Insurance Fund Administration Agency

Insurance Fund Administration Agency The FDRE Proclamation No. 799/2013 introduced Vehicle Insurance Against Third Party Risks. This is t

The Federal Democratic Republic of Ethiopian Proclamation No. 559/2008 has introduced Vehicle Insurance Against Third Party Risks, which requires owner of vehicle to have a minimum third party motor insurance that provides compensation to victims of road traffic accidents. Article 19 and Article 21 of the Proclamation provide the establishment of Insurance Fund and Insurance Fund Administration (

IFAA) to undertake among other things compensation to victims of Uninsured and Untraced vehicles and also guarantee that all road accident victims receive Emergency Medical Treatment. Accordingly, the Ethiopian Insurance Fund Administration (IFAA) was instituted in 2008 taking these responsibilities and to overview the effective implementation, monitoring and review the provisions of the Proclamation on the ground.

ትዉልዱ ዛሬም በአረንጓዴ አሻራው ታሪክ እየሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡የመንገድ ደህንነት እና የመድን ፈንድ አገልግሎት አመራር እና ሰራተኞች 4ተኛው ዙር የአርንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን በምስራቅ ሸ...
07/07/2022

ትዉልዱ ዛሬም በአረንጓዴ አሻራው ታሪክ እየሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡
የመንገድ ደህንነት እና የመድን ፈንድ አገልግሎት አመራር እና ሰራተኞች 4ተኛው ዙር የአርንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ በ29/10/2014 ዓ.ም የችግኝ ተከላ አካሂደዋል ፡፡
የችግኝ ተከላውን መርሃ ግብር በይፋ ያስጀመሩት የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አባሶ ሲሆኑ በንግግራቸው እንደገለፁት የሀገር ግንባታው የትውልድ ቅብብሎሽ እንደሆነ ሁሉ ይህም ትውልድ አራተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በመሳተፍ በሀገር ግንባታው የድርሻውን እያበረከተ ታሪክም እየሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል ፡፡
በዕለቱ መርሃ ግብር 2000 ችግኞች ተተክለዋል፡፡ በቀጣይ በጋ ወራት የመኮትኮት የመንከባከብና ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ በዕለቱ የትራንስፖርት ሎጅስቲክ ሚንስቴርና ተጠሪ ተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች የአመቱን የመጀመሪያ ዙር የችግኝ ተከላ አካሂደዋል፡፡ በቀጣይ ሀምሌ 06/ 2014 ዓም 100,000 (መቶ ሺ) ችግኞችን እንደሚተከሉ በዕለቱ የተገኙ ሚንስቴር ዴታዎች ገልፀዋል ፡፡

በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚወጡ  እስትራቴጂዎች፣ ፖሊሲዎች፣ ህጎች እና ደንቦች የተሸከርካሪ አደጋን ለመቀነስ የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወጡ ተገለፀ፡፡የመንገድ ደህንነትና የመድን ፈንድ አገልግሎት...
13/06/2022

በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚወጡ እስትራቴጂዎች፣ ፖሊሲዎች፣ ህጎች እና ደንቦች የተሸከርካሪ አደጋን ለመቀነስ የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወጡ ተገለፀ፡፡
የመንገድ ደህንነትና የመድን ፈንድ አገልግሎት በደንብ ቁጥር 493/2014 በተሰጠውን ስልጣንና ተግባር እና አለማቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ህጎች ላይ በካፒታል ሆቴል በ6/10/20141 ዓ.ም ከባለድርሻ አካላት ጋር ወርክሾፕ አካሂዶል፡፡
በዕለቱን ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመንገድ ደህንነትና የመድን ፈንድ አገልግሎት የኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ አዲል አብዱላሂ አንደገለፁት አገልግሎቱ የተሰጠውን ስልጣንና ተግባር የማስተዋወቅ፣ የመንገድ ትራፊክ ደህንንነት ህጎችን የማስፈፀም እና በአለም አቀፍ ደረጃ የወጡና ሀገራችን የተስማማችበትን የመንገድ ደህንነትና የመድን ፈንድን የሚመለከቱ ስምምነቶች መተግበርና አፈፃፀማቸውን መከታታል ለመቤቱ ከተሰጡት ስልጣን ውስጥ እንደሚጠቀስ በንግግራቸው ገልፀዋል፡፡
በወርክሾፑ ላይ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ ማቋቋሚያ በድንብ ቁጥር 493/2014 የተሰጡትን ስልጣንና ተግባራት በአቶ ዮናስ በለጠ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን ከዚህም ጋር በተያያዘ የብሉምበርግ ኢንሼቲቭ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ዮሃንስ ለገሰ የመንገድ ደህንነት አለማቀፍ ተሞክሮዎችን በህግ አተገባበር ላይ ያሉ ክፍተቶችን እና የአደጋ መንስኤ አቅርበዋል፡፡ እንደ ሃገርም በዘርፉ በተለያያ ጊዜ የመንገድ ደህንነት የህግ መእቀፎችን ለማሻሻል በወጣው የትራፊክ ደንብ ቁጥር 208/2011 ላይ ያሉትን የትርጉም ክፍተቶችን በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተደርበታል፡፡
በመጨረሻም በቀረበው ሰነድ ላይ ከተሳተፊዎች በተነሱ ጥያቄዎች ውይይት ተደርጓል፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ የአለም አቀፍ የህግ ማስከበር ሰኬትና ተሞክሮዎች ቀርበው በሃገር ደረጃ በየጊዜው ለሚደርሱ አደጋዎች የመጀመሪያው ክፍተት ህግን ማስከበር ላይ እንደሆነና በዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶች ላይ ትኩርት እንዲሰጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለመንገድ ትራፊክ አደጋ መቀነስ የድሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ ተደርጎ የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡

የመንገድ ደህንነት እና የመድን ፈንድ አገልግሎት ከባለድርሻ አካላት  ጋር የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች የአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት  አሰጣጥ  እና የፈንድ አጠቃቀም ላይ የዘጠኝ ወራት እቅድ...
13/06/2022

የመንገድ ደህንነት እና የመድን ፈንድ አገልግሎት ከባለድርሻ አካላት ጋር የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች የአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት
አሰጣጥ እና የፈንድ አጠቃቀም ላይ የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡
የመንገድ ደህነንት እና የመድን ፈንድ አገልግሎት ፣የጤና ሚንስቴር፣የፌዴራል ፖሊስ ፣የክልል ፓሊስ ኮሚሽኖች፣የክልል ጤና ቢሮዎች እና የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የጤና እና የፓሊስ ቢሮዎች የዘጠኝ ወራት የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች የአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ እና የፈንድ አጠቃቀም ላይ በአዳማ ከተማ ከረዮ ሆቴል በ4/10/2014 ዓ/ም ተገመገመ፡፡
በእለቱ ፕሮግራም ላይ እንኳን ደህና መጣችሁ እና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመንገድ ደህንነት እና የመድን ፈንድ አገልግሎት ኦፕሬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አዲል አብዱላሂ ሲሆኑ በንግግራቸውም የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች የአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ በሆነ እና በተገቢው ሰዓት አገልግሎቱን በመስጠት የሰውን ህይወት ከሞት መታደግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ከመቅረፍም በተጨማሪ ከሞራል አንፃር እንደ ዜጋ ማህበራዊ ሀላፊነት መወጣት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ሁሉም ክልሎች የተሽከርካሪ አደጋ የአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት አፈፃፀማቸውና ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር እና የነበሯቸዉን ጠንካራና ደካማ ጎኖች የያዘ አፈፃፀም በሪፖርታቸው ላይ በማካተት አቅርበዋል ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በክልሎች እና በሁለቱ የከተማ አስተዳደር በደረሱ አደጋዎች የሞት፣ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳቶች እና የንብረት ውድመትን በዝርዝር አንስተዋል፡፡
በመጨረሻም በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ውይይት ተደርጎ በርካታ ሀሳቦች ተነስተው ከጤና ሚንስቴር እና ከመንገድ ደህንነት እና መድን ፈንድ አገልግሎት ምላሽ ተሰቶባቸዉ የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል ፡፡

20/05/2022
17/05/2022

የመንገድ ደህንነት ማስጠበቅ የቁጥጥር ዘመቻ

14/04/2022
ብሔራዊ የመንገድ ደህንነት ቴክኒካል የስራ ቡድን የምስረታ ፕሮግራም በአዳማ ከተማ መጋቢት 15/01/2014 ዓ.ም ተካሄደ……………………………… …………………………. ……………………. የመንገድ ደህን...
25/03/2022

ብሔራዊ የመንገድ ደህንነት ቴክኒካል የስራ ቡድን የምስረታ ፕሮግራም በአዳማ ከተማ መጋቢት 15/01/2014 ዓ.ም ተካሄደ
……………………………… …………………………. …………………….
የመንገድ ደህንነት ቴክኒካል የስራ ቡድን ምስረታን አስመልክቶም የተከበሩ አቶ ጀማል አባሶ የመንገድ ደህንነት እና የመድን ፈንድ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እና በኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ኢንድራጂት ሀዛሪካ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን
አቶ ጀማሉ አባሶ በንግግራቸውም ለአንድ ሀገር ሁለተናዊ ዕድገት የመንገድ ትራንሰፖርት እየተጫወተ ያለው ሚና የላቀ መሆኑን ያነሱ ሲሆን ይህ ዘርፍ ከዚህም በላይ ድርሻው የጎላ እንዳይሆን የመንገድት ትራፊክ አደጋ በዜጎች እና በሀገር ሁለተናዊ እድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳረፈ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በመሆኑም የመንገድ ትራፊክ አደጋን ለማሰፈን የሁሉንመ አካላት ርዕብርብ የሚሻ በአንድ ተቋም ብቻ የሚሰራ ባለመሆኑ ብሔራዊ የመንገድ ደህንነት ቴክኒካል የስራ ቡድን ማቋቋሙ ግድ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በጋራ ዕቅድ ለማቀድ ተቀራርቦ ለመስራት እና የነቃ ተሳትፎን ለማጠናከር እንዲሁም የመንገድ ደህንነት ተግባራትን ለማሻሻል የባለሙያዎች ስብስብ መኖሩ ድርሻው የላቀ መሆኑንም አውስተዋል፡፡
በመጨረሻም የተቋቋመው ብሔራዊ የመንገድ ደህንነት ቴክኒካል የስራ ቡድን ቁልፍ የሆኑ ሴክተሮችን ለማስተባበርና የመንገድ ደህንነትን ለማሻሻል እንዲሁም በሰዎች ላይ የሚደርሰውን ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ለመቀነስ የላቀ ሚና እንዳለው ጠቅሰው ለዚህ ቴክኒካ ቡድን ምስረታ መሳካት የድርሻቸውን የተወጡ አካላትን አመስግነው ለብሔራዊ የመንገድ ደህንነት ቴክኒካል የስራ ቡድን መልካም የስራ ጊዜ ይኖራቸው ዘንድ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

አሉታዊ መጤ ባህሎች በወጣቶች ስብዕና ላይ በሚያስከትለው ተፅዕኖ ለተቋሙ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።------------------- ------- ------ --------የመንገድ ደህንነትና መድን...
23/03/2022

አሉታዊ መጤ ባህሎች በወጣቶች ስብዕና ላይ በሚያስከትለው ተፅዕኖ ለተቋሙ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።
------------------- ------- ------ --------
የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት በሴቶችና ህፃናት ዳይሬክቶሬት አሉታዊናመጤ ባህሎችና አደንዛዥ ዕፆች በወጣቶች ሰብዕና ላይ በሚያስከትለው ተፅዕኖ ዙሪያ መጋቢት 13 ቀን 2014 ዓ.ም በዲባቤ ሆቴል ስልጠና ተሰጠ።

የዕለቱ ፕሮግራም በማስመልከት የተቋሙ የሴቶችና ህፃናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት አያሌው የመክፈቻ ንግግር በማድረግ እንኳን ለማርች 8 አደረሳቹህ ብለዋል። ወ/ሮ መሰረት አያሌው በንግግራቸው የወጣቶች ስብዕና ለመገንባት ተቋማችን ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት ለመስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስተር የወጣቶች ስብዕና ባለሙያ አቶ ኑረዲን ሽኩሪ ባቀረቡት ሰነድ ላይ እንደገለፁት አደንዛዥ ዕፆች የሚያስከትሉት ማህበራዊ ቀውስ እንዲሁም የጤና ጉዳት ምርታማነትን በመቀነስ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ጫና ውስጥ ስለሚከት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ከሚኒስተር መስሪያቤቱ ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።
በመጨረሻም ማርች 8 በማስመልከት እና ተሽከርካሪና ሴቶች በሚሉ ርዕሶች ዙሪያ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

Address

Kazanchis Elily International Hotel Building 2 (3rd & 4th Floor)
Addis Ababa
1288

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Insurance Fund Administration Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Insurance Fund Administration Agency:

Share