Pawe Agricultural Research Center

Pawe Agricultural Research Center The center was established in 1986, a year after a devastating famine, to support settlers in the region by providing improved technologies.

it evolved into one of EIAR's main research centers.

ሐምሌ 28፣ 2018 ዓ.ም — የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል በ2018/19 ምርት ዘመን በግብርና ኤክስቴንሽን ምርምር ክፍል ከወረዳዎች ጋር በመተባበር እየሰራባቸው የሚገኙትን የቴክኖሎጂ ማስተ...
05/08/2026

ሐምሌ 28፣ 2018 ዓ.ም — የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል በ2018/19 ምርት ዘመን በግብርና ኤክስቴንሽን ምርምር ክፍል ከወረዳዎች ጋር በመተባበር እየሰራባቸው የሚገኙትን የቴክኖሎጂ ማስተዋወቅ የምርምር ስራዎች የመስክ ምልከታ አካሄደ።
የመስክ ምልከታው በመተከል ዞን ስር በሚገኙት በዳንጉር እና ፓዌ ወረዳዎች ላይ የተከናወነ ሲሆን፣ የማዕከል ዳይሬክተር አቶ ደስታ አበበ እና ሌሎች የምርምር ማናጅመንት አካላት በመገኘት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በምልከታው ወቅት የተመለከቱዋቸው ዋና ዋና ስራዎች፡
• የኩታ ገጠም ስራዎች (ክላስተር):- የአኩሪ አተር፣ ሩዝ እና ሰሊጥ ክላስተር ስራዎች።
• የቅድመ ሰርቶ ማሳያ ስራዎች:- የበቆሎ፣ የሩዝ፣ የመኖ እና የለውዝ ቅድመ ሰርቶ ማሳያ የምርምር ስራዎች።
ማናጅመንቱ በቦታው ተገኝቶ ባደረገው ምልከታ፣ እየተሰሩ ያሉት የቅድመ ሰርቶ ማሳያ እና ሰፋፊ የኩታ ገጠም ስራዎች በአግባቡ መሬት ላይ ማረፋቸውንና ውጤታማ በሆነ መልኩ መሰራታቸውን አረጋግጧል። እነዚህ የምርምር ስራዎች ለአርሶ አደሩ የቴክኖሎጂ እና የዕውቀት ሽግግርን በአግባቡ የሚያሳልጡ መሆናቸው በመስክ ምልከታው ተገልጿል።
የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል — ለምርታማነትና ለዕውቀት ሽግግር!!

#መተከል #ዳንጉር #ፓዌ #ኢትዮጵያ

PARC 2018/19 cropping season, the Agricultural Extension Team of the Pawe Agricultural Research Center (ARC) has been ac...
23/07/2026

PARC 2018/19 cropping season, the Agricultural Extension Team of the Pawe Agricultural Research Center (ARC) has been actively implementing robust Pre-Extension Demonstration (PED) and Large-Scale Demonstration programs within its targeted working areas (Metekel and neighboring zones), vigorously working to ensure food security and expand agricultural technologies.

(ፓዌ፦ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል በምትኬ ተፋሰስ ላይ ያከናወነውን የምርምርና ልማት ስራዎችን አጠናቆ አስረከበ።የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል የአርሶ አደሮችን ግ...
06/07/2026

(ፓዌ፦ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል በምትኬ ተፋሰስ ላይ ያከናወነውን የምርምርና ልማት ስራዎችን አጠናቆ አስረከበ።

የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል የአርሶ አደሮችን ግንዛቤ በማሳደግ እና ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ ምርትና ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ በትጋት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል ። ምርምር ማዕከሉ ባለፉት ዓመታት በምትኬ ተፋሰስ ላይ ሲያከናውን የነበረውን የምርምርና ልማት ሥራን በማጠናቀቅ፥ ቀጣይ ተፋሰሱን ለሚያስተዳደሩ ተቋማትና ተጠቃሚ ባለድርሻ አካላት የርክክብና የላቀ የእውቅና የምስክር ወረቀት የመስጠት ስነ-ስርዓት በዛሬው ዕለት በድምቀት አካሂዷል።

የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ደስታ አበበ እንደገለጹት፤ምትኬ ተፋሰስ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ተራቁቶ ለአካባቢው አርሶ አደሮች ምንም ዓይነት ጥቅም በማይሰጥበት ደረጃ ላይ እንደነበር አስታውሰዋል። ምርምር ማዕከሉ ተፋሰሱን ተራክቦ አስፈላጊውን ጥናት በማከናወን ባደረገው ዘርፈ-ብዙ ርብርብ አሁን ላይ ውጤታማ መሆን መቻሉን ገልጸው፥የተከናወኑ የልማት ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የውል ስምምነት የፈጸሙ አካላት አካባቢውን በባለቤትነት የመጠበቅና የመንከባከብ ከፍተኛ ሃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም ሎዳሞ በስነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የምርምር ማዕከሉ ለአርሶ አደሮች የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅና በማስረጽ ስኬታማ እንዲሆኑ ትርጉም ያለው ሥራ እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ማዕከሉ ባለፉት ጊዚያት ምትኬ ተፋሰስን መልሶ በመልማት ጥቅም ላይ እንዲውል ከፍተኛ ወጭ እና ጉልበት ማውጣቱን ያነሱት ምክትል አስተዳዳሪው፥ በቀጣይም የተፋሰሱ ህልውና ተረጋግጦ የሚፈለገው ውጤት እንዲመዘገብ የወረዳው አስተዳዳር ምክር ቤት ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመቀናጀት ከሚያደርገው ጥረት ባለፈ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ተጠቃሚ አርሶ አደሮች አስፈላጊውን ጥበቃና እንክብካቤ በማድረግ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል።

የማዕከሉ የአፈርና ውሃ አያያዝ ምርምር የስራ ሂደት ተጠሪ የሆኑት የኔሰው አሳዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የምትኬ መማማሪያ ተፋሰስ በተገቢው መንገድ ተጠብቆ ለአካባቢው ነዋሪዎች የሚፈለገውን ውጤት እንዲሰጥ ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ ገልፀዋል።

በዚሁ ታላቅ መርሃ ግብር ላይ በፓዌ ወረዳ ቀበሌ 2 መንደር 23/45 እና 10 የሚገኘውን "ምትኬ መማማሪያ ተፋሰስ" የአካባቢ መራቆትንና የተፈጥሮ ሀብት መመናመንን በመከላከል፣ የስነ-ምህዳርን ሚዛን በመጠበቅ፣ የውኃ ሀብትን በማሳደግ እና የምድር ሙቀትን አማቂ ጋዞችን ልቀት በመቀነስ የመሬት የማምረት አቅም ተጠብቆ ለወደፊቱ ትውልድ እንዲተላለፍ ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ የላቀ የእውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል።

በመረሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ የላቀ የእውቅና የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ባለድርሻ አካላት ለኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት፤ ለመተከል ዞን ግብርና መምሪያ፤ለፓዌ ወረዳ መስተዳድር ጽ/ቤት፤ለፓዌ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት፤ለፓዊ ወረዳ ፖሊስ መምሪያ፤ለፓዌ ወረዳ ቀበሌ 2 መንደር 23/45 እና 10 ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና አርሶ አደሮች እንዲሁም ለፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል እና የማዕከሉ የአፈርና ውሃ አያያዝ ምርምር የስራ ሂደት ናቸው።

23/06/2026
የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል በመተከል እና አዊ ዞን ወረዳዎች ለሚገኙ የግብርና ባለሙያዎች እና ለተመረጡ አርሶ አደሮች በአኩሪ አተር፣ ሩዝ እና ሰሊጥ ሰብሎችን በኩታ-ገጠም/ክላስተር የአመራ...
11/06/2026

የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል በመተከል እና አዊ ዞን ወረዳዎች ለሚገኙ የግብርና ባለሙያዎች እና ለተመረጡ አርሶ አደሮች በአኩሪ አተር፣ ሩዝ እና ሰሊጥ ሰብሎችን በኩታ-ገጠም/ክላስተር የአመራረት ዘዴ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ።

(ሰኔ 3፣ 2018 ዓ.ም) ምርምር ማዕከሉ በመተከል ዞን ስር ለሚገኙ አራት ወራዳዎች (ፓዌ፣ዳንጉር፣ማንዱራ እና ጉባ) እንዲሁም በአዊ ዞን ለሚገኘዉ ለጃዊ ወረዳ ባለሙያዎች የክላስተር ተሳታፊ አርሶ አደሮች የአቅም ግምባታ ስልጠናዉ ተሰጥቷል፡፡

የፓዊ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ደስታ አበበ ለስልጣና ተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የስልጠና የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የስልጠናዉን ቆይታ አስመልከተዉ መልዕክት አስተላለፈዋል፡፡ አቶ ደስታ አበበ በመልዕክታቸዉ ምርምር ማዕከሉ በየዓመቱ በየደረጃዉ ላሉ የግብርና ባለሙያዎች እና አርሶ አደሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የአቅም ግምባታ ስልጠናዎችን እና በማዕከሉ የወጡ ቴክኖሎጂዎችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡

አቶ ደስታ አክለዉም ምርምር ማዕከሉ በኩታ-ገጠም እርሻ ለሚሰሩ የምርምር ሥራዎች የምናቀርባቸዉ ምርጥ ዘሮች በተዘዋዋሪ (revolving seed system) መልኩ ለአርሶ አደሮች እንዲቀርቡና በቀጣይ ተደራሽ ያልሆኑ አርሶ አደሮች እንዲያገኙ እና የቴክኖሎጂ እና የዕዉቀት ሽግግሩ በተሳለጠ መልኩ እንዲቀጥል በአፅንኦት አሳስበዋል፡፡
እንደ ምርምር የሚዉጡ ቴክኖሎጂዎች በኩታ-ገጠም እና ሌሎች የአሰራር ስልቶችን በመጠቀም ለተጠቃሚዎቸ ማስተዋወቅ እና የቴክኖሎጂ ስርፀትን አጠናክሮ መቀጠል ይቻል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የየድድሻዉን መወጣት አለበት በማለት አቶ ደስታ በመልዕክታቸዉ ገልፀዋል፡፡

በፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል የግብርና ኤክስቴንሽን ምርምር ሥራ ሂደት ተጠሪ የሆኑት አቶ ታከለ አጥናፉ የግብርና ምርታማነትን ለመጨመር፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ የአርሶ አደሩን መተዳደሪያ ማሻሻል እና ዘላቂነት ያለዉ ልማትን ለማረጋገጥ በምርምር የሚሰጡ ምክረ-ሃሳቦችን በአግባቡ መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ዘመናዊ እና ገበያ ተኮር አገልግሎት ጊዜው የደረሰበትን የዲጂታል ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ለመተግበር እንደ "ማማ ዩኒየን" ባሉ የገበያ ትስስሮች አማካኝነት አርሶ አደሩ ምርቱን በተሻለ ዋጋ እንዲሸጥ እና በግብርናው ዘርፍ ተጠቃሚ እንዲሆን የሚያስችሉ አዳዲስ የአሰራር ስልቶችን መከተልም ያስፈልጋል ብለዋል።

አቶ ታከለ አክለዉም የኩታ-ገጠም አመራረት የባለድርሻ አካላት ትብብር እና ቁርጠኝነት የሚጠይቅ በመሆኑ ስኬታማ እና ዉጤታመማ የኩታ-ገጠም ስራን ለመስራት እና የአርሶ አደሩን ምርታማነት በመጨመር ኑሮዉን ማሻሻል ይቻል ዘንድ ሁሉም የየድርሻዉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል፡፡
የኩታ-ገጠም/ክላስተር እርሻ፤ የአኩሪ አተር፣ ሩዝ እና ሰሊጥ ሰብሎች አመራረት እና አያያዝ ሥልጠናዎች እንዲሁም የሰብል በሽታ፣ተባይ እና ቁጥጥር እና የዘር አመራረት እና አያያዝ ስልጠናዎች በሚገባ በሚመለከታቸዉ የማዕከሉ ተመራማሪዎች ለግብርና ባለሙያዎች እና አርሶ አደሮች ተሰጥተዋል፡፡

የመተከል ዞን ግብርና መምሪያ ተወካይ አቶ ዘዉዱ ፀጋዬ ከሁሉም ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ስልጠናዉን የወሰዱ ባለሙየዎች በወሰዱት ስልጠና መሰረት አርሶ አደሮችን ማስልጠን እና በተግባር በተሰጠዉ ስልጠና እና ምክረ-ሃሳብ መሰረት ወደ መሬት ማዉረድ ያስፈልጋል በማለት መልዕክታቸዉን በማስተላለፍ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡
አቶ ዘዉዱ በመልዕክታቸዉ በኩታ-ገጠም የሚሰሩ ሰብሎች እንደ ዞን ትልቅ የዘር ምንጭ ሁነዉ የዞኑን የዘር ጥያቄ የሚመልሱ ስለሆነ አስፈላጊዉን ግብዓት እና ሙያዊ ድጋፍ በማድረግ በልዩ ትኩረት ሊሰሩ ይገባል በማለት የስራ መመሪያ እና አቅጣጫ ለሁሉም ወረዳዎች አስተላለፈዋል፡፡
ከሁሉም ወረዳዎች የተገኙ የግብርና ባለሙያዎች እና የወረዳ ግብር ፅ/ቤት ኃላፊዎችም እንደ ወረዳ አስፈለላጊዉን ቅድመ ዝግጅት ያደረጉ መሆኑን በመግለፅ ለቀጣይ ሥራዎችም በተሰጠዉ ስልጠና እና ምክረ-ሀሳብ ለመተግበር ቁርጠኛ መሆናቸዉን ገልፀዋል፡፡ በመጨረሻም የመተከል ዞን ግብርና መምሪያ ተወካይ አቶ ዘዉዱ የተሠጠዉ ስልጠና ዉጤታማ እንደነበር በመግለፅ በተሰጠዉ ስልጠና መሰረት ሥራዎች መሬት ላይ አሳርፈን በዉጤት ያገናኘን በማለት የዕለቱን የስልጠና ፕሮግራም ዘግተዋል፡፡

“የማር ምርታማነትን ለማሳደግ የንብ ማነብ ሥራን ማዘመንና የከተማ ግብርናን ማጠናከር ወሳኝ ነው”ፓዌ - ግንቦት 28/2018 ዓ.ምየፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል የማር ምርታማነትን ለማሳደግ የ...
05/06/2026

“የማር ምርታማነትን ለማሳደግ የንብ ማነብ ሥራን ማዘመንና የከተማ ግብርናን ማጠናከር ወሳኝ ነው”

ፓዌ - ግንቦት 28/2018 ዓ.ም

የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል የማር ምርታማነትን ለማሳደግ የንብ ማነብ ሥራን ማዘመን፣ እንዲሁም የከተማ ግብርናን አካቶ በዘርፉ መሥራት ወሳኝ መፍትሔ መሆኑን አስታወቀ።

ምርምር ማዕከሉ በመተከል ዞን ፓዌ ከተማ 02 ቀበሌ ለሚገኙ አዲስ የተደራጁ አርሶ አደሮች እና የግብርና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሰጥቷል። ሥልጠናው የንብ ማነብ ዕውቀትና ክህሎትን በማሳደግ፣ ባህላዊ አሠራርን ወደ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመቀየር እና የከተማ ግብርናን ለማጎልበት ያለመ ነው።

የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ደስታ አበበ እንደገለጹት፣ ንብ ማነብ ለዜጎች ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ከመሆኑ ባሻገር ለምግብ ዋስትና፣ ለሰብል ምርታማነት መጨመር እና ለአየር ንብረት ጥበቃ ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል። በተለይም የከተማ ግብርናን በንብ ማነብ ስራ በማቀናጀት፣ የከተማ ነዋሪዎች ባላቸው ውስን ቦታ ሳይቀር ምርታማ መሆን እንደሚችሉና ለምግብ ዋስትናው ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚችሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ከፍተኛ ተመራማሪ አቶ ሀብቴ አረጋ በበኩላቸው፣ ማዕከሉ ያለውን ክፍተት በመለየት ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም መሰረት ምርታማነትንና ጥራትን ለማሳደግ የተሻሻሉ ዘመናዊ የቀርከሃ ቀፎዎች እና የንብ ቀሰም እፅዋት ቴክኖሎጂዎችን ምርምር ማዕከሉ በማስተዋወቅ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝም አስረድቶል።

እነዚህ ቴክኖሎጂዎች በገጠር ብቻ ሳይሆን በከተማ ግብርና መዋቅር ውስጥም በቀላሉ ተግባራዊ የሚደረጉ ናቸው ብለዋል።

የፓዌ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አይቸው ሞገስ እንደገለጹት፣ አርሶ አደሮች እና የከተማ ግብርና ተሳታፊዎች የቴክኖሎጂ ድጋፉን ተቀብለው ወደ ተግባር እንዲገቡ ከቀበሌ እስከ ወረዳ ባሉ የግብርና ባለሙያዎች በኩል አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።

በመጨረሻም ምርምር ማዕከሉ ከዘርፉ ተገቢውን ጥቅም ለማግኘት፣ ከንብ አናቢዎች፣ ማኅበራት፣ ተቋማት እና የከተማ ግብርና ተሳታፊዎች ጋር በቅንጅት እንደሚሠራ አረጋግጧል።

በፓዌ የግብርና ምርምር ማዕከል አርሶ አደሮችን ታሳቢ ያደረገ የካሼውነት ፍራፍሬና የሞቃታማ አካባቢ ቡና  ዝርያዎች አመራረት ስልቶች ላይ ያተኮረ ተግባራዊ ስልጠና ተሰጥቷል።በሆርቲካልቸር ምር...
29/05/2026

በፓዌ የግብርና ምርምር ማዕከል አርሶ አደሮችን ታሳቢ ያደረገ የካሼውነት ፍራፍሬና የሞቃታማ አካባቢ ቡና ዝርያዎች አመራረት ስልቶች ላይ ያተኮረ ተግባራዊ ስልጠና ተሰጥቷል።

በሆርቲካልቸር ምርምር ፕሮግራም አማካኝነት በካሼዉነት እና በሞቃታማ አካባቢዎች ለሚበቅሉ የቡና ዝርያዎች ሲከናወን የቆየው የምርምር እና የማላመድ ስራ አበረታች ውጤቶችን ማስመዝገቡን የፓዌ የግብርና ምርምር ማዕከል ገለጸ።

በዚህም መሰረት፣ ለተለያዩ የአየር ንብረት ሁኔታዎች ተስማሚ ሆነው የተገኙት የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች ለግብርና ማህበረሰቡ የማስተዋወቅ ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል።
የሆርቲካልቸር ምርምር ፕሮግራም በከፍተኛ ጥንቃቄ የካሼዉነት እና በሞቃታማ አካባቢዎች ተስማሚ የሆኑ የቡና ዝርያዎችን ለመለየትና ለማላመድ ጥልቅ ጥናቶችን ሲያካሂድ ቆይቷል።

የአካባቢውን የስነ-ምህዳር ሁኔታ መሰረት በማድረግ ምርታማነታቸው የላቀ፣ በሽታን የመከላከል አቅማቸው ከፍተኛ እና ለገበያ ተፈላጊነት ያላቸውን ዝርያዎች በማግኘት በአሁኑ ወቅት በምርምር የተገኙት እነዚህ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ለአርሶ አደሩ እንዲደርሱ እና በስፋት እንዲተገበሩ የማስተዋወቅና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

ለዓመታት ሲካሄድ የቆየው የመስክ ምርምር አሁን ላይ ወደ ተግባራዊ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። አርሶ አደሮቻችን እነዚህን ምርጥ ዝርያዎች በመጠቀም ምርታቸውን በጥራትና በብዛት እንዲያሳድጉና የኑሮ ደረጃቸውን እንዲያሻሽሉ ምቹ ሁኔታዎችን እየፈጠርን ነው" ሲሉ ስልጠና የሰጡት የዘርፉ ባለሙያዎች ገልጸዋል።
በቡና እና ሌሎች አትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ላይ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ የጋራ ውይይቶችና የመስክ ጉብኝቶች ተደርገዋል።

ምርምር ማዕከሉ አርሶ አደሩ ዘመናዊ የቡና አዝመራ ቴክኖሎጂዎችን እንዲጠቀም በማበረታታት፣ የቡና ምርትን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማሳደግና የኢትዮጵያን የቡና የውጭ ንግድ ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ላይ ይገኛል።

05/05/2026
የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክትበፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል ለ6 ዓመት ተመራማሪነት እና የስራ ሂደት ተጠሪ ሆነው ያገለገሉ፣ ለ4 ዓመታት ደግሞ የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ሆነው...
30/04/2026

የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት

በፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል ለ6 ዓመት ተመራማሪነት እና የስራ ሂደት ተጠሪ ሆነው ያገለገሉ፣ ለ4 ዓመታት ደግሞ የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ሆነው ካገለገሉ በኋላ አዲስ ወደ ተከፈተው የወረኢሉ ግብርና ምርምር ማዕከል በመዛወር ከማቋቋም ባሻገር እስከ ተሾሙበት ቀን ድረስ ለ3 ዓመታት ዳይሬክተር ሆነው አገልግለዋል። በቆዩባቸው ጊዜያትም ተቋሙን ውጤታማ ያደረጉ ስራዎችን አከናውነዋል።

ለሀገርና ለወገን የሚተርፍ ዕውቀትና የሥራ ትጋት የታጠቁት የቀድሞ ሥራ ባልደረባችን አቶ ደሳለኝ ተሻለ፤ ላለፉት 13 ዓመታት በግብርናው የምርምር ዘርፍ ያሳዩት ቁርጠኝነት ዛሬ ለታላቅ አገራዊ ኃላፊነት አብቅቷቸዋል።

እነዚህን ተከታታይ ውጤታማ የሥራ ጉዞዎችን ተከትሎ፣ በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አማካኝነት በኢትዮጵያ ግብርና ሚኒስቴር የእርሻና ሆርቲካልቸር ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ሆነው ተሹመዋል።

ከመሠረቱ ተነስተው ዕውቀትንና ልምድን አከማችተው፣ ዛሬ ለዚህ ከፍተኛ አገራዊ ኃላፊነት በመብቃትዎ ታላቅ ኩራት ይሰማናል።
ይህ ሹመት የልፋትዎ ውጤት፣ የትጋትዎ ምንዳ ነው። በአዲሱ የሥራ መስክዎ የኢትዮጵያን ግብርና ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግሩ ሙሉ እምነታችን ነው።"

ለዚህ ስኬትም የፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል በመሉ የማዕከሉ ሠራተኞች ስም የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፏል።

(ፓዌ:-መጋቢት 29/2018 ዓ.ም) በፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል ለጥበቃ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ።በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት (EIAR) ስር በሚገኘው በፓዌ ግ...
08/04/2026

(ፓዌ:-መጋቢት 29/2018 ዓ.ም) በፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል ለጥበቃ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ።

በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት (EIAR) ስር በሚገኘው በፓዌ ግብርና ምርምር ማዕከል፣ የመሠረታዊ አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ ስር ለሚገኙ የጥበቃ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጥቷል።

ሥልጠናውን የሰጡት የመሠረታዊ አገልግሎት ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ መርከቡ ደግዋለ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የጥበቃ ሠራተኞችን የሥራ አፈጻጸም እና ግንዛቤ ማሳደግ ነው።

ይህ ሥልጠና የማዕከሉን ደኅንነት እና የጥበቃ ሥራዎችን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አሰረድተዋል። ተሳታፊዎቹም በሥራቸው ላይ ሊያጋጥሟቸው ስለሚችሉ ጉዳዮች እና ስለሚጠበቅባቸው ኃላፊነት ሰፊ ግንዛቤ አግኝተዋል።

በመጨረሻም፣ እንዲህ ያሉ አጫጭር ሥልጠናዎች የሠራተኞችን አቅም በመገንባት ረገድ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን የማዕከሉ የሥራ ኃላፊዎች ገልጸዋል።

Address

Metekel, Pawe
Addis Ababa
25

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Pawe Agricultural Research Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share