Addis Ababa Design And Construction Works Bureau

Addis Ababa Design And Construction Works Bureau የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኝ መንግስታዊ ተቋም ነው፡፡

05/09/2026
ለነዋሪው እፎይታን የሰጡ  የአንድ ማዕከል የገቢያ ማዕከላት በአዳስ አበባየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኑሮ ውድነት መባባስ መንስኤ የሆኑትን የምርት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ የፍጆታ እና ...
05/09/2026

ለነዋሪው እፎይታን የሰጡ የአንድ ማዕከል የገቢያ ማዕከላት በአዳስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኑሮ ውድነት መባባስ መንስኤ የሆኑትን የምርት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ የፍጆታ እና የሰብል ምርቶች አቅርቦት ከአርሶ አደሮች፣ ከዮኔን እና ከባለሀብቶች ጋር በማስተሳሰር ምርት ወደ ከተማ በቀጥታ እንዲገባ በማድረግ ሸማቹ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የአንድ ማዕከል የገቢያ ማዕከላትን በተለያዩ ቦታዎች በመገንባት ለህዝብ ጥቅም እያዋለ ይገኛል፡፡

በተለይም በከተማዋ ለዋጋ ንረትና ለንግድ ሚዛን መዛባት ምክንያት የሆኑ ህገ-ወጥ ነጋዴዎች እና ደላሎች ላይ ህጋዊ እርምጃዎችን በመውሰድ በገበያው ላይ ይታይ የነበረውን የዋጋ ንረት በነዚህ የአንድ ማዕከል የገቢያ ማዕከላት አማካኝነት በማስቀረት ገቢያው እንዲረጋጋ ማድረግ ችሏል ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ ግንባታውን አጠናቆ ለህዝብ ክፍት ያደረገው 7ኛውን የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ለዚህ አይነተኛ ማሳያ ነው ።

በለሚ የአንድ ማዕከል ገቢያ በሸማቹ እና በአምራች መሀከል የቀጥታ ግንኙነት እንዲኖር በማድረግ ማህበረሰቡ ለዕለት ፍጆታ የሚጠቀምባቸውን የሰብል ምርቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬዎች፣ የበርበሬና የቅመማቅመም ምርቶች እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በአንድ ማዕከል መሸመት እንዲችሉ እድል ፈጥሯል ፡፡

በዚህ ሁለገብ የገቢያ ማዕከል የሚቀርቡ ምርቶች ከ15 እስከ 20 በመቶ የዋጋ ቅናሽ የሚሸጥበት፣ ዋጋ የሚያንረውን ህገ ወጥ የደላላ ሰንሰለት በመበጣጠስ ከአምራቹ ያልተቋረጠ ምርት የሚቀርብበትና የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና በመረዳት ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት የተቻለበት ስኬታማ ስራ ነው።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች በአዲስ አበባ የተለያዩ የቱሪዝም መዳረሻዎች እና የወንዝ ዳርቻ ልማትን ጎበኙ፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች በአዲስ አበባ ከአንጦጦ መቀጠያ እስከ ፒኮ...
05/09/2026

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች በአዲስ አበባ የተለያዩ የቱሪዝም መዳረሻዎች እና የወንዝ ዳርቻ ልማትን ጎበኙ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች በአዲስ አበባ ከአንጦጦ መቀጠያ እስከ ፒኮክ ፓርክ ድረስ የተሰሩትን የወንዝ ዳርቻ ልማትን ጉብኝተዋል:: ሰራተኞቹ የመዲናዋን አዲስ ገጽታና የቱሪዝም ሳቢነት የሚያጎሉ የመሰረተ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን ተመልከተዋል።

በጉብኝታቸውም በመዲናዋ የተከናወኑት የልማት ስራዎች እጅግ የሚደነቁ መሆናቸውን ጠቁመው፣ አዲስ አበባን የአፍሪካ የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን ሁሉን አቀፍ የልማት ስራ እንደሚደግፉ እና የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን በከተማዋ የሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ሰራተኞች በመዲናዋ የለሙትን የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዲጎበኙ በርካታ የማስተዋወቅ ስራን እያከናወነ ይገኛል::

03/09/2026

ከተስፍ መቁረጥ ወደ አዲስ ህይወት!

አምራችና ሸማቹ በቀጥታ የሚገናኝባቸው ልዩ የአዲስ አመት ባዛሮች በ11 ከፍለ ከተሞች ለህዝብ ክፍት ሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበዓላት ወቅት የሚከሰተውን የምርት እጥረትና የዋጋ ን...
03/09/2026

አምራችና ሸማቹ በቀጥታ የሚገናኝባቸው ልዩ የአዲስ አመት ባዛሮች በ11 ከፍለ ከተሞች ለህዝብ ክፍት ሆኑ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበዓላት ወቅት የሚከሰተውን የምርት እጥረትና የዋጋ ንረት ለመከላከል አምራቾች ከሸማች ጋር በቀጥታ የሚገናኝባቸው ልዩ የአዲስ አመት ባዘሮችን በ11 ከፍለ ከተሞች በዛሬው ዕለት ለህዝብ ከፍት አድርጓል፡፡

አስተዳደሩ በዛሬው ዕለት የአዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ ከእሁድ ገበያዎች በተጨማሪ በ11 ክፍለ ከተሞች የበዓል ባዛሮች በይፋ ያስጀመረ ሲሆን ሸማቾች ከትራንስፖርት እንግልት ነፃ በሆነ መልኩ በአቅራቢያቸው ከሚገኙ የሸማቾች ሱቆችና የባዛር ማዕከላት መሰረታዊ የግብርናና የኢንዱስትሪ ፍጆታ ምርቶችን ጨምሮ እንደ ሽንኩርት፣ ቅቤ፣ እንቁላል፣ ዱቄት፣ ዘይት እና የባልትና ውጤቶች እንዲሁም የሀገር ባህልና ዘመናዊ አልባሳትና የተለያዩ ጌጣጌጦች፣ የእደ ጥበብ ውጤቶች እና ልዩ ልዩ የፅዳት ዕቃዎች በስፋት ቀርበዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና የክፍለ ከተሞቹ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የ በዛሬው ዕለት የተከፈቱትን ባዛሮች በስፍራው በመገኙት በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን፤ ዛሬ ከተከፈተው ልዩ የአዲስ ዓመት ባዛሮች በተጨማሪ በከተማዋ በሚገኙ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች ላይ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው በቀጥታ እየቀረበ ይገኛል፡፡

እነዚህ የዘመን መለወጫ በዓል ልዩ ባዛሮች ከዛሬ ነሀሴ 28 ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 5/2018 ዓ.ም ድረስ በድምቀት የሚቆይ ሲሆን ነዋሪዎች ወደ ባዛሩ እና ወደ በገቢያ ማእከላት እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ገቢያ በመምጣት የቀረቡትን ሰፊ የገበያ አማራጮች በመጠቀም ተመጣጣኝ እና ጥራት ያለው ግብዓት መሸመት እንደሚችሉ ተነግሯል፡፡

03/09/2026

አዲስ አበባ ለህፃናት ምቹ የሆነች ከተማ!

03/09/2026

የትውልድ እና የእናቶች እፎይታ

03/09/2026

የነገውን ለማጨድ ዛሬን እንዝራ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬ...
03/09/2026

በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል።

‎በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል።

‎ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው።
‎ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Address

ስድስት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ህንፃ ላይ፡፡
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa Design And Construction Works Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ababa Design And Construction Works Bureau:

Shortcuts

Share