም በራሳቸው ሊኮሩ ይገባል ብለዋል።

“ኢትዮጵያውያን ከማለዳው ጀምሮ በቁርጠኝነት ለመምረጥ ተሰልፈዋል፤ ይህን ታላቅ ሁነት በኢትዮጵያ የተለያዩ ቦታዎች ተመልክተነዋል፤ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ የታዘብነው ምርጫ በስኬት በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ” ሲሉ አጠቃላይ ሁኔታውን ገልጸውታል።

“ኢትዮጵያውያን ታሪክ ይሠራሉ፤ ቀኝ ገዢዎችን በጋራ ተዋግተዋል፤ ይህም በአፍሪካ ብቸኛ ሀገር እንድትሆን አስችሏታል፤ የአፍሪካ የነፃነት ምልክቷ ኢትዮጵያ ነች” ብለዋል።

የአፍሪካ ኅብረት ምርጫውን ለመታዘብ ቀጠሮ ከያዘ ጊዜ ጀምሮ የምርጫውን ታማኝነት እና ዴሞክራሲያዊነት ስንከታተል ነበር ያሉት ኡሁሩ ኬንያታ፣ ምርጫ ቦርድ ቀደም ብሎ የሠራው ሥራ መራጮች ሳይደናገሩ ድምፅ እንዲሰጡ እንዳስቻለ አንሥተዋል።

በምርጫው ዕለት የፖለቲካ ፓርቲ ታዛቢዎች የምርጫውን ሂደት በነጻነት ሲከታተሉ እንደነበር ጠቁመው፣ “በዚህም የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያለውን ታላቅ ቁርጠኝነት የታዘብንበት ነበር” ብለዋል።

Address

Mexico
Addis Ababa
15052

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30

Telephone

+251115159603

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa City Government Bureau of Justice posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ababa City Government Bureau of Justice:

Share