07/07/2022
ትዉልዱ ዛሬም በአረንጓዴ አሻራው ታሪክ እየሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡
የመንገድ ደህንነት እና የመድን ፈንድ አገልግሎት አመራር እና ሰራተኞች 4ተኛው ዙር የአርንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርን በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ በ29/10/2014 ዓ.ም የችግኝ ተከላ አካሂደዋል ፡፡
የችግኝ ተከላውን መርሃ ግብር በይፋ ያስጀመሩት የአገልግሎቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አባሶ ሲሆኑ በንግግራቸው እንደገለፁት የሀገር ግንባታው የትውልድ ቅብብሎሽ እንደሆነ ሁሉ ይህም ትውልድ አራተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በመሳተፍ በሀገር ግንባታው የድርሻውን እያበረከተ ታሪክም እየሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል ፡፡
በዕለቱ መርሃ ግብር 2000 ችግኞች ተተክለዋል፡፡ በቀጣይ በጋ ወራት የመኮትኮት የመንከባከብና ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ተብሏል፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ በዕለቱ የትራንስፖርት ሎጅስቲክ ሚንስቴርና ተጠሪ ተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች የአመቱን የመጀመሪያ ዙር የችግኝ ተከላ አካሂደዋል፡፡ በቀጣይ ሀምሌ 06/ 2014 ዓም 100,000 (መቶ ሺ) ችግኞችን እንደሚተከሉ በዕለቱ የተገኙ ሚንስቴር ዴታዎች ገልፀዋል ፡፡