03/06/2026
በሀሰተኛ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለመገልገል የሞከሩ ግለሰቦች በፅኑ እስራት ተቀጡ
***********************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 26/2018 ዓ.ም) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን በሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው የነበሩ ሁለት ግለሰቦች በጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጥተዋል፡፡
ተከሳሾቹ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት 1ኛ ተከሳሽ የ2ኛ ተከሳሽ ጠበቃ ሲሆን፣ 2ኛ ተከሳሽ ከአይናቴ ሎሪሶ ከተባለች ግለሰብ ጋር በነበረው የውርስ ክርክር ከክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 47413 በሆነው በቀን 12/06/16 ዓ.ም ለ2ኛ ተከሳሽ የተወሰነ በማስመሰል ሀሰተኛ የጠቅላይ ፍ/ቤት ማህተምና የጠቅላይ ፍ/ቤቱ ምክትል ፐሬዝዳንት ፊርማ ያልሆነውን በማሳረፍ ሀሰተኛ የውሳኔ ግልባጭ ለ2ኛ ተከሳሽ የሰጠ መሆኑ ተመላክቷል፡፡
እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽ የተዘጋጀውን ሐሰተኛ ውሳኔ እያወቀ በመገልገል የግል ተበዳይ አይናቴ ሎሪሶን የውርስ ክስ በመቃወም ለዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፍ/ቤት ያቀረበ በመሆኑ ሁሉም ተከሳሾች በፈጸሙት ሀሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ላይ እንደነበሩ ተገልጿል፡፡
የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የክስ መዝገብ የመረመረው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሾቹን ጥፋተኛ ናቸው በማለት 2 አመት ከ9 ወር ጽኑ እስራት እና 1 ሺህ ብር እንዲቀጡ መወሰኑን ከዞኑ ፍትህ መምሪያ ፌስቡክ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!
የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾
ሞባይል መተግበሪያ
ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...
or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231
ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/
ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/
ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149
ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።