05/09/2026
በክፍለ ከተማው የሚገኙ የህብረት ስራ ማህበራት መጪውን በአላት ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ምርቶችን በስፋት ማቅረባቸውን ገለፁ።
ኮልፌ ኮሙኒኬሽን ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም
መጪውን በአላት ምክንያት በማድረግ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በክፍለ ከተማው የሚገኙ የሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ዝግጅት ማድረጋቸው ገልፀዋል።
በክፍለ ከተማው የሚገኙ የወይራ ቤተል፣ራዕይና ጀሞ የህብረት ስራ ማህበራት ለበአሉ የኢንዱስትሪና የተለያዩ የግብርና ምርቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረባቸውን በቂ ምርትም እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
ለበአሉ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ጤፍ፤ የጥራጥሬ እህሎች፤ዘይት፤ ሽንኩርት፤ እንቁላል ፤ ቅቤና ፣ ዱቄት የመሳሰሉ ምርቶችን ማቅረባቸዉንም ጠቁመዋል።
የክፍለ ከተማው የህብረት ስራ ፅህፈት ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሀረግ አብርሀ እንዳሉት በክፍለ ከተማዉ በሚገኙ 13 የሸማች ህብረት ሰራ ማህበራት እና 1 ዩንየን መጪውን በአል ታሳቢ ያደረጉ የግብርናና የኢንዱስትሪ እና ለበአሉ የሚያስፈልጉ ምርቶችን በበቂ መጠን መኖሩን ገልፀዋል።
ማህበራቱ አስፈላጊዉን ዝግጅት ማድረጋቸዉን የጠቀሱት ሀላፊዋ ለበአሉ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን ጤፍ፤ የጥራጥሬ እህሎች፤ዘይት፤ ሽንኩርት፤ እንቁላል ፤ ቅቤና ዱቄት የመሳሰሉ ምርቶችን በማቅረብ ሰዉ ሰራሽ የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በአላቱን ታሳቢ ያደረጉ መሰረታዊ የፎጆታ ምርቶች በማህበራቱ ሱቆችና መጋዘኖች በቂ መጠን መኖሩንና በቀጣይ ቀናቶችም በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል የገለፁት ወ/ሮ ሀረግ አንድ ኪሎ ስጋም በሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ስጋ ቤቶች በ1200 ብር እንደቀረበም አንስተዋል።
ሲገበያዩ ያገኘናቸው ሸማቾች እንደገለፁት በአቅራቢያቸው በሚገኙ የሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘታቸውን ገልፀዋል።