Ethiopian Health Insurance Service

Ethiopian Health Insurance Service to promote Health Insurance in Ethiopia Ethiopian Health Insurance Service

የኢትዮጵያ ጤና መድኅን አገልግሎት የ9 ወራት የዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ01/09/2018 ኢጤመአየኢትዮጵያ ጤና መድኅን አገልግሎት የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን...
09/05/2026

የኢትዮጵያ ጤና መድኅን አገልግሎት የ9 ወራት የዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ
01/09/2018 ኢጤመአ
የኢትዮጵያ ጤና መድኅን አገልግሎት የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን አስመልክቶ ከመላው ሠራተኞቹ ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ። በውይይቱ ላይ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋየ ወርቁ ተገኝተው የሥራ መመሪያና ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ ተቋሙ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ያስመዘገባቸው አበይት ድሎችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በዝርዝር ተናግረዋል።
አሁን አለንበት ደረጃ ለመድረስ የተመቻቹ ነገሮችም የመኖራቸውን ያክል ውጣ ውርዶች ነበሩ ያሉት አቶ ተስፋየ የቀጣዮቹ ቀሪ ወራቶች እስካሁን ያልተሰሩ ተግባራት የሚከናወኑበትና የ2019 በጀት አመት የዝግጅትት ስራዎችም በመኖራቸው በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
የዕቅድ አፈጻጸሙን ሪፖርት ያቀረቡት የአገልግሎት የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ከፍያለው ሞቲ፣ተቋሙ በዘጠኝ ወራት ውስጥ የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን (CBHI) ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉንና በአገር አቀፍ ደረጃ የወረዳ ሽፋኑን 96% መድረሱን ገልጸውው፣የአባላቱን ቁጥር 15 ሚሊዮን በማድረስ አጠቃላይ ተጠቃሚዎችን ወደ 69 ሚሊዮን ማደጉን ይፋ አድርገዋል።
የአባላትን መረጃ በዘመናዊ መንገድ ለመያዝ የሚያስችል የዲጂታል ሲስተም በትግበራ ላይ ሲሆን፣ ከ650 በላይ ወረዳዎች መረጃዎቻቸውን ወደ ሲስተሙ አስገብተዋል። በተጨማሪም የማኅበራዊ ጤና መድኅን (SHI) ትግበራን ለማሳለጥ አዲስ ሲስተም ለምቶ ወደ ሥራ መግባቱም ተወስቷል
በአገር አቀፍ ደረጃ ሁሉን አቀፍ የጤና መድኅን ሽፋን ለማሳደግ በ17 የሀገሪቱ ክፍሎች ከሚገኙ የማህበረሰብ ራዲዮ ጣቢያዎች ጋር በመቀናጀት ሳምንታዊ ፕሮግራሞች መጀመራቸው እና ከኢትዮጵያ ራዲዮ ጋር በመተባበር በመካከለኛው ሞገድ (MW) መደበኛ የአየር ሰዓት ተረክቦ ስራ መጀመሩን የገለጸው ሪፖርቱ፣
እንደ ኢቢሲ፣ ፋና እና ኢዜአ ካሉ ግዙፍ የሚዲያ ተቋማት ጋር በመተባበር ከ55 ጊዜ በላይ ዘገባዎች እንዲተላለፉ መደረጉና በከፍተኛ አመራሮች በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የ16 የሚዲያ ተቋማትን ሽፋን ማገኝቱ ተነግሯል።
ለዓመታት ሲጠበቅ የነበረው የማኅበራዊ ጤና መድኅን ሥርዓት ባሳለፍነው ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ተጀምሮ የጤናው ዘርፍ የመንግሥት ሠራተኞችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ሥርዓቱ እንዲገቡ መደረጉም ተነግሯል
አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ከአባላት መዋጮና ከተለያዩ ድጎማዎች በአጠቃላይ ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብ መቻሉን ገልጾ፣የመክፈል አቅም ለሌላቸው ዜጎች የሚሰጠው የጥቅል ድጎማ ሙሉ በሙሉ ለወረዳዎች የተላለፈ ሲሆን፣ መጠኑም 2.9 ቢሊዮን ብር መሆኑ አስታውሷል።
በሆስፒታሎች የሚሰጠውን የህክምና አገልግሎት ጥራት ለማረጋገጥ የክሊኒካል ኦዲት ሥራዎች መከናወናቸውና ከመንግሥት የሪፎርም ሥራዎች ጋር ተያይዞ የሠራተኞች የብቃት ምዘናና የደመወዝ ስኬል ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጋቸው የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና የሠራተኛውን አቅም ለመገንባት የትሰሩ ተግባራት መሆናቸውን በሪፖርቱ አመላክቷል
በክልል ደረጃ የሚፈለገው የከፍተኛ አመራር ድጋፍ አናሳ መሆን፣ ከሥራው ስፋት ጋር የሚመጥን አደረጃጀት አለመፈጠርና በጤና ተቋማት የሚሰጠው የሕክምና አገልግሎት የጥራት ችግር፣ ደካማ የመረጃ ልውውጥና የጥራት ቁጥጥር ሥርዓት፣ እንዲሁም የሥራ እንቅስቃሴን የሚያደናቅፍ የተሽከርካሪ እጥረት የስራ መሰናክሎች ነበሩ ያለው በሪፖርቱ ቀርብዋል፡፡
የሪፎርም ተግባራትን ማጠናከር፣ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚሆን አዲስ የኢንቨስትመንት ስትራቴጂክ ዕቅድ ማዘጋጀት፣የፌደራል ፑል የሚመሰረትበትን ሁኔታ በማመቻቸት የፋይናንስ መሰረቱን ማጠናከርና የክሌም ማኔጅመንትን እና የፋይናንስ ኦዲትን ማጠናከር፣ እንዲሁም አሰራርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ማድረግ በትኩረት ሊሰራባቸው የታቀዱ ጉዳዮች ናቸው ብሏል"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥን እያቀላጠፈ መሆኑ ተገለጸ30/08/ 2018 ዓ/ም ኢጤመአየየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሀኪም እና የሆስፒታሉ ፕሮቮስት አማ...
08/05/2026

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥን እያቀላጠፈ መሆኑ ተገለጸ
30/08/ 2018 ዓ/ም ኢጤመአ
የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሀኪም እና የሆስፒታሉ ፕሮቮስት አማካሪ ዶክተር አብዮት አለሙ፤ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን (CBHI) በአሁኑ ወቅት የህክምና ስርአቱን በከፍተኛ ሁኔታ እያገዘ እንደሚገኝ ገለጹ።
ዶክተር አብዮት እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት የሆስፒታሉ የህክምና ፈላጊዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ እስከ 89 በመቶ የሚሆኑት የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ናቸው። ይህም ስርአቱ ለማህበረሰቡ ያለውን ተደራሽነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዶክተር አብዮት የመድህን አገልግሎቱ በስራቸው ላይ ያመጣውን በጎ ተጽእኖ ሲያብራሩ፣ ቀደም ሲል ሀኪሞች ታካሚው ለህክምናው ክፍያ የመክፈል አቅም አለው ወይስ የለውም በሚል ስጋት ይሳቀቁ ነበር። አሁን ግን ይህ ተቀርፎ ሀኪሞች የታካሚውን የገንዘብ አቅም ሳይሆን የጤና ሁኔታን ብቻ መሰረት በማድረግ አስፈላጊውን ህክምና በነጻነት እንዲያዙ አስችሏቸዋል። በመድህን አማካኝነት የሚሰበሰበው ክፍያ የሆስፒታሉ የውስጥ ገቢ እንዲያድግና የህክምና ግብአቶችን ለማሟላት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።
የጤና መድህን ስርዓት ዜጎች ከኪስ የሚከፈል የክፍያ ስጋት ስለሌለባቸው ህመማቸው ሳይጸናባቸው በጊዜ ወደ ህክምና ተቋም እንዲመጡ በማስቻሉ፣ በሽታዎች ስር ሳይሰዱ መፍትሄ እንዲያገኙ ትልቅ ሚና ተጫውቷል ሲሉ አክለዋል።
የካቲት 12 ሆስፒታል ከኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ጋር መልካም የስራ ግንኙነት እንዳለውና ከሚመለከታቸው የስራ ሀላፊዎች ጋር በየጊዜው በመገናኘት ተጋርጠው የሚመጡ ችግሮችን በጋራ እየፈቱ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

የጤና መድህን ለዜጎችም ለባለሙያዎችም እፎይታን ሰጥቷል” - ዶ/ር አንተነህ ምትኩ30/08/2018 ዓም ኢጤመአየየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር አንተነህ ምትኩ፣...
08/05/2026

የጤና መድህን ለዜጎችም ለባለሙያዎችም እፎይታን ሰጥቷል” - ዶ/ር አንተነህ ምትኩ
30/08/2018 ዓም ኢጤመአ
የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ዋና ስራ አስኪያጅ ዶክተር አንተነህ ምትኩ፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት ዜጎችን ካልታሰበ የህክምና ወጪ ስጋት ከመታደጉ ባለፈ፣ ለህክምና ባለሙያዎችም ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠሩን ገለጹ።
ሆስፒታሉ ከኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ጋር በገባው ውል መሰረት ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የጠቀሱት ዋና ስራ አስኪያጁ፤ አገልግሎቱ በተለይ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎች በገንዘብ እጥረት ምክንያት ሳይሳቀቁ የታከሙበትንና የዳኑበትን አጋጣሚ ማየት ትልቅ ሙያዊ እርካታ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
ከጤና መድህን አገልግሎት መጀመር በፊት የነበረውን ሁኔታ ያስታወሱት ዶክተር አንተነህ፣ “ቀደም ሲል የህክምና ባለሙያዎች ለአንድ ታካሚ አስፈላጊውን ምርመራና መድሃኒት ለማዘዝ የታካሚውን የመክፈል አቅም ግምት ውስጥ ማስገባት ግድ ይላቸው ነበር፤ ይህም በባለሙያው ላይ ከፍተኛ የስነ-ልቦና ጫና ይፈጥር ነበር” ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ግን ባለሙያዎች ያለምንም መሳቀቅ አስፈላጊውን ህክምና እንዲሰጡ ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል።
በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ያብራሩት ዋና ስራ አስኪያጁ፣ በዓመት ከሚስተናገዱ 300 ሺህ ተመላላሸ ታካሚዎች መካከል 200 ሺህ የሚሆኑት የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎች ናቸው።
በተጨምሪም 29 ሺህ ከሚሆኑት አመታዊ የተኝቶ ታካሚዎችታካሚዎች ውስጥ 19 ሺህ ያህሉ በአገልግሎቱ የታቀፉ ናቸው። ይህ ቁጥር የሚያሳየው ህብረተሰቡ የህክምና ወጪ ስጋት ሳይኖርበት ወደ ጤና ተቋማት የመምጣት ልምዱ እያደገ መምጣቱን ሲሆን፣ ከገቢ አኳያም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ለሰጠነው የህክምና አገልግሎት የመልሶ ክፍያ 76 ሚሊየን ብር አግኝተናል ብለዋል፡፡
ቀደም ሲል በመድሃኒት እጥረት ዙሪያ የሚነሱ ቅሬታዎች በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው መፈታታቸውን የገለጹት ዶክተር አንተነህ፣ ቀሪ ችግሮችን ለመቅረፍ የጤና ተቋማት፣ የመድሃኒት አቅራቢዎችና የጤና መድህን አገልግሎት በቅንጅት የሚሰሩበት መድረክ ሊመቻች እንደሚገባ አሳስበዋል።
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን ፋይዳ በእነ አቶ ታዬ ሰርጤ ቤተሰብ29/08/2018ዓ.ም  ኢጤመአአቶ ታዬ ሰርጤ የ70 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ እና የ4 ቤተሰቦች አስተዳዳሪ ናቸው። ነዋሪነታቸው...
07/05/2026

የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን ፋይዳ በእነ አቶ ታዬ ሰርጤ ቤተሰብ
29/08/2018ዓ.ም ኢጤመአ
አቶ ታዬ ሰርጤ የ70 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ እና የ4 ቤተሰቦች አስተዳዳሪ ናቸው። ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ወረዳ 6 (በተለምዶ ሳሪስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ) ነው። አቶ ታዬ በሳሪስ የመጀመሪ ደረጃ ህክምና መስጫ ማዕከል እግራቸውን የመደንዘዝ ስሜት እየተሰማቸው ለህክምና በመጡበት ወቅት ካነጋገርናቸው ታካሚዎች አንዱ ናቸው።
አቶ ታዬ ስለ ጤና መድኅኑ ያላቸው ግንዛቤ እጅግ ጥልቅ ነው። ፕሮግራሙ በአካባቢያቸው በተጀመረበት ማግስት ነበር አባል የሆኑት። አባል ለመሆን የወሰኑበትን ምክንያት ሲገልጹም፦ "መንግስት የጤና መድኅን ተጠቃሚ እንድንሆን ሲያመጣልን የህብረተሰቡን የመረዳዳደት እና የመደጋገፍ እሴትን ለማሳደግ እንደሆነ ገብቶኛል" ይላሉ።
እንደ አቶ ታዬ እምነት፣ የጤና መድኅን ስርዓት ለታመሙት ብቻ ሳይሆን ጤነኛ ለሆኑትም ትልቅ ትርጉም አለው። "ብንታመም ልንታከምበት፣ ባንታመም ደግሞ ሌሎች የሚታመሙትን ለመደገፍ የመጣው ስርዓት በሽታን በመቆጣጠር ሰዎች በዕለት ስራቸው ውጤታማ እንዲሆኑ እና በሀገር ልማት ላይ እንዲሳተፉ እገዛ ያደርጋል" በማለት የጤና መድኅኑን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያስረዳሉ። ይህ አስተሳሰብ "ጤናማ ዜጋ ለሀገር እድገት መሰረት ነው" የሚለውን መርህ በግልጽ ያሳያል።
ምንም እንኳን የጤና መድኅኑ በአግባቡ እና በጥራት ህክምና ማግኘት መቻላቸው ቢሆንም፣ አቶ ታዬ ያጋጠሟቸውን ክፍተቶች ከመጠቆም አልተቆጠቡም። በተለይም የመድኃኒት አቅርቦት ላይ ትልቅ ችግር እንዳለ ይናገራሉ።
ታካሚው በጤና ጣቢያው ታይቶ መድኃኒት ሲታዘዝለት፣ በጤና ጣቢያውም ሆነ በ'ከነማ' መድኃኒት ቤት ካጣ፣ ወደ ግል ፋርማሲዎች እንዲሄድ ይገደዳል። "የውጭ የመድኃኒት ዋጋ ከእኛ አቅም በላይ ነው" የሚሉት አቶ ታዬ፣ አገልግሎቱ ሙሉ እንዲሆን ከተፈለገ የመድኃኒት አቅርቦት ጉዳይ በአፋጣኝ ሊስተካከል እንደሚገባ በአጽንኦት ያሳስባሉ።
የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትን ያገኘ እና ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ስርዓት ነው። ይሁን እንጂ የጤና ተቋማት የመድኃኒት ክምችታቸውን በማሳለጥ እና አቅርቦቱን አስተማማኝ በማድረግ የታካሚዎችን እንግልት መቀነስ ይኖርባቸዋል።
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

ማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህንና የዜጎች ተጠቃሚነት28/08/2018 ዓም ኢጤመአየሕክምና አገልግሎት ዋጋና የኑሮ ውድነቱ ተዳምሮ ለብዙዎች ፈተና በሆነበት በዚህ ወቅት፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤ...
06/05/2026

ማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህንና የዜጎች ተጠቃሚነት
28/08/2018 ዓም ኢጤመአ
የሕክምና አገልግሎት ዋጋና የኑሮ ውድነቱ ተዳምሮ ለብዙዎች ፈተና በሆነበት በዚህ ወቅት፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ሥርዓት ለብዙ ኢትዮጵያውያን ትልቅ እፎይታ እየሆነ ይገኛል። አዲስ አበባ ሳሪስ አካባቢ የሚኖሩትና የሁለት ልጆች አባት የሆኑት የ60 ዓመቱ አዛውንት አቶ ሰለሞን ዴሴ የዚህ ተጠቃሚነት ምስክር ናቸው።
አቶ ሰለሞን ቀደም ሲል በግል ድርጅት ውስጥ በሹፌርነት ሙያ ተቀጥረው ቤተሰባቸውን ያስተዳድሩ ነበር። አሁን ላይ ግን ቋሚ ሥራ የላቸውም። ልጆቻቸውም ገና ለሥራ ያልደረሱ በመሆናቸው፣ በገቢ እጥረት ውስጥ ሆነው የሕክምና ወጪን መሸፈን የማይታሰብ እንደሆነባቸው እንዲህ ሲሉ ይገልጻሉ፦
"ወደ ጤና መድህን ሥርዓት ከገባሁ ጀምሮ እኔም ቤተሰቤም በአገልግሎቱ እየተጠቀምን እንገኛለን፤ ትልቅ የሃሳብ ሸክም ነው ከላያችን ላይ ያነሳልን። ከኑሮ አልፎ ለሕክምና የሚሆን ገቢ በሌለበት ሁኔታ፣ የጤና መድህን ለእኔ እጅግ ጠቃሚ ማህበራዊ አገልግሎት ነው።"
አቶ ሰለሞን ለምርመራ ውጤት ሆስፒታል በተገኙበት ወቅት እንደተናገሩት፣ የመድህን ሥርዓቱ በመንግስት የሚደጎም በመሆኑ አቅመ ደካሞችን በእጅጉ እየረዳ ይገኛል። "ለአንድ ጊዜ ሕክምና የማይበቃ ዓመታዊ የአባልነት መዋጮ ከፍለን ነው የምንታከመው፤ ይህ ባይሆን ኖሮ በአሁኑ ሰዓት የሕክምና ወጪን በግላችን መቻል አንችልም ነበር" ይላሉ።
እኚሁ አባት ለዓመታት በአስም በሽታ ስለሚሰቃዩ ተከታታይ ሕክምና ያስፈልጋቸዋል። ይህንን አስቸጋሪ የጤና ሁኔታና የልጃቸውን የጨጓራ ህመም ያለ ምንም እንግልት በመድህን አገልግሎቱ ማከም መቻላቸውን በደስታ ይናገራሉ፦
እኔ አስም ስላለብኝ ተከታታይ ሕክምና ነው የምወስደው፤ ያንንም እዚሁ በጤና መድህን አገኛለሁ፣ልጄም ጨጓራ አሞት መጥቶ ሁሉንም ሕክምና እዚሁ አግኝቶ ነው የሄደው ይሄ ድግሞ ለኔ ቀላል የሚባል ጥቅም አይደለም ይላሉ ባለታሪካችን።
የአቶ ሰለሞን ተሞክሮ እንደሚያሳየው፣ የጤና መድህን በተለይም ቋሚ ገቢ ለሌላቸውና ዝቅተኛ ኑሮ ለሚመሩ የህብረተሰብ ክፍሎች የህልውና ዋስትና እየሆነ ነው። ለአንድ ጊዜ የሕክምና ወጪ የማይበቃ ክፍያ በመክፈል፣ ዓመቱን ሙሉ ሙሉ የጤና አገልግሎት ማግኘት መቻሉ ማህበራዊ ፍትህን ከማረጋገጡም በላይ፣ ዜጎች በሕመም ምክንያት ወደ ባሰ ድህነት እንዳይገቡ ትልቅ ጋሻ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

የረጅም ጊዜ ህክምና ወጪ ለመቋቋም-የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን ጠቀሜታ አለው 28/08/2018 ዓ.ም ኢጤመአየማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን (CBHI) ህብረተሰቡ በጋራ መረዳዳትና መደጋገፍ...
06/05/2026

የረጅም ጊዜ ህክምና ወጪ ለመቋቋም-የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን ጠቀሜታ አለው
28/08/2018 ዓ.ም ኢጤመአ
የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን (CBHI) ህብረተሰቡ በጋራ መረዳዳትና መደጋገፍ መርህ ላይ ተመስርቶ የህክምና ዋስትና እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል። በአዳማ ሆስፒታል ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ውስጥ ያገኘነው ወጣት ተሰማ ለማ፣ የዚህ ሥርዓት ተጠቃሚነትና ያለውን ፋይዳ በተጨባጭ ምስክርነቱ ያስረዳናል።
ወጣት ተሰማ ለማ የ27 ዓመት ጎልማሳ ሲሆን፣ የአምስት ቤተሰብ አባላትንና በፅኑ የታመመችውን ቤተሰቡን ዲማ ኮርማን እያስታመመ ይገኛል። ወጣት ዲማ መጀመሪያ ላይ በቦስት ወረዳ፣ ቦፋ ቀበሌ በሚገኘው ጎዳኢራ የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና መስጫ ማዕከል የህክምና ክትትል ስታደርግ ቆይታለች። ይሁን እንጂ የያዛት የሰውነት ማበጥና የማነቀጥቀት ህመም እየፀናባት በመሄዱ፣ ለተሻለ ምርመራና ህክምና ወደ አዳማ ሆስፒታል ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለመምጣት ተገዳለች።
በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ለተሰማና ለቤተሰቦቹ ትልቅ እፎይታ የሆነላቸው የጤና መድኅን አባልነታቸው ነው። ዲማ ለረጅም ጊዜ ስትታመም የቆየች ቢሆንም፣ የማህበረሰብ ዓቀፍ ጤና መድኅን አባል በመሆኗ የህክምና ወጪዋን በከፍተኛ ደረጃ እንደሸፈነላት ተሰማ በምስጋና ይናገራል። "
የጤና መድኅን ከገንዘብ ቁጠባ ባለፈ የህብረተሰቡን የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል የሚያጠናክር መሆኑን ተሰማ ያስረዳል። ይህ ሥርዓት ጤነኛው የታመመውን፣ ሀብታሙ ደሀውን የሚረዳበትና ወጪን በጋራ በማጋራት ሸክምን የሚያቀልበት የጋራ እሴት መሆኑን በኩራት ይገልጻል። ተሰማ ይህን ሲናገር በምክንያት ነው። ከዚህ ቀደም አባቱ በገጠማቸው የውስጥ የሆድ ህመም ምክንያት በዚሁ አግባብ ታክመው መዳናቸውን ያስታውሳል።
ወጣት ተሰማ የጤና መድኅንን ጠቀሜታ ቢያደንቅም፣ በስራ ላይ ያሉ ተግዳሮቶች ግን አገልግሎቱን ሙሉ እንዳያደርጉት ስጋቱን ይገልጻል። በተለይም በመጀመሪያ ደረጃ የህክምና መስጫ ማዕከላት (ጤና ጣቢያዎች) የሚታየው የመድኃኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች እጥረት ህብረተሰቡን ለእንግልትና ለተጨማሪ ወጪ እየዳረገው ይገኛል ወጣት ተሰማ ተናግሯል።
"አባል ሆነን ክርድ እያለን፣ ነገር ግን በጤና ተቋሙ ውስጥ መድኃኒትና መመርመሪያ መሳሪያ ባለመኖሩ ምክንያት ወደ ውጭ የግል ተቋማት ሄደን በውድ ዋጋ እንድንገዛ እንገደዳለን" የሚለው ተሰማ፣ ይህም ለድሃው ማህበረሰብ ትልቅ ሸክም መሆኑን ይገልጻል።
"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

የጤና መድህን አገልግሎት 'ነፍስ አድን' መሆኑን በተግባር ያረጋገጡት አቶ ስምኦን ቻሌ27/08/2018 ዓም ኢጤመአ"ጤና የታደሉት ሀብት ቢሆንም፣ ሕመም ደግሞ ለማንም የማይቀር የተፈጥሮ ሂደት...
05/05/2026

የጤና መድህን አገልግሎት 'ነፍስ አድን' መሆኑን በተግባር ያረጋገጡት አቶ ስምኦን ቻሌ
27/08/2018 ዓም ኢጤመአ
"ጤና የታደሉት ሀብት ቢሆንም፣ ሕመም ደግሞ ለማንም የማይቀር የተፈጥሮ ሂደት ነው። በተለይ በዕድሜ መግፋትና በሥራ ማቆም ወቅት የሚከሰቱ የጤና እክሎች የኢኮኖሚ አቅምን በእጅጉ ይፈታተናሉ። የ78 ዓመቱ አዛውንት አቶ ስምኦን ቻሌም ይህ ፈተና ከገጠማቸው ወገኖች አንዱ ቢሆኑም፣ የጤና መድህን አገልግሎት ግን የችግር ጊዜ ደራሽ ሆኖላቸዋል። የአቶ ስምኦንን ተሞክሮና ምክረ-ሀሳብ እንደሚከተለው ቀርቧል።"
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አካባቢ የሚኖሩት የ78 ዓመቱ አባት አቶ ስምኦን ቻሌ፣ የጤና መድህን አገልግሎት ለሳቸውና ለቤተሰባቸው ያለውን ፋይዳ እንዲህ ሲሉ በምስክርነት ገልጸዋል።
አቶ ስምኦን የጤና መድህን ተጠቃሚ የሆኑት በ2012 ዓ.ም ነው። ስድስት ልጆችን ወልደው ለቁምነገር ቢያበቁም፣ በአሁኑ ወቅት ግን ከአንዷ ልጃቸው በስተቀር አብሯቸው የሚኖር የለም። "ጉልበቴ በደከመበትና ሥራ ባቆምኩበት ወቅት የመጣው የጤና መድህን አገልግሎት ለኔ ትልቅ እፎይታ ነው" ይላሉ።
አቶ ስምኦን ስለ አገልግሎቱ ሲናገሩ፦ "እኔም ሆንኩ ቤተሰቦቼ በጤና መድህን ደብተራችን ነው እየታከምን ያለነው። በተለይ ለኔና ለባለቤቴ ያለው ጥቅም ተነግሮ አያልቅም። እኔ የደም ግፊት ታማሚ በመሆኔ ተከታታይ ሕክምና ያስፈልገኛል። አሁንም ሕይወቴን እያቆየ ያለው ይሄው አገልግሎት ነው። ይሄንን ሁሉ ሕክምና በክፍያ ቢሆን ኖሮ ምን ይውጠኝ ነበር?" በማለት የአገልግሎቱን አስፈላጊነት ያስረዳሉ።
እኝህ አባት አገልግሎቱ "ነፍስ አድን" መሆኑን ቢመሰክሩም፣ ለተጠቃሚው ምቾት ሲባል መስተካከል ያለበትን ክፍተት መጠቆም አረሱም። በተለይ በጤና ጣቢያዎች መድኃኒት በማይኖርበት ወቅት፣ ወደ ከነማ ፋርማሲዎች ሲሄዱ "የለም" የሚል ምላሽ እንደሚያጋጥማቸውና ይህም ለታካሚዎች ፈተና እየሆነ በመሆኑ የሚመለከተው አካል ሊያስብበት እንደሚገባ አሳስበዋል።
አቶ ስምኦን ቻሌ የጤና መድህን ለአረጋውያንና ለዝቅተኛው የኅብረተሰብ ክፍል ዋስትና መሆኑን በተግባር ያዩ ምስክር ናቸው። በመሆኑም ይህ መልካም እና ነፍስ አድን የሆነ አገልግሎት ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ሁሉም ዜጋ ተጠቃሚ እንዲሆን የበኩላቸውን ጥሪ አስተላልፈዋል።"Youtube: https://www.youtube.com/-HealthInsurance
Website: www.ehis.gov.et
Twitter: http://twitter.com/service4E
Facebook: https://web.facebook.com/EthioHIS/
Telegram: https://t.me/buuu1lTelegram: https://t.me/buu

X (formerly Twitter) (https://twitter.com/service4E)
Ethiopia Health Insurance Service () / X

Address

Nifase Silke Lafto Around Gotera Pepsi , GUAVA Building
Addis Ababa
21254/1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Health Insurance Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share