05/09/2026
ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 "መሰረታዊ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ፍጆታ ምርቶች በጥራት እና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማህበረሰባችን በማቅረብ ገበያን እናረጋጋለን" በሚል መሪ ቃል የ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የበዓል ገበያ በተከፈተ ባዛር ።
የበዓል ገበያው የነዋሪውን የኑሮ ጫና ለማቃለል እና የገበያ ዋጋ ንረትን ለማረጋጋት ያለመ ሲሆን፤ ይህም አስተዳደሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው ተግባራት አንዱ እና ተጠናክሮ የቀጠለ ውጤታማ ስራ ነው።
በተጨማሪም ህብረተሰቡ በአቅራቢያው የበዓል መጠቀሚያ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ የሚያስችል ሲሆን፤ ህብረተሰቡን ካላስፈላጊ ወጪ ለማዳን የገበያ ማዕከላት ጭምር የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በስፋትና በጥራት እየቀረቡ ይገኛሉ።
ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም