Federal Ethics and Anti-Corruption Commission

Federal Ethics and Anti-Corruption Commission Federal Ethics and Anti-Corruption Commission
(1)

የጥቆማመስመር ስልክ =0115533852 ወይም 0935947533
Youtube:https://www.youtube.com/channel/UCO_WiCAiDIkMMwqsZGK47nw/?guided_help_flow=5/
Twitter: https://twitter.com/EthiopiaFeacc
Facebook: https://www.facebook.com/feaccOfficial/
Telegram: https://t.me/feacc
Asset registration and Declaration: https://feaccdars.gov.et

በሀሰተኛ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለመገልገል የሞከሩ ግለሰቦች በፅኑ እስራት ተቀጡ***********************(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም) ‎በደቡብ ኢትዮጵያ ...
03/06/2026

በሀሰተኛ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለመገልገል የሞከሩ ግለሰቦች በፅኑ እስራት ተቀጡ

***********************

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም) ‎በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው የነበሩ ሁለት ግለሰቦች በጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጥተዋል፡፡

‎ተከሳሾቹ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት 1ኛ ተከሳሽ የ2ኛ ተከሳሽ ጠበቃ ሲሆን፣ 2ኛ ተከሳሽ ከአይናቴ ሎሪሶ ከተባለች ግለሰብ ጋር በነበረው የውርስ ክርክር ከክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 47413 በሆነው በቀን 12/06/16 ዓ.ም ለ2ኛ ተከሳሽ የተወሰነ በማስመሰል ሀሰተኛ የጠቅላይ ፍ/ቤት ማህተምና የጠቅላይ ፍ/ቤቱ ምክትል ፐሬዝዳንት ፊርማ ያልሆነውን በማሳረፍ ሀሰተኛ የውሳኔ ግልባጭ ለ2ኛ ተከሳሽ የሰጠ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽ የተዘጋጀውን ሐሰተኛ ውሳኔ እያወቀ በመገልገል የግል ተበዳይ አይናቴ ሎሪሶን የውርስ ክስ በመቃወም ለዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፍ/ቤት ያቀረበ በመሆኑ ሁሉም ተከሳሾች በፈጸሙት ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ላይ እንደነበሩ ተገልጿል፡፡

‎የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የክስ መዝገብ የመረመረው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሾቹን ጥፋተኛ ናቸው በማለት 2 አመት ከ9 ወር ጽኑ እስራት እና 1 ሺህ ብር እንዲቀጡ መወሰኑን ከዞኑ ፍትህ መምሪያ ፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት የሙስና ወንጀል የሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት****************ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት በተገልጋዩ ህብረተሰብ እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል ባለ ግ...
03/06/2026

ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት የሙስና ወንጀል የሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት

****************

ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት በተገልጋዩ ህብረተሰብ እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል ባለ ግንኙነት የሚፈጸም ተገቢነት የሌለው ተግባር ነው፡፡ ተገልጋዩ የህብረተሰብ ክፍል በህግ ክርክሮች እና በአስተዳደር አካላት የሚሰጡ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን ለማግኘት ወደ ተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ፊት ይቀርባሉ፡፡

በዚሁ ሁኔታ አገልግሎት ፈልጎ የቀረበው ተገልጋይ እንደ ጉዳዩ ባህሪ በህግ እና አሰራር በተቀመጠ ምክንያታዊ ጊዜ ውስጥ ለጉዳዩ እልባት አግኝቶ መሸኘት አለበት፡፡ ይህ የማይሆን ከሆነ ተገልጋዮችን ተገቢ ላልሆነ እንግልት በመዳረግ ጊዜያቸውን፣ ገንዘባቸውን እና ጉልበታቸውን እንዲያባክኑ በማድረግ፣ ለከፋ ምሬት እና ተስፋ በመቁረጥ በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሻክር ይሆናል፡፡

ያለአግባብ ጉዳይ ማጓተት በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 18 መሰረት ማንኛውም የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ኃላፊ ወይም ሠራተኛ በኃላፊነቱ በሥራው ምክንያት በቀረበለት ጉዳይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ጥቅም ለማግኘት ሲል በጉዳዩ ላይ ጥቅም ያለውን ማንኛውንም ሰው ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት በማሰብ ከህግ፣ ከመመሪያ ወይም ከተለመደው አሰራር ውጪ ያለበቂ ምክንያት ጉዳዩን ያልወሰነ፣ ያዘገየ ወይም ባለጉዳይን ያጉላላ እንደሆነ እንደ ጉዳዩ ታይቶ በገንዘብ ወይም በእስራት ይቀጣል፡፡

በአዋጁ እንደተደነገገው ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት የሙስና ወንጀል የሆነበትን መሠረታዊ ምክንያት ነው፡፡ በዚህም መሰረት የሙስና ወንጀሎች በመሰረታዊነት የሚፈጸሙት የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለአንዱ ወገን በተለያዩ ምክንያቶች በማዳላት ሌላውን ወገን ለመጥቀም በማሰብ ነው።

የዚህ ወንጀል ፈጻሚዎች ጉዳይን አለአግባብ የማጓተት ተግባር የሚፈጽሙት ባለጉዳዩ በመመላለስ ምክንያት ከሚደርስበት እንግልት ለማምለጥ ሲል ገንዘብ እንዲከፍላቸው ተጽእኖ ለማሳደር አልያም ባለጉዳዩ ተማሮ ጉዳዩን መከታተሉን እንዲተወው በማድረግ የባለጉዳዩን መብት ለመረጡት ሌላኛው ሰው በማስተላለፍ በዚህም የሚከፈላቸውን ተገቢ ያልሆነ የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ነው ማለት ይቻላል፡፡

የመንግስት መስሪያ ቤቶችም ሆኑ የልማት ድርጅቶች እንዲሁም የህዝባዊ ድርጅቶች ተገልጋዮቻቸውን ሲያስተናግዱ አገልግሎት ወይም ውሳኔ የሚሰጥበት ጉዳይ ያለውን ልዩ ባህሪ ግምት ውስጥ በማስገባት በህግ እና በአሠራር ሥርዓት እንዲሁም የተለመዱ አካባቢያዊ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ለተገልጋዮቻቸው በተገቢው ጊዜ ውሳኔ የመስጠት ግዴታ አለባቸው፡፡

ይህ ሳይሆን ቀርቶ ያለ በቂ ምክንያት ህግ እና አሰራርን በመጣስ ተገልጋዮችን ለማንገላታት እና ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት እንዲሁም አገልግሎት ጠያቂው ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ጉዳይን ያለበቂ ምክንያት ማጓተት በህግ የሚያስጠይቅ እና የሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል ተግባር መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡

ተገልጋዩ ማህበሰረብ በመንግስትም ይሁን ህዝባዊ ተቋማት አገልግሎት ለማግኘት ሲሄድ በህግ እና አሠራር ስርዓት የተቀመጡ የአሰራር ደረጃዎችን ተረድቶ በዛ ውስጥ ውሳኔ እንዲያገኝ መጠየቅ እና ይህ በማይሆንበት ጊዜ ጉዳዩን ያለ በቂ ምክንያት የሚያጓትቱ የመንግስት እና ህዝባዊ ድርጅት ሠራተኞች እና ኃላፊዎች ላይ የህግ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት በመጠቆም ተባባሪ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

የሙስና ስጋት ተጋላጭነትን አስቀድሞ በማጥናት ሙስናን መከላከል የተቋማት የዕለት ተዕለት ተግባር ሊሆን ይገባል!********************በተቋማት የሙስና ስጋት ተጋላጭነትን አስቀድሞ ማ...
02/06/2026

የሙስና ስጋት ተጋላጭነትን አስቀድሞ በማጥናት ሙስናን መከላከል የተቋማት የዕለት ተዕለት ተግባር ሊሆን ይገባል!

********************

በተቋማት የሙስና ስጋት ተጋላጭነትን አስቀድሞ ማጥናት ሙስናን ለመከላከል ውጤታማ መንገድ ነው። ተቋማት አገልግሎት የሚሰጡባቸው አዋጆች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች እና የዕለት ተዕለት የሥራ ሂደቶች ለሙስና ክፍተት የሚፈጥሩ መሆናቸውን አስቀድሞ ማጥናት ያስፈልጋል።

በተቋማት ውሳኔ የሚሰጥበት ተደራራቢ ኃላፊነት በአንድ ግለሰብ እጅ መከማቸት፣ ግልጽነት ማነስ እና የተጠያቂነት ሥርዓት መላላት ለሙስና ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። እነዚህን አስቀድሞ በጥናት ክፍተቶችን መለየት ለችግሩ መፍትሔ ለመስጠት የመጀመሪያው እርምጃ ነው።

ተቋማት አሠራራቸውን፣ የፋይናንስ እንቅስቃሴያቸውን እና የሰው ኃይል አስተዳደራቸውን የሚከታተሉበት ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት በየጊዜው መተግበር አለባቸው።

አንድ ተቋም የአሠራር ክፍተቶቹን እያጠና የሚያስተካክል ከሆነ፣ ደንበኞች ፍትሐዊና ፈጣን አገልግሎት ያገኛሉ፤ ይህም በተቋሙ ላይ ያለውን አመኔታ ይጨምራል። እንዲሁም ሙስና በሀገርና በተቋም ደረጃ የሚያስከትለውን ከፍተኛ የኢኮኖሚና የንብረት ብክነት አስቀድሞ ያስቀራል።

ሙስናን መከላከል በአንድ ወቅት ዘመቻ ብቻ ተደርጎ የሚያልቅ ወይም አልፎ አልፎ የሚከናወን ተግባር መሆን የለበትም። እያንዳንዱ የመንግሥትም ሆነ የግል ተቋም በየቀኑ በሚያከናውነው ተግባር ውስጥ የንቅናቄው አካል መሆን አለበት። ከአመራሩ ጀምሮ እስከ ታችኛው ፈጻሚ ባለሙያ ድረስ ታማኝነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት የሥራ ባህል መሆን ይኖርበታል።

ስለሆነም፣ ሙስና ከተፈጸመ በኋላ በሕግ ለመጠየቅ ከሚደረገው ጥረት ይልቅ፣ ተቋማት የአሠራር ሥርዓቶቻቸውን በየጊዜው በመፈተሽ ክፍተቶችን መዝጋት ይኖርባቸዋል። ሙስናን መከላከል የትርፍ ጊዜ ሥራ ሳይሆን የተቋማት የህልውና እና የዕለት ተዕለት የሥራ ስምሪት መሆን አለበት።

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

በርካታ የመንግስት ሠራተኞች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ **************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም) የሳዑዲ አረቢያ የተቆጣጣሪ እና የፀረ-ሙስና ባለስልጣን ...
02/06/2026

በርካታ የመንግስት ሠራተኞች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ

****************

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም) የሳዑዲ አረቢያ የተቆጣጣሪ እና የፀረ-ሙስና ባለስልጣን (ናዛሃ) ባለፈው ግንቦት ወር በሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው 160 የመንግስት ሰራተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል።

በቁጥጥር ስር የዋሉት ክትትሎችን በማድረግ፣ የተጠረጠሩባቸውን ጉዳዮችን በማጣራት እና በርካታ የወንጀል እና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን መጣሳቸውን ተከትሎ ነው።

ባለፈው ወር ናዛሃ በሀጅ ሰሞን በቅዱሳን እና የአገልግሎት መስጫ ቦታዎች ከ15 ሺህ ከሚጠጉ ክትትሎች በተጨማሪ በመንግስት መስሪያቤቶች 2,365 ሠራተኞች ላይ ክትትሎችን አድርጓል።

ከእነዚህ ክትትሎች በ480 ሠራተኞች ላይ በተጠረጠሩባቸው ጉዳዮች ላይ ምርመራ ከተደረገባቸው መካከል 160 የሚሆኑት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል የማዘጋጃ ቤትና ቤቶች ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና የእስልምና ጉዳዮች የጥሪ እና መመሪያ ሚኒስቴር እንዲሁም የዘካት፣ የታክስ እና ጉምሩክ ባለስልጣን ሰራተኞች ይገኙበታል ተብሏል።

የተከሰሱባቸው ወንጀሎችም ጉቦ እና የመንግስት የሥራ ቦታዎችን አላግባብ መጠቀምን ያጠቃልላል ሲል ሳውዲ ጋዜጣ ዘግቧል።

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

መልካም ሥነምግባር ያለው መራጭ ለሀገሩ ዘላቂ ሰላም፣ ለፍትሕ መረጋገጥ እና ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ መሠረት የሚጥል ንቁ ዜጋ ነው!*****************​የአንድን ሀገር እድገት የሚያሳ...
31/05/2026

መልካም ሥነምግባር ያለው መራጭ ለሀገሩ ዘላቂ ሰላም፣ ለፍትሕ መረጋገጥ እና ለጠንካራ ተቋማት ግንባታ መሠረት የሚጥል ንቁ ዜጋ ነው!

*****************

​የአንድን ሀገር እድገት የሚያሳድገውና ወደ ብልፅግና የሚያሸጋግረው በዕውቀት፣ በኃላፊነት ስሜት እና በበሰለ የሞራል እሴት የሚመራ ንቁ ዜጋ ሲኖር ነው።

በአንድ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ የመራጩ ሕዝብ ንቃተ ሕሊና እና የሥነምግባር ደረጃ የሂደቱን ስኬታማነት የሚወስን ዋነኛ ምሰሶ ነው። መራጮች መልካም ሥነምግባርን ተላብሰው ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ሲወጡ የሚከተሉትን ጥቅሞች ይኖሩታል።

​👉 የሕዝብ እውነተኛ ፍላጎት ይንጸባረቃል፦ መራጩ ሕዝብ ከጥቅማ ጥቅም፣ ከዘር ወይም ከማስፈራራት ነፃ ሆኖ በራሱ ሕሊና እና በፓርቲዎች አማራጭ የፖሊሲ ሃሳብ ላይ ብቻ ተመስርቶ ድምፁን ሲሰጥ፣ እውነተኛ የሕዝብ ውክልና ያለው መንግስት ይቋቋማል።

​👉 ሰላማዊና ሥርዓታዊ ሂደት ይኖራል፦ ሥነምግባር ያለው መራጭ የሌሎችን የመምረጥና የመመረጥ መብት ያከብራል፤ የሐሳብ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ያስተናግዳል። ይህም በምርጫ ወቅትና ከምርጫ በኋላ ሊነሱ የሚችሉ አላስፈላጊ ጉዳዮችን ያስቀራል።

​👉 ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓት ይገነባል፦ መራጮች ድምጻቸውን በጥንቃቄና በኃላፊነት ስሜት ሲሰጡ፣ ተመራጭ ፓርቲዎችም ቢሆኑ ለሕዝብ ቃል የገቡትን ተግባራዊ ለማድረግና በቅንነት ለማገልገል ይገደዳሉ።

​በመሆኑም፣ እያንዳንዱ ዜጋ ወደ ምርጫ ጣቢያ ሲያቀና፣ የሚሰጣት አንዲት ድምፅ የሀገርን የወደፊት ዕጣ ፈንታ፣ ሰላምና ልማት የመወሰን ታላቅ አቅም እንዳላት ማመን አለበት። ይህንን ኃላፊነት በሰላማዊ፣ በታማኝ እና በበሰለ ሥነምግባር መወጣት የሁሉም ዜጋ ቀዳሚ ተግባር ሊሆን ይገባል።

!

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

የተቀናጀ የሙስና መከላከል ስልቶች ********************ሙስናን በአንድ ተቋም ወይም በቅጣት ብቻ ከመዋጋት ይልቅ፣ ችግሩን ከመሰረቱ ለመቅረፍ የተለያዩ እርስ በእርስ የሚደጋገፉ አካ...
30/05/2026

የተቀናጀ የሙስና መከላከል ስልቶች

********************

ሙስናን በአንድ ተቋም ወይም በቅጣት ብቻ ከመዋጋት ይልቅ፣ ችግሩን ከመሰረቱ ለመቅረፍ የተለያዩ እርስ በእርስ የሚደጋገፉ አካሄዶችን አቀናጅቶ መተግበር ላይ ማተኮር ይገባል፡፡ ይህ ስልት በዋናነት በሥነምግባር ግንባታ፣ በሙስና መከላከል እና በህግ ተፈጻሚነት (እርምጃ) ምሰሶዎች ላይ የሚቆም ነው። በዚህም የተቀናጁ የሙስና መከላከል ዋና ዋና ስልቶች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

​✍ የህዝብ ግንዛቤን ማሳደግ እና የሥነ-ምግባር ግንባታ፡- ሙስናን በዘላቂነት ለመከላከል ማህበረሰቡ በሙስና አስከፊነትና በሥነ-ምግባር ላይ ያለው እውቀትና አመለካከት መቀየር አለበት። የሥነ-ምግባር ትምህርት ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ድረስ በስርዓተ-ትምህርት ውስጥ በማካተት ታማኝ፣ ቅን እና መልካም ሥነ-ምግባር ያለው ትውልድ መገንባት ይገባል፡፡

ሙስናን ለመከላከል የንቅናቄና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻዎችን በሚዲያ፣ በማህበራዊ ሚዲያዎች እና በህዝባዊ መድረኮች አማካኝነት የሙስናን ጎጂነት እና አስከፊነት ለህዝብ ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡

​✍ በተቋማት ግልጽነትና ተጠያቂነት ማስፈን፡- ሙስና የሚከሰተው አሰራሮች ግልጽ ካለመሆነና ለግል ውሳኔ ሰፊ እድል በሚሰጥበት ወቅት ነው። ግልጽነትና ተጠያቂነት የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶችን፣ የበጀት አጠቃቀምን እና የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥን ለህዝብ ክፍት በማድረግ ሙስናን መከላከል ይገባል።

​✍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ፡- የአገልግሎት አሰጣጥን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማስደገፍ ከሰው እጅ ንክኪ በመቀነስ ጉቦ የመጠየቅና የመስጠት እድሎችን ማጥበብ ያስፈልጋል።

​✍ የህግ ማዕቀፎችን ማጠናከር፡- የአገር ውስጥ እና ዓለምአቀፍ የህግ ማዕቀፎችን በማጣጣም የሙስና መከላከያ ህጎችን ማክበር እና ማስከበር ይገባል። የህግ ማሻሻያዎች የፀረ-ሙስና አዋጆችንና ደንቦችን ከወቅታዊ የሙስና ውስብስብ ባህሪ ጋር አብሮ እንዲሄድ ያስችላሉ።

​✍ ዓለምአቀፍ ስምምነቶችን መተግበር፦ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀረ-ሙስና ኮንቬንሽን (UNCAC) እና የአፍሪካ ህብረት የሙስና መከላከልና መዋጋት ኮንቬንሽን (AUCPCC) እና ሌሎች የስምምነት መርሆች በአገር ውስጥ ህጎችና አሰራሮች ውስጥ ማካተት ሙስናን በተቀናጀ መልኩ ለመከላከል ከሚግዙ ስልቶች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።

​✍ የባለድርሻ አካላት ቅንጅትና ተሳትፎን ማሳደግ፡- ሙስናን በአንድ ተቋም ብቻ መከላከል ስለማይቻል የተቀናጀ አቀራረብ የሁሉንም አካላት ተሳትፎ ይጠይቃል። ዘርፋ በግልጽነትና በፍትሀዊ ውድድር ላይ የተመሰረተ እንዲሆን መደገፍ እና የሲቪል ማህበራት በክትትል ስራዎች ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ ያስፈልጋል።

በአጠቃላይ፣ የተቀናጀ የሙስና መከላከል ስልት ስኬታማ የሚሆነው ተቋማትና ባለድርሻ አካላት በተናጠል ሳይሆን በቅንጅትና ትብብር ሙስናን መታገል ሲችሉ ብቻ ነው። ስለሆነም፣ ሙስናን በመታገል ሀገራችን በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካና ማህበራዊ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ውጤታማ የማድረግ ኃላፊነታችን መወጣት ይጠበቅብናል።

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

በሙስና ወንጀል የተከሰሱ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ ******************** (ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም) በአማራ ክልል በደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር የአብማ ክፍለ ...
29/05/2026

በሙስና ወንጀል የተከሰሱ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ

********************

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም) በአማራ ክልል በደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር የአብማ ክፍለ ከተማ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ከመሬት ጋር በተያያዘ ሙያቸውንና ስልጣናቸውን ተጠቅመው በፈጸሙት የሙስና ወንጀል 10 ተከሳሾች በእስራት ተቀጥተዋል፡፡

ተከሳሾች፣ የሰነድ አልባ መረጃን በማጽናት እና በማጽደቅ ሂደት የመንግስትን መሬት ለሌላ ግለሰብ አሳልፈው በመስጠት በፈፀሙት የሙስና ወንጀል በቁጥጥር ስር ውለው አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት መዝገቡን ለምስራቅ ጎጃም ዞን አቃቢ ህግ መምሪያ መላክ መቻሉን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ የሙስና ወንጅሎች ምርመራ ዋና ክፍል ሃላፊ ኮማንደር ጌታነህ አሰፋ ገልጸዋል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን አቃቢ ህግ መምሪያ ከፖሊስ የደረሰውን የምርመራ መዝገብ በማደራጀትና ክስ በመመስረት በህግ አግባብ ሲታይ ከቆየ በኋላ የምስራቅ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀን በ19/9/2018 ዓ,ም በዋለው ችሎት ተከሳሾች ጥፋተኛ መሆናቸው በሰውና በሰነድ ማስረጃ ተረጋግጧል፡፡

በዚህም 1ኛ አቶ አላምር ተስፋዬ፣ 2ኛ ወ/ሮ ሀይማኖት ታሪኩ፣ 3ኛ አቶ መኳንንት ጠለለ፣ 4ኛ አቶ እንዳልካቸው፣ 5ኛ አቶ ተሻለ መብራቴ፣ 6ኛ አቶ ዮሴፍ ጌትነት እና 7ኛ አቶ ስላንተ ጥበቡ እያንዳንዳቸው በሁለት መዝገብ በ10 አመት እስራት ተቀጥተዋል፡፡

8ኛ ወ/ሮ ታሪክ ሞትባይኖር በተለዬ መንገድ ከግለሰቦች ጋር በመመሳጠር የቴክኒክ ኮሚቴውንና የአብይ ኮሚቴውን በማሳመን ለግለሰቦች መብት ከመፍጠር ባሻገር በራሷ ልጆች ስም የመንግስትን መሬት በማዘወር መብት የፈጠረች መሆኑን በማስረጃ በመረጋገጡ በሁለት መዝገብ በ12 አመት እንዲሁም ወ/ሮ ሶሊያና መሀሪና ወ/ሮ አብዮት እጅጉ እያንዳንዳቸው በ3 አመት እስራት መቀጣታቸውን ገልጸዋል።

የሙስና ወንጀል የመልካም አስተዳደር ችግር ከመፍጠሩም በላይ በሀገር ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮችን በማስከተል በህዝብ እና በመንግስት መካከል መተማመን እና ተቀራርበው እንዳይሰሩ የሚያደርግ መጥፎ በሽታ በመሆኑ ማንኛውም ህብረተሰብ የሙስና ወንጀል ሊፈፀም መሆኑን ሲያውቅ ወይም ሲመለከት ጥቆማ በመስጠት እና ለህግ ተባባሪ በመሆን የዜግነት ድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባ ማሳሰባቸውን ከከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ የፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

29/05/2026

ህግን በማክበር ሙስናን እንከላከል!

********************

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

በቅንነትና በታማኝነት መስራት፣ ለሀገር ዕድገት የሚከፈል ታላቅ ግብር ነው!********************ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ለዜጎች የጋራ ብልጽግና መሠረቱ የገንዘብ ግብር ብ...
28/05/2026

በቅንነትና በታማኝነት መስራት፣ ለሀገር ዕድገት የሚከፈል ታላቅ ግብር ነው!

********************

ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገትና ለዜጎች የጋራ ብልጽግና መሠረቱ የገንዘብ ግብር ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱ ዜጋ በተሰማራበት የሥራ መስክ የሚያሳይበት የሞራልና የሙያ ግብር ጭምር ነው።

​የሀገር ግንባታ የሚጀምረው ከግል ማንነታችንና ከዕለት ተዕለት ተግባራችን ነው። የምንከፍለው የገንዘብ ግብር መሠረተ-ልማትን እንደሚገነባው ሁሉ፣ በቅንነትና በታማኝነት የምናበረክተው አገልግሎት ደግሞ የሀገርን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሠረት ያጠናክራል።

​በሥራችን የምናሳየው እውነተኛነት፣ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን በማስወገድ ተቋማዊ አሠራራችን በሕግና በሥርዓት ላይ እንዲገነባ ያደርጋል። ታማኝነትና ቅንነት ምርጫ ሳይሆን፣ ለትውልድ የሚተርፍ አሻራ የምናስቀምጥበትና ለሀገር ዕድገት የምንከፍለው ትልቁ የዜግነት ግብራችን ነው።

​የአንድ ሀገር ዕድገትና ስልጣኔ የሚለካው በሕንጻዎቿ መርዘም ብቻ ሳይሆን፣ በተቋሞቿና በዜጎቿ የሞራል ልዕልና ጭምር ነው። ቅንነትና ታማኝነት በሌለበት አካባቢ ፍትሕ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት ሊሰፍኑ አይችሉም።

ሥራን በቅንነት መስራት ማለት የተሰጠንን ኃላፊነት ያለ አድሎ ግልጽ በሆነ አሰራርና ለሕዝብ ጥቅም ቅድሚያ በመስጠት መወጣት ነው።

​ታማኝነት ባሕል በሆነበት ተቋም ውስጥ ለብልሹ አሠራርና ለግል ጥቅም ማሳደጃ የሚሆን ቀዳዳ አይኖርም፤ ይህ ደግሞ ተቋማዊ ግልጽነትንና የሕዝብ አመኔታን ይገነባል።

በታማኝነት የምናፈስሰው እያንዳንዱ ጠብታ ላብ፣ ለሀገራችን ዘላቂ ዕድገት የምናበረክተው ታላቅ ስጦታ ነው። ዛሬ የምንዘራው የሥነምግባር እሴት፣ ነገ ጠንካራ ተቋምና የበለጸገች ሀገር እንድትገነባ ያደርጋል።

​ስለሆነም፣ እያንዳንዱ ተቋም በሥርዓት እንዲመራና እያንዳንዱ ዜጋም በሥነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ እንዲገነባ የድርሻችንን በመወጣት፣ ቅንነትና ታማኝነትን የሥራችን መመሪያ በማድረግ የሀገራችንን የዕድገት ጉዞ ማፋጠን ይኖርብናል።

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!***********************​የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል የታ...
27/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

***********************

የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል የታላቅ መስዋዕትነት፣ የታማኝነት፣ ለፈጣሪ የመታዘዝ እና የጽናት መገለጫ ነው። ይህ ታላቅ በዓል ለራስ ብቻ ከመኖር ይልቅ ለሕዝብና ለሃገር መልካምን ማሰብን፣ ፍትሃዊነትን እና እውነትን ያስተምረናል።

​እውነተኛ የሥነ-ምግባር ግንባታ የሚጀምረው ራስን ለታማኝነትና ለቅንነት አሳልፎ በመስጠት ነው። ታማኝነት ባለበት ደግሞ ሙስና እና ብልሹ አሠራሮች ቦታ የላቸውም።

​በዚህ በተቀደሰ ዕለት፣ የተጣለብንን ኃላፊነት በቅንነትና በንጽህና በመወጣት፣ የሌሎችን መብት ባለመንካትና የሕዝብን አደራ በመጠበቅ እና ሙስናንና ብልሹ አሠራርን በመጸየፍና በመከላከል የበዓሉን መንፈሳዊ እሴቶች በተግባር ማሳየት ይገባል።

ስለሆነም ፍቅርን፣ አንድነትን እና መልካም ሥነ-ምግባርን በማስፈን ሃገራችንን ከሙስና የፀዳች እና በልማት የጸናች ማድረግ ይኖርብናል።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆን የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ይመኛል።

ኢድ-ሙባረክ !

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

Address

Addis Ababa
KAZANCHES

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Federal Ethics and Anti-Corruption Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share