01/09/2026
የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በ2019 በጀት ዓመት 9 ቢሊዮን ቶን ጭነት ለማጓጓዝ አቅዷል
++++++++++++++++
- የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በተያዘው የ2019 በጀት ዓመት 9 ቢሊዮን ቶን ጭነት ለማጓጓዝ ማቀዱንና ተቋሙን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማስደገፍ አገልግሎቱን ለማቀላጠፍ እየሠራ መሆኑን አስታወቀ።
የተቋሙ የዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዋና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ስንታየሁ ኃይለማርያም እንደገለጹት፤ በ2018 በጀት ዓመት 7 ቢሊዮን ቶን ጭነት አጓጉዟል። በጀት ዓመቱ 157 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቷል። ከ500 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘት ተችሏል ብለዋል።
በዚህ በጀት ዓመት ደግሞ ከባለፈው ዓመት በ2 ቢሊዮን ቶን ብልጫ ያለው 9 ቢሊዮን ቶን ጭነት በማጓጓዝ የሕዝብ አገልጋይነቱንና ትርፋማነቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የ2019 በጀት ዓመት በ50 ቢሊዮን ብር የካፒታል ኢንቨስትመንት አይሲቲን (ICT) ጨምሮ የተቋሙን አሠራር ለማቀላጠፍና የጭነት ሂደቱን ከመነሻ እስከ መዳረሻ በቴክኖሎጂ ለመቆጣጠር በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 850 ሚሊዮን ብር ማዳን የቻለ ሲሆን፣ ከደረቅ ወደቦች፣ ከፋይናንስና ቴክኖሎጂ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመሥራት የደንበኞችን የጊዜና የገንዘብ ብክነት ለመቀነስ ማቀዱንም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል በመካከለኛው ምሥራቅ በተከሰተው የፖለቲካ ውጥረት ምክንያት ጊቤ የተባለችው መርከብ በሆርሙዝ ሰርጥ ለ116 ቀናት ለመቆም መገደዷ፣ የዱቤ ተጠቃሚዎች ክፍያ አለመፈጸም፤ በጂቡቲ ወደብ ብቻ መወሰን በሥራው ላይ ጫና ፈጥረው እንደነበር አቶ ስንታየሁገልጸዋል።
በክፍለዮሐንስ አንበርብር
#ኢትዮጵያ