Lideta Woreda 04 Communication Office

Lideta  Woreda 04 Communication Office በቂና የተሟላ መረጃ ያለው፣ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን ያጐ�

01/06/2026
ዛሬ ማልዳችሁ ወደ መስቀል አደባባይ የተመማችሁ የከተማችን ነዋሪዎች፣ ይህ ብልጽግናን ከመደገፍ ያለፈ ዴሞክራሲያዊ ሥርአትን የማፅናት የጀግንነት አውድ ነው። “በምርጫ ብቻ!” የሚለውን ታላቅ ...
26/05/2026

ዛሬ ማልዳችሁ ወደ መስቀል አደባባይ የተመማችሁ የከተማችን ነዋሪዎች፣ ይህ ብልጽግናን ከመደገፍ ያለፈ ዴሞክራሲያዊ ሥርአትን የማፅናት የጀግንነት አውድ ነው።
“በምርጫ ብቻ!” የሚለውን ታላቅ መልዕክት ለዓለም አስተላልፋችኋል፤ የሁል ጊዜ የአብሮነታችሁ መልዕክት ሀገር ማፅናት ነው፤ እናመስግናለን፤ ፅኑ!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ክብርት ከንቲባ Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ

በክ/ከተማችን  ተመርቀው ለህዝብ አገልግሎት ክፍት የሆኑ  2 ት/ቤቶች እና 3 የማህበረሰብ አቀፍ የህፃናት ማቆያዎች በፎቶ !!!!
25/05/2026

በክ/ከተማችን ተመርቀው ለህዝብ አገልግሎት ክፍት የሆኑ 2 ት/ቤቶች እና 3 የማህበረሰብ አቀፍ የህፃናት ማቆያዎች በፎቶ !!!!

24/05/2026

ለነገው ማህበረሰብ አብሮነት

በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ተገንብተው የተጠናቀቁ የህፃናት ማቆያና መጫዎቻ ቦታዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ።በክፍለ ከተማው በራስ አቅም ተገንብተው የተጠናቀቁ የህፃናት  የቀን እ...
24/05/2026

በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ተገንብተው የተጠናቀቁ የህፃናት ማቆያና መጫዎቻ ቦታዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ።

በክፍለ ከተማው በራስ አቅም ተገንብተው የተጠናቀቁ የህፃናት የቀን እንክብካቤ ማዕከላት እና መጫዎቻ ቦታዎች ተመርቀው በዛሬው እለት ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

በመርሀ ግብሩ ላይ አዲስ አበባ ከተማ ስሟና ግብሯ የተገናኘላት የብልፅግና ተምሳሌት የሆነች ከተማ ለማድረግ ብርቱ አመራር በመስጠት ብርቱውን የከተማዋን ነዋሪ በማሳተፍ ከፍ ያሉ ስራዎች መሰራታቸውን ተገልጿል።

በህብረተሰብ ተሳትፎ እና በመንግስት ካፒታል ችግር ፈቺ የሆኑ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን በዛሬው እለት ግንባታቸው ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ እና ግብአት የተሟላላቸው የህፃናት የቀን እንክብካኬ ማዕከላትና መጫዎቻ ቦታዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።

የትውልድ ስብራትን በመጠገን አገር ለመገንባት ፋይዳው የጎላ በመሆኑ ስትራቴጂክ ፅ/ቤት ተቋቁሞ፣ ደንብ ወጥቶለት፣ አሰራር ተዘርግቶለት የተቀናጀ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።

ትውልድ መገንባት አገርን ለመገንባት መሰረት ከመሆኑም በተጨማሪ ህፃናት መብቶቻቸው የመከበር እና በእንክብካቤ የማደግ ተፈጥሯዊም ህገ-መንግስታዊም መብት ስላላቸው የጋራ ርብርብ ያስፈልጋል።

በዛሬው እለት በከተማዋ ተገንብተው የተጠናቀቁ በቀዳማይ ልጅነት መርሀ-ግብር የተከናወኑ የህፃናት የቀን እንክብካቤ ማዕከላት፣ የህፃናት ማቆያ ና መጫዎቻ ቦታዎች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን እና እነዚህ ብዙ ካፒታል የፈሰሰባቸውን ፕሮጀክቶች ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዲጠብቅ ጥሪ ቀርቧል።

ከእንግዲህ በአዲስ አበባ ከተማ ልጆች በዕድላቸዉ ሳይሆን በእንክብካቤ ያደጋሉ!

በልደታ ክ/ከተማ የተገነቡ 2 ት/ቤቶችና 3  የህፃናት ማቆያዎች ተመረቁበልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረጉ።በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ...
24/05/2026

በልደታ ክ/ከተማ የተገነቡ 2 ት/ቤቶችና 3 የህፃናት ማቆያዎች ተመረቁ

በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረጉ።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እንደገለፁት ከለውጡ በፊት አብዛኞቹ ት/ቤቶች ለመማር ማስተማር ምቹ ያልሆኑ ምቹ የተማሪዎች መቀመጫ ያለነበራቸው ነበሩ ብለው ትውልድ ተኮር ሰው ተኮር የሆነው የለውጡ መንግስት ሀገር የምትገነባው በትምህርት መሆኑን እምነት ይዞ ት/ቤቶች ላይ በመስራት መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ችሏል በማለት ተናግረዋል።

ከለውጡ ቀደም ብሎ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ለመማር ሁሉም ህፃናት እድል የማያገኙበት ገንዘብ ያላቸው ብቻ የሚማሩበት ነበረ ያሉት ኢንጅነር ወንድሙ መንግስት ይህንን አስተሳሰብ በመቀየር ሁሉም ህፃናት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት የሚያገኙበትን ዕድል ፈጥሯል ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጲያን በፅኑ መሰረት ላይ ለማስቀመጥ የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናት ላይ መስራት ያስፈልጋል ብለው በዚህም የለውጡ መንግስት ለትምህርት ዘርፉ ትኩረት በመስጠት ከዩኒቨርስቲ የሚስተካከሉ ት/ቤቶችን ከመገንባት ባለፈ የተማሪዎች የምገባ ስርዓት በመዘርጋትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ የወላጆችን ሸክም እያቃለለ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ባደረጉት ንግግር የለውጡ መንግስት ሀገር የምትሰራው ትውልድ ሲሰራ ነው የሚል መርህን አንግቦ በትምህርት ዘርፉ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት አድርጓል ብለው በዚህም ባለፍት የለውጥ ዓመታት ደረጃቸውን የጠበቁ ለመማር ማስተማሩ ምቹ የሆኑ ት/ቤቶችን በመገንባትና በግብዓት የማሟላት ተግባር በማከናወን ትውልድ ግንባታ ላይ በትኩረት ሰርቷል ሲሉ ገልፀዋል።

ከለውጡ ወዲህ ደረጃቸውን የጠበቁ ምቹ፣ ሳቢና ማራኪ ት/ቤቶችን ከመገንባት ባለፈ ህፃናት ስለሚለብሱትና ስለሚበሉት እንዳይጨነቁ በግብዓትና በወላጅ ገቢ ማነስ ከትምህርታቸው ወደ ኃላ እንዳይቀሩ ለማድረግ በትኩረት መሰራቱን የገለፁት የትምህርት ቢሮ ኃላፊው በዚህም የወላጆችን ሸክም ያቃለለ የምገባ ስርዓትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ በስነ-ምግባር የታነፀ እና ውጤታማ የሆነ ትውልድ የመገንባት ሂደቱን አጠናክሮ ቀጥሏል በማለት ገልፀዋል።

የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደገለፁት የበጀት ዓመቱን ስንጀምር ከነዋሪዎቻችን ጋር ምክክር አድርገን ማህበረሰቡ ያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ነቅሰን በመያዝ ወደ ዕቅድ ቀይረን በተቀየረ 24/7 የስራ ባህል እቅዳችንን በመተግበር 70 ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለረጅም ዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ የማህበረሰቡ ችግሮች ምላሽ እንዲያገኙ አስችለናል ብለዋል።

አስተዳደሩ ትውልድ ግንባታ ላይ ትኩረት በማድረግ ትውልድን በስነ-ምግባር የሚያንፁ ፣ በአካልና በስነ-ልቦና የዳበረ እንዲሆን የሚስችሉ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በዚህም ት/ቤቶችን፣ የህፃናት ማቆያዎችን፣ የህፃናት መዋያዎችንና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን የቅድሚያ ቅድሚያ ሰጥተን በመገንባት ለአገልግሎት ክፍት እያደረግን ነው ሲሉ ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ የኑሮ ውድነትን የሚያቃልሉ ፣ትውልድን የሚቀርፁ፣ ለማህበረሰቡ ማህበራዊ እፎይታን የሚሰጡ ፕሮጀክቶችን ገንብተን በማስመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ይህንን ስራ ስናከናውን ከጎናችን የነበራቹህ ባለሀብቶች እና ነዋሪዎች ምስጋና ይገባቹሃል ብለዋል።

የሃይማኖት ተቋማት ለሰላም ግንባታ፣ ለህብረተሰብ ንቃተ ህሊና ማጎልበትና ለወንጀል መከላከል የሚያደርጉትን ተሳትፎ ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸዉ ተገለፀ።በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በ7ተኛ...
23/05/2026

የሃይማኖት ተቋማት ለሰላም ግንባታ፣ ለህብረተሰብ ንቃተ ህሊና ማጎልበትና ለወንጀል መከላከል የሚያደርጉትን ተሳትፎ ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸዉ ተገለፀ።

በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በ7ተኛው ሀገራዊ እና ክልላዊ ምርጫን በማስመልከት ከተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት የተወጣጡ አባቶች ጋር በሰላም፣ ፀጥታ እና ማህበራዊ መረጋጋት ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

በውይይቱ ወቅት ህብረተሰቡ ለሰላም ባለቤት በመሆን ማንኛውንም የፀጥታ ስጋትና ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ በቅድሚያ በመከላከል ከፀጥታ አካላት ጋር በትብብር መስራት እንዳለበት ተጠቁሟል።

እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች በስብከቶቻቸውና በማህበረሰብ ውስጥ በሚያደርጉት ተከታታይ ግንኙነት የጥላቻ ንግግሮችን፣ አሉባልታዎችንና የሰላም እንቅፋቶችን በመከላከል ለሀገራችን የተረጋጋ ሰላም መረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው ተመላክቷል።

በመድረኩ ላይ ሰላምና ፀጥታ የመንግሥት መዋቅር ብቻ ሳይሆን የህብረተሰቡ የጋራ ኃላፊነት መሆኑ ተጠቅሶ በተለይም የሃይማኖት አባቶች ህብረተሰቡን ወደ ሰላም፣ መቻቻልና አንድነት በመምራት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳላቸው ተገልጿል።

የሃይማኖት አባቶች በበኩላቸው በሀገራችን ሰላም እንዲጠናከርና ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ዜጋ የድርሻውን መወጣት እንደሚገባው እና ሰላም የሁሉም ዜጋ የጋራ እሴት መሆኑን በመግለፅ በቀጣይ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት ህብረተሰቡ በሰላም መርጦ እንዲመለስ ከህዝቡና ከፀጥታ አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

Address

Sarbet , Infront Of Vatican Embassy
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lideta Woreda 04 Communication Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share